Wednesday, April 24, 2013

በአዲስ አበባ 3 ዓመት አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው የቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ቦታ የኢንደስትሪ ዞን ነው በማለት ፈረሰ

ቅዱስ ሩፋኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 15 2005 ዓ.ም)፡- በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 የሚገኝው የቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን በኢንደስትሪ ዞን ላይ የተሰራ ነው በሚል የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ለቅዱስ ሲኖዶስ በጻፈው ደብዳቤ 24 ሰዓት ሳይሞላው ማፍረሱን የደብሩ ኃላፊዎች አስወቁ፡፡

ሚያዚያ 9 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ አንድ ሰዓት ሲሆን የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ ኤልሳቤት መንግስቱ የደብሩን ኃላፊዎች በጽ/ቤታቸው እንዲገኙ የስልክ ጥሪ በማድረግ ቤተክርስቲያን እዲያፈርሱ የነገሯቸው መሆኑን ያስረዱት የደብሩ ኃላፊዎች ቤተ ክርስቲያን የማፍረስ ስልጣን  የእነሱ አለመሆኑን በመግለጻቸው በማግስቱ ጠዋት 3 ሰዓት ወረዳው ለሲኖዶስ የላከው ደብዳቤ ይዘው ከወረዳው ተወካይ ጋር በሲኖዶስ ተገናኝተው እየተወያዩ ሳለ የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ በሶስት መኪና ፖሊስ በመታገዝ በሕገ ወጥ መንገድ እንዲፈርስ ማድረጋቸው የደብሩ ኃላፊዎች  አስታወቁ፡፡

ስለ ዴር ሡልጣን ገዳም የኢትዮጵያው ቅ/ሲኖዶስ ከግብጽ ቅ/ሲኖዶስ ጋራ ይወያያል


    His Holiness on Interview
  • ፓትርያሪኩ የቅድስት ሀገር የታሪክና ቅድስና ይዞታችንን ለማስከበር ሕዝባዊ ዲፕሎማሲው ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል
  • ፓትርያሪኩ የ፳፻፭ ዓ.ም በዓለ ትንሣኤ የኢየሩሳሌም ተሳላሚ ምእመናንን አሰናብተዋል፤ እጅጋየሁ በየነ ሕገ ወጥ ጥቅም የምትሰበስብበት ‹አስጎብኚና የጉዞ ወኪል› በስንብት መርሐ ግብሩ አልተካተተም
  • ‹‹የዴር ሡልጣን ችግር ከመካከለኛው ምሥራቅ ጠቅላላ ገጽታዎች ተለይቶ መታየት የለበትም፡፡›› /በግብጽ መንግሥታዊ ሥልጣን የያዘው የእስላም ወንድማማቾች አቋም/
  • ‹‹ጉዳዩ ብሔራዊ ስለኾነ ከዐረብ ወንድሞቻችንና ከእስላሞች ጋራ ካልኾነ በቀር ወደ ኢየሩሳሌም አንገባም፡፡ ይህን በተመለከተ ሁላችንም በአንድነት ቆመናል፡፡›› /ፖፕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ዴር ሡልጣንን በተመለከተ በእስራኤል ላይ የቱሪዝም ጫና ለመፍጠር የሞከሩበት ጋዜጣዊ መግለጫ/
  • ‹‹ኢትዮጵያውያን ምእመናን በታሪክ ይዞታችንና በወገኖቻችን መካከል በብዛት መገኘት ለቅድስና ይዞታችንና ለወገኖቻችን ክብር በቀላሉ የማይገመት ዋስትና ያለው ነው፡፡ ጉዟችን ከሁሉም አቅጣጫ ድጋፍ እያገኘ በበለጠ ከቀጠለ በታሪክ ይዞታችን ላይ ያለው ችግር መፍትሔ አግኝቶ የመንፈስ ዕረፍትና ርካታ እንደሚገኝ ተስፋ አለን፡፡›› /በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ ለተሳላሚዎች ከተናገሩት/

Friday, April 19, 2013

ከሸፈ እንዴ?! ‹‹ዜና ቤተ ክርስቲያን›› ጋዜጣ በመጽሔት ቅጽ መታተም ጀመረ!


