Monday, November 3, 2025

የማኅበራዊ ዘመቻው መካተት ያለባቸው ሐሳቦች 

፩. በኦርቶዶክሳውያን ላይ የጥቃት አድራሹ አካል ከመንግሥት ጋር በመናበብ የሚሠራው ጠቅላይ ቤተ ክህነት እና  ሲኖዶስ ስለሆነ 
ለችግራችን ምንጭ አድርጎ በመቁጠር ድምጽ ማሰማት። 

፪. የጠቅላይ ቤተ ክህነት ወይም ቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ ጉዳቱ ወደ ደረሰበት አካባቢ በመሄድ ወገኖቻችንን እንዲጎበኝና እንዲያጽናና መጠየቅ።

፫. በጉዳቱ አካላቸውን ንብረታሸውን ላጡ ወገኖቻችን አስቸኳይ እርዳታ እንዲያደርግ መጠየቅ።

፬. በጉዳቱ ሰማእትነት ለተቀበሉ ወገኖች ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለአረርቲ ክርስቲያኖች እንዳደረገው ጸሎተ ፍትሐት እንዲያደርግ በተመሳሳይ ቀን በሁሉም አድባራት እንዲደረግ ጥያቄ ማቅረብ።

፭. ሁሉም አህጉረ ስብከቶች ለዚህ ጉዳት መግለጫ እንዲሰጡ መጠየቅ ካልሆነ ከገዳያችን ለይተን አናያቸውም።

፮. በቀጣይ ይህ ችግር እንዳይከሰት መፍትሔ የሚለውን በአስቸኳይ በዝርዝር ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ እንዲያሳውቅ። 

፯. በአርሲ ሃገረ ስብከት በተደጋጋሚ ከፍተኛ ተጋድሎ ሰማእትነት የተቀበሉ የሰማእታት ልጆች ሕጻናት ቤተክህነቱ ተቀብሎ በማሳደጊያ እንዲወስዳቸውና እንዲያሳድግ መጠየቅ። 



ንዋይ ካሳሁን

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

No comments:

Post a Comment