የአብባቢያን መድረክ

ውድ አንባቢያን፣
በዚህ ገጽ ላይ ስለ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ወቅቱ የተለያዩ ርዕሶች ላይ ሊቃውንትን አማክረን፣ ከተለያዩ የቤተ ክርስቲያናችንን መጻሕፍት አገላብጠን መልሶች ይሆናሉ  ብለን የምናስበውን ሁሉ ለአንባቢያን እናቀርባለን። በዚህ መድረክ የሚስተናገዱ ጥያቄዎች በተቻለ መጠን ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ብቻ እንዲሆን አስቀድመን ለማስገንዘብ እንወዳለን፣ በተቻለ መጠን የሰው ስሞችን ከማንሳት ተቆጥበት በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ እንዲሆን አስቀድመን ለማስገንዘብ እንወዳለን።
ጥያቄያችሁን በዚህ ወይም በኢሜል አድራሻችን
kurtegnalejoch@gmail.com ልታደርሱን ትችላላችሁ።

ቸር ይግጠመን
የመላው ዓለም የተዋሕዶ ቤተሰብ

5 comments:

  1. የተዋሕዶ ቤተሰቦች እንደምን ከርማችኃል ሰላማችሁ ይብዛ
    አንድ አስተያየት ለመስጠት ነው፣ ስለ ዌብ ሳይታችሁ በእውነት ጥሩ ነገር እያደረጋችሁ ነው በርቱበት ነገር ግን እንደው ለመጠቆም ያህል እዚህ ላይ በብዛት ስለ አባ ፋኑኤል ብዙ ነገሮችን አስነብባችሁናል ጥያቄዬ ምንድነው፥ እርሳቸው ይሄንን ዌብ ሳይት ያዩታል ወይ? ወይስ በምን ይታወቃል እንደሚያዩት ምክንያቱም በቅርቡ ካስነበባችሁን የምክር አገልግሎት በሚለው ውስጥ የጠቆማችኃቸው ምክሮች ነበሩ በሙሉ በቀጥታ እርሳቸውን የሚመለከቱ ናቸው እና ምናልባት ከምክሮቹ ሁሉንም ባይሆን አንዳንዶቹን ሊጠቀሙበት ካቻሉ ምናለበት በሆነ መልኩ በቀጥታ ለሳቸው የሚደርስበትን መንገድ ብትፈልጉ ብዬ ለመጠቆም ያህል ነው እና ምናልባት ከተቻለ እንደዛ ብታደርጉ ለማለት ነው።
    እግዚአብሔር ስራችሁን በጎደለው ይሙላላችሁ
    በርቱ ከጎናችሁ ነን

    ReplyDelete
  2. † በኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን ውስጥ መታረም አለበት ብዬ የማምንበት አክብሮታዊ የስም አጠራር ስህተት አለ ፡፡
    የተለያዩ ሰዋችን የሀይማኖት አባቶችን የመንግስት ባለስልጣናትን መሪዋችን ክብር የማይገባቸው ሰዋችን ሁሉ ወዘተ አንቱ እያልን በአክብሮት እንጠራለን እነሱንና ይህን አለም የፈጠረውን አምላክ ግን ከነሱ አሳንሰን አንተ ማርያምንም አንቼ ስላሴዋችን አንቱ ቅድሳንን አንቱ እየሱስን አንተ ወዘተ ብለን እንጠራለን የተዘባረቀ አጠራር ሆነ ወይ የአማርኛው መዝገበ ቃላት መስተካከል አለበት ወይም አንድ ማስተካክያ ግዜው ሳይረፍድ መደረግ አለበት እጅግ አሳፋሪና የአምላክን ክብር የሚያሳንስ የሰዋችን ስምና ክብር ከፍ የሚያደርግ በሰው የተሰራ ስህተት ነው ፡፡ መጸሀፍ ቅድስ በመጀመርያ ወደ ኢትዬጵያ ቋንቋ ሲተሮጎም ነው ስህተት ተሰራ ብዬ የማምነው ይህም ለምሳሌ አንቱ የሚለው ቃል በአማርኛ ሲኖር በእስራኤል ቋንቋ ግን የለም ስለዚህ ተርጔሚዋቹ ለምን በቀጥታ ቃሉን ከኛ ባህልና ቋንቋ አንጻር እንዳልተሮጎሙት አላውቅም በአሁኑ ትውልድ ያለን ምእመናንና የሀይማኖት አባቶች ግን ልናርመው ልናስተካከለው ልንለውጠው ይገባል ከሱ በላይ ማንንም ስሙን ማንንነቱን አክብረን ልንጠራ አይገባም ሰዋችን በአክብሮት ልንጠራቸው ከስፈለገ በመአረግ ስማቸው እና አቶ ፣ወይዘሮ ፣ጋሼ ፣እትዬ ፣አባ ፣ወዘተ ማለት እንችላለን ስለዚህ አንቱ የሚለው አጠራር ለሰው ተገቢ አይደለም ከአማርኛ መዝገበ ቃላት ውስጥ መውጣት አለበት በጣም ትልቅ ስሀተት ነው ፡፡ †††