His Holiness Abune Matyas Zena BeteK Magazine Cover
  • መጽሔቱ የቤተ ክርስቲያንን የሕዝብ ግንኙነት ሥራ የሚያጠናክር ነው፡፡
  • በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች በየሩብ ዓመቱ በላቀ የኅትመት ጥራት ይዘጋጃል፡፡
  • አዘጋጂው በአዲስ መልክ የተዋቀረው የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው፡፡
  • የዝግጅቱ ውጥን ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በ፳፻፭ ዓ.ም የበጀት ዓመት ለማካሄድ ካቀደው ተቋማዊ የአደረጃጀት ለውጥና የወቅታዊ እንቅስቃሴዎችን መረጃ በተሻለ አሠራር ከመቀመር አኳያ በመምሪያው የሕዝብ ግንኙነት ቁልፍ ተግባራት ውስጥ ቀደም ብሎ ዓላማና ግብ ተወስኖለት የተካተተ እንጂ ከፓትርያሪኩ ‹‹የዜና መዋዕል ዝግጅት›› ጋራ ፈጽሞ የተያያዘ አይደለም፡፡
  • መጽሔቱ ቤተ ክርስቲያናችን በኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መስኮች የምታከናውናቸው ተግባራትና ውጤቶቻቸው በአገር ውስጥና በውጭ ባለድርሻ አካላት እንዲታወቁ እንዲሁም ‹‹ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት ስትራቴጂ›› ላይ አተኩሮ ይዘጋጃል፡፡
  • በመጽሔቱ ዝግጅት ሂደት የሚገኘው ልምድ ወደፊት ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ መጽሐፍ እንዲኖራት በመምሪያው ለታሰበው ዕቅድ ግብዓት እንደሚኾን ተመልክቷል፡፡
  • ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ የመጽሔቱ ኅትመት ወቅቱን ጠብቆ እንዲቀጥል መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ እናስ፣ የከሸፈው÷  የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አራማጁ ብሎግ ወይስ የመጽሔቱ አዘጋጆች ዕቅድ?!

