Wednesday, July 25, 2012

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የፓትርያርክነት ማዕርግ የተቀዳጀችበት የነጻነት በዓል - በዓለ ሢመተ ፓትርያርክ - አከባበር የመንፈሳዊ ውርደትና የምዝበራ መንገድ ኾኗል


(ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 16/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 23/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ በሙስና፣ ብኵንነት፣ ኑፋቄ እና ዐምባገነናዊ አሠራር የነቀዘው የአባ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና 20 ዓመት በዓለ ሢመት ዛሬ ምሽት ለሁለተኛ ጊዜ በሼራተን አዲስ ይከበራል። የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት እና ራእይ ለትውልድ /Vision for Generation/ የተባለው አካል የጥቅም ትስስር የፈጠሩበት የሼራተኑ በዓለ ሢመት ዝግጅት በቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት ይኹን በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት አይታወቅም።


የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የአብያተ እምነት መሪዎች፣ አምባሳደሮችና ታዋቂ ግለሰቦችን ጨምሮ እስከ 1500 እንግዶች ይታደሙበታል በተባለው ይኸው ዝግጅት ከጥቅም ትስስር ባሻገር÷ በግንቦቱ ቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ እና ውሳኔዎች ክፉኛ የተጋለጠውን የአባ ጳውሎስን ማንነት ለማደስ የታሰበበት ‹የሕዝብ ግንኙነት› ሥራ እንደኾነ ተጠቁሟል። በበዓለ ሢመቱ አከባበር የቀደሙት ፓትርያርኮች መልካም ስምና ዝና በተለያዩ ስልቶች እየተንኳሰሰ በምትኩ በሙስና፣ ኑፋቄ እና ዐምባገነናዊ አሠራር የተበሳበሰው የአባ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና የሥራ ክንውን ብቻ “በወደር የለሽነት” /በእንግሊዝኛው የበዓለ ሢመት ኅትመት ላይ እንደተገለጸው - ‘unparalleled efforts/ እንደ ግለሰብ መሞገሱ ብዙዎችን አሳዝኗል።

Tuesday, July 17, 2012

የዲሲው አባ መላኩ/ አባ ፋኑኤል - እዚያው በጸበልዎ ! ከሲያትል ዋሽንግተን


ሰሞኑን ወደ ሲያትል ዋሽንግተን ለመሄድ በዝግጅት ላይ የሚገኙት አባ ፋኑኤል ገና የመምጣታቸው ዜና ከመሰማቱ ጀምሮ በርካታ
የአካባቢው ምዕመናን ተቃውሞ እያሰሙ ነው። በሲያትል ዋሽንግተን ከተማ የሚገኙ ቤተክርስቲያናት በተለይ የቅዱስ አማኑኤል
ቀንደኛው የተሃድሶ ጋሻ ጃግሬ ከነባራኪው
የቅዱስ ሚካኤል፣ የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያናት ምዕመናን ድምጻቸው የሁሉም አይምጡብን፣ አይድረሱብን እርሶ ይዘው የሚመጡት ከፋፋይ እና በታኝ ሃሳብዎን "እዛው በጸበልዎ" እያሉ ይገኛሉ፤ ነገር ግን በተቃራኒው የሕዝበ ክርስቲያኑን እሮሮ እና ቁጣ ችላ በማለት ስልጣን እና ሹመት ወይም ጥቅም ፈላጊ እና ለነፍሳቸው ሳይሆን ለሥጋቸው ባደሩ የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎች ጋባዥነት