    ReplyDelete
  3. † በኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን ውስጥ መታረም አለበት ብዬ የማምንበት አክብሮታዊ የስም አጠራር ስህተት አለ ፡፡
    የተለያዩ ሰዋችን የሀይማኖት አባቶችን የመንግስት ባለስልጣናትን መሪዋችን ክብር የማይገባቸው ሰዋችን ሁሉ ወዘተ አንቱ እያልን በአክብሮት እንጠራለን እነሱንና ይህን አለም የፈጠረውን አምላክ ግን ከነሱ አሳንሰን አንተ ማርያምንም አንቼ ስላሴዋችን አንቱ ቅድሳንን አንቱ እየሱስን አንተ ወዘተ ብለን እንጠራለን የተዘባረቀ አጠራር ሆነ ወይ የአማርኛው መዝገበ ቃላት መስተካከል አለበት ወይም አንድ ማስተካክያ ግዜው ሳይረፍድ መደረግ አለበት እጅግ አሳፋሪና የአምላክን ክብር የሚያሳንስ የሰዋችን ስምና ክብር ከፍ የሚያደርግ በሰው የተሰራ ስህተት ነው ፡፡ መጸሀፍ ቅድስ በመጀመርያ ወደ ኢትዬጵያ ቋንቋ ሲተሮጎም ነው ስህተት ተሰራ ብዬ የማምነው ይህም ለምሳሌ አንቱ የሚለው ቃል በአማርኛ ሲኖር በእስራኤል ቋንቋ ግን የለም ስለዚህ ተርጔሚዋቹ ለምን በቀጥታ ቃሉን ከኛ ባህልና ቋንቋ አንጻር እንዳልተሮጎሙት አላውቅም በአሁኑ ትውልድ ያለን ምእመናንና የሀይማኖት አባቶች ግን ልናርመው ልናስተካከለው ልንለውጠው ይገባል ከሱ በላይ ማንንም ስሙን ማንንነቱን አክብረን ልንጠራ አይገባም ሰዋችን በአክብሮት ልንጠራቸው ከስፈለገ በመአረግ ስማቸው እና አቶ ፣ወይዘሮ ፣ጋሼ ፣እትዬ ፣አባ ፣ወዘተ ማለት እንችላለን ስለዚህ አንቱ የሚለው አጠራር ለሰው ተገቢ አይደለም ከአማርኛ መዝገበ ቃላት ውስጥ መውጣት አለበት በጣም ትልቅ ስሀተት ነው ፡፡ †††

    ReplyDelete
    Replies
    1. ውድ “Senahoy F”
      ከቅንነት በመነጨ ስሜት በጻፍከዉ አስተያየት ላይ "በኢትዮጵያ በተ ክርስቱያን ዉስጥ መታረም ያለበት የአነጋገር ባህል አለ" በማለት ያነሳኸዉ ሃሳብ መሰረታዊ ስህተት ያለበት ይመስለኛል፡፡ ለምን ቢባል በእናት ቤተ ክርስቲያናችን ዉስጥ እዉቀት ቢበዛ እንጂ አይጎድልምና ቤተ ክርስቲያን ለእያንዳንዱ ለምታከናዉነዉ ስራ ምክንያት እና በእዉቀት ላይ የተመሰረተ ማብራሪያ አላት፡፡ ቤተ ክርስቲያን ስንዱ እመቤት የምትባለዉም ለዚሁ ነዉ፡፡
      ለምሳሌ አንተ ያነሳሃቸዉ ነጥብ በእኔ ግንዛቤና ትምህርት እንኳን ብናይ፡-
      ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ እግዚአብሔርን አንተ ብላ የምታስተምርበት ምክንያት አንድም እግዚአብሔር ራሱ የዘመን/የጊዜ ባለቤት እንጂ ለእርሱ ዘመን የማይቆጠርለት ዘላለማዊ (በባህሪዉ እርግና የለሌበት) ስለሆነ ሁለትም እግዚአብሔር የሰዉ ልጆች ሁሉ አባት ስለሆነና ልጅ ደግሞ አባቱን በልጅነት አንደበት አንተ ማለቱ ለአባት ደስታ እንጂ የሚያስከፋ ስላልሆነ ነዉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ምድራዊያን ሰዎችን አንቱ ማለቱ በእድሜ እርግናቸዉ አክብሮት ስለሚገባ ነዉ ባይ ነኝ፡፡ ስለሆነም ባነሳኸዉ ሃሳብ ሰፊ ማብራሪያ ለማግኘት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሊቃዉንት መጠየቁ በእጅጉ ተመራጭ ነዉ፡፡

      Delete
  4. milashu betam tiru new gin, andim,huletim tebelo yekerebew bebetekirstian agelaletse tikekil ayemeselegnim egiziabiher yistilign

    ReplyDelete