Thursday, April 18, 2013

ሰበር ዜና – ‹‹ለፓትርያሪኩ መመሪያ ለመስጠት ተዘጋጅተዋል›› የተባሉት ኣባይ ፀሃየ ከደጅ ተመለሱ


  • በሦስት ቡድኖ የተደራጀው የጨለማው ቡድን ‹‹የኣባይ ፀሃዬን አመራር›› ያቀናጃል
  • መመሪያው÷ የልዩ ጽ/ቤት፣ ፕሮቶኮል፣ ጥበቃ ሓላፊዎችን ምደባ ይመለከታል ተብሏል
  • ‹‹ኣባይ ፀሃዬ ከስኳር ኮርፖሬሽን በተጨማሪ ጠቅላይ ቤተ ክህነትን በበላይነት እንዲመሩ ከመንግሥት ትእዛዝ ተላልፏል፡፡ የትግራይ ተወላጆች የግቢውን አመራር ሙሉ በሙሉ እንረከበዋለን፡፡ ከዚህ በኋላ ቤተ ክርስቲያን በትግራዎት እንጂ በአማራ አትመራም፡፡ ለሚኒስትሮች የሚፈለገውን ጥቅም እያቀረብን እናስፈጽመዋለን፡፡››
/ኣባይ ፀሃዬ ለፓትርያሪኩ የሚሰጡትን ‹‹አመራር›› ከእነ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ጋራ ያስተባብራሉ የተባሉት በምሥራቅ ትግራይ የደብረ ኣላማ አሲራ መቲራ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም አበምኔት አባ ገብረ መድኅን ኀይለ ጊዮርጊስ ዛሬ ጠዋት የተናገሩት/
  • ፓትርያሪኩ ‹‹አባ›› ነኝ ባዩን ከግቢው እንዲያርቁላቸው መመሪያ ሰጥተዋል፤ ተፈጻሚነት ይኖረው ይኾን?
  • መንግሥት፣ የቤተ ክርስቲያን አመራርና ምእመኑ ጉዳዩን ከምር አጢነው አቋም እንዲወስዱ ተጠይቋል፡፡
abai-tsehaye-tigraionline
አቶ ኣባይ ፀሃዬ
ከአምስተኛው ፓትርያሪክ ኅልፈተ ሕይወት በኋላ፣ የመንበረ ፓትርያሪኩን ላዕላይ መዋቅሮች በመቆጣጠርና ለተቋማዊ ለውጥ የታቀዱትን ተግባራት በማምከን÷ 1)ቡድናዊና ግለሰባዊ ጥቅሙን አስጠብቆ ለመቆየት፣ 2)ኦርቶዶክሳዊ ማንነትን በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ደብዛውን ለማጥፋት በልዩ ኹኔታ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የጨለማው ቡድን÷ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን በጎጠኝነት፣ በፖሊቲካዊ ታማኝነትና በጥቅም ስቦ እና አቅርቦ ማሰለፍ መጀመሩ ተዘገበ፡፡

በረኀብ የተዳከሙት ደቀ መዛሙርት ልመና በፖሊስ ታገደ፤ ፖሊስ ደቀ መዛሙርቱን ለመርዳት ከሚሞክሩ ምእመናን ጋራ ተወዛግቧል


  • ሓላፊዎቹ ከመምህራን የቀረቡላቸውን ሦስት ማግባቢያዎች በሙሉ ውድቅ አድርገዋል
  • ደቀ መዛሙርቱ በኮሌጁ አስተዳደር ላይ ክሥ መመሥረታቸው ተጠቁሟል
  • በአዲስ አበባ ዘመድ/መጠጊያ የሌላቸው ደቀ መዛሙርት በእጅጉ ተቸግረዋል
  • ፓትርያሪኩ ‹‹ጣልቃ አልገባም›› ማለታቸው የመምህራኑን ጥረት ጎድቷል
  • ‹‹ሃይማኖት የሌለው መምህር አያስተምረንም ባልን በረኀብ እየተቀጣን ነው›› /በደቀ መዛሙርቱ ከተለጠፉት ጥቅሶች አንዱ/
ሚያዝያ 7 ቀን 2005 ዓ.ም፤ ንጋት ላይ ነው፡፡ በአራት ኪሎ ወ.ወ.ክ.ማ በኩል ወደ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴCollege bld 01 ካቴድራል በሚያስገባው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሦስተኛ በር በርካታ ምእመናን ተሰባስበዋል፡፡ ዕለቱ የቅድስት ሥላሴ ወርኀዊ በዓል መታሰቢያ እንደመኾኑ የምእመናኑ ቁጥር ከፍተኛ ነበር፡፡ በኮሌጁ ቅጽር ውስጥ ቆመው ጥቁር ቀሚሳቸውን እንደለበሱ መሥመር ይዘውና ፊታቸውን በካቴድራሉ መውጫና መግቢያ ላይ አድርገው በዝምታ የቆሙትን ደቀ መዛሙርት ይመለከታሉ፡፡ የብዙዎቹ ደቀ መዛሙርት ገጽታ ድካምና ጉስቁልና ይነበብበታል፡፡ ከፊት ለፊታቸው ነጭ ጨርቅ ተዘርግቷል፡፡

Sunday, April 14, 2013

የቅ/ሥላሴ መን/ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት ቀሚሳቸውን አንጥፈው ሲለምኑ ዋሉ

His Grace Abune Timothy
ብፁዕ አቡነ ጢሞቲዎስ
የኮሌጁ የበላይ ሃላፊ ሊቀ ጳጳስ

  • የኮሌጁ ካፊቴሪያ ለደቀ መዛሙርቱ ምግብ እንዳያዘጋጅ በሊቀ ጳጳሱ ታዝዟል
  • ሊቀ ጳጳሱ ሁሉም መምህራን በመደበኛው የቀን መርሐ ግብር እንዳያስተምሩ ከልክለዋል
  • ሊቀ ጳጳሱ በቅ/ሲኖዶስ ውሳኔ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሥራውን እንዳይጀምር አድርገዋል
  • በሊቀ ጳጳሱ ዙሪያ የተሰለፈው የቤተ ክህነቱ የጨለማ ቡድን ፓትርያሪኩንም እያሳሳተ ነው
  • ደቀ መዛሙርቱን ለማስወጣት የተጠራው የፖሊስ ኀይል ርምጃ ለመውሰድ ፈቃደኛ አልኾነም
  • በኮሌጁ የሚዘዋወሩ ስመ ደኅንነቶች ደቀ መዛሙርቱን፣ መምህራኑንና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን እያስፈራሩ ነው
ይህ ፻ውን የሐራ ዘተዋሕዶ ዘገባ ለንባብ ያበቃንበት ጦማር ነው፡፡ ከጦማሮቹ የሚበዙት የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ተቋማዊ መገለጫ ለመኾን ስለ ደረሰው ጥቅመኝነትን የመከባከብ፣ ሙስናንና የአሠራር ብልሹነትን የማንገሥ፣ ከሙሰኞችና ጥቅመኞች ጋራ የመደራደር አስተሳሰብና ተግባር የሚመለከቱ ናቸው፡፡ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር እና የደቀ መዛሙርቱ ውዝግብ አያያዝና እየተወሳሰበ የመጣበት ኹኔታ ከዚህ የተለየ መነሻ የለውም፡፡
የኮሌጁ መምህራን እንደሚናገሩት፣ የትምህርት አስተዳደሩ እንዲሻሻልና የደቀ መዛሙርቱ አካዳሚያዊ መብቶች እንዲከበሩ የቀረቡ ጥያቄዎችን ሓላፊነት በተሞላበት መንገድ ደቀ መዛሙርቱን ከመምህራኑ ጋራ በግልጽ በማወያየት ምላሽ መስጠት ይቻላል፡፡ ይህም ካልኾነ የመማር ማስተማሩን ጤናማነት/ሰላማዊነት ለመጠበቅ ተቃውሞ የቀረበባቸውና ከደቀ መዛሙርቱ ጋራ መስማማት ያልቻሉ መምህራን ከሓላፊነታቸው ገለል እንዲሉ ማድረግ ነው፡፡
ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ
(የኮሌጁ የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ)
እየኾነ ያለው ግን ላለፉት 14 ዓመታት በኮሌጁ የበላይ ሓላፊነት ከቆዩ ሊቀ ጳጳስ የሚጠበቅ አይደለም፡፡ ደቀ መዛሙርቱ በቅ/ሲኖዶስ የተቋቋመው ኮሚቴ የማጣራት ሥራውን ጨርሶ ጥያቄያቸው ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ የተቃውሟቸው ሁለቱ ሓላፊዎችና መምህራን ወደ ክፍል ገብተው እንዳያስተምሩ በመከላከላቸው እልክ የተጋቡት ሊቀ ጳጳሱ ‹‹ያቋረጣችኹትን ትምህርት በአግባቡ አልጀመራችኹም›› በሚል የቀኑ መደበኛ መርሐ ግብር ከመጋቢት 30 ቀን ጀምሮ የተዘጋ መኾኑን የኮሌጁን ክብ ማኅተም ይዞ መጋቢት 30 ቀን 2005 ዓ.ም ጠዋት በወጣ ማስታወቂያ አሳስበዋል፤ በቁጥር 181 ያህል የሚኾኑት የቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርትም ንብረት አስረክበው በአስቸኳይ ከኮሌጁ እንዲወጡ አዝዘዋል፡፡

የኮሌጁ የቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርት ኮሌጁን እንዲለቁ ታዘዙ


  • መንሥኤው ‹‹ትምህርት በአግባቡ አልጀመራችኹም›› የሚል ነው
  • ‹‹ማስታወቂያው ለብቀላና እስር ሰበብ መፈለጊያ ነው›› /ደቀ መዛሙርቱ/
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር የቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርት ከዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ የኮሌጁን ንብረት እያስረከቡ ኮሌጁን እንዲለቁ አሳሰበ፡፡ ኮሌጁ ማሳሰቢያውን በዛሬው ዕለት በቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርቱ ላይ ያወጣው ‹‹ያቋረጣችኹትን ትምህርት አግባብነት ባለው መንገድ አልጀመራችኹም›› በሚል ነው፡፡
Holy Trinity College Academic Programs
የኮሌጁ የትምህርት መርሐ ግብር

Wednesday, April 10, 2013

መታሰር ያልሰለቸው ቀበሮ መነኩሴ




(አንድ አድርገን ሚያዚያ 1 2005 ዓ.ም)፡- በደብረ ብርሐን ከተማ አባ በረከት የሚባል ሰው በገዳማት እና በአድባራት ላይ ብዙ ጉዳት እንዳደረሰ ገልጸን ከወራት በፊት መጻፈችን ይታወሳል፡፡ አባ በረከት መጀመሪያ ጎንደር ይኖር የነበረ ከዚያም ደንጨት ዮሐንስ ገዳም ሲያገለግል የነበረ ሰው ሲሆን ከመንዝ አካባቢ እንደመጣ የጀርባ ታሪኩ ይናገራል ፡፡ የካቲት 2004 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሐን ከተማ በደብረ ማዕዶት ቅድስት አርሴማ ገዳም በመግባት ሲያገለግል እንደነበር መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡ በዚህ ገዳም የሚመጡ በርካታ እህቶችን በማታለል ዝሙት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ ስለተደረሰበት ይህን ድርጊቱን እንዲያቆም ከወንድሞች ምክር ተሰጥቶትም ነበር፡፡  በቤተመቅደስ ውስጥ ድፍረትና ክህደት የተሞላበት የአማኙን እምነት የሚቀንስና ለትልቅ ድፍረት የሚያደፋፍር እንቅስቃሴዎች ሲያደርግ እንደነበር በጊዜው በቦታው የነበሩ የአይን እማኞች  ገልጸዋል ፤ ገዳም ሲገባ አብራው የመጣች ወለተ መስቀል የምትባል  መነኩሴ የነበረች ሲሆን ፤ በገዳሙ በነበረው ቆይታ ለገዳማውያን አገልጋይ ካህናት ‹‹ከአንድ እናት ማህጸን የወጣን እህቴ ነች›› እያለ ሲያወራ እና ሲያስወራም ነበር ፡፡(ሴትየዋ በአሁኑ ሰዓት ከአባ በረከት የልጅ እናት ሆናለች)፡፡ ይህ ሰው አውደ ምህረት አግኝቶ የለሰለሰ የኦርቶዶክስ የሚመስል ውስጡ እሾህ የሆነ ትምህርት ባያስተምርም እንኳን ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፤ ስለ ቅዱሳን መላእክት ፤ ስለ ጻድቃን ሰማዕታት ያማልዳሉ? አያማልዱም? የሚል አርእስት በማንሳት በርካታ እህቶች ፤ ወንድሞችና የአብት ተማሪዎች ላይ ውስጥ ውስጡን ምንፍቅና ሲዘራ እንደነበር ከእሱ ጋር ከተወያዩ ጥቂት ምዕመና አማካኝነት ለማወቅ ተችሏል ፡፡

Friday, April 5, 2013

የነገረ መለኰት ምሩቃን ማኅበር አባላት የተሐድሶ ኑፋቄን እንዲዋጉ ፓትርያሪኩ አሳሰቡ


  • ማኅበሩ በሦስት አህጉረ ስብከት ቅርንጫፍ ቢሮዎችን ከፍቷል
  • የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ሥራ አስፈጻሚን በዳግም ምርጫ አጠናክሯል
  • መናፍቁ አሰግድ ሣህሉን ለማስመረጥ የተደረገው ሙከራ ተቀባይነት አላገኘም
  • ሁለት የፀረ – ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ሰባክያንና ዘማርያን ጥምረት አባላት በሥራ አስፈጻሚነት ተካተዋል
  • ማኅበሩ ሕጋዊ ዕውቅናና ተቀባይነት ካላቸው የቤተ ክርስቲያናችን አካላት ጋራ ሁሉ ተባብሮ ለመሥራት ያለውን ዝግጁነት ዳግም አረጋግጧል
Theology Association Logoበቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እና በቅዱስ ፍሬምናጦስ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ምሩቃንን በአባልነት በመያዝ የተመሠረተ ነው፤ ዋና ዓላማው÷ የወንጌል ትምህርት ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች ሐዋርያዊ አገልግሎት መስጠት፣ የቤተ ክርስቲያናችን ዶግማ፣ ሥርዐት፣ ትውፊት እና ንዋያተ ቅድሳት በአግባቡ እንዲጠበቁ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ ነው – የነገረ መለኰት ምሩቃን ማኅበር፡፡
ማኅበሩ ዓላማውን የሚተገብርባቸውየስብከተ ወንጌል፣ የትምህርት፣ የኅትመትና ሥርጭት፣ የሕግ፣ የልማት፣ የመረጃና መዛግብት፣ የሒሳብና ንብረት አስተዳደር እንዲሁም የቁጥጥር ክፍሎችን አዋቅሯል፤ እኒህን ተግባራት የሚያስፈጽሙ 12 የሥራ አስፈጻሚና አፈጻጸሙን በበላይነት የሚመሩ 12 የሥራ አመራር አባላት እንዳሉትም ማኅበሩ ያሰራጫቸው መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

Tuesday, April 2, 2013

የኮሌጁ አስተዳደር የቀን መደበኛ መርሐ ግብር ላልተወሰነ ጊዜ መዘጋቱን አስታወቀ


  • ማስታወቂያው የተለጠፈው በመርሐ ግብሩ አስተባባሪ ዘላለም ረድኤት ነው
  • ደቀ መዛሙርቱ በተቃውሟቸው ለመቀጠል በመስማማት ትምህርት ጀምረዋል
  • ‹‹ሲያስወጡን እንተናነቃለን፤ ኮሌጁን ቅ/ሲኖዶስ እንጂ ዘላለም አይዘጋውም›› /ደቀ መዛሙርቱ
  • የኮሌጁ የበላይ ሓላፊ ‹‹[ለደቀ መዛሙርቱ] እንኳን ምሳ ራት አልሰጥም›› እያሉ ነው
ሙስናንና የአሠራር ብልሹነትን በመቃወም ከሁለት ሳምንት በላይ በተቃውሞ የሰነበቱት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የቀን መደበኛ መርሐ ግብር ደቀ መዛሙርት በትላንትናው ዕለት ረፋድና ከሰዓት በኋላ በክፍል በመገኘት ትምህርት ጀምረዋል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ትምህርት በማቋረጥና በካፊቴሪያው ከመመገብ በመከልከል በኮሌጁ እየከፋ የመጣው ሙስናና የአሠራር ብልሹነት እንዲስተካከል፣ ለዚህም ተጠያቂ ናቸው ያሏቸው ሁለት ሓላፊዎች ከቦታቸው እንዲነሡ ያቀረቡትን ጥያቄ እየተማሩም ለመቀጠል በመወሰን ነው ትምህርታቸውን ለመጀመር የተስማሙት፡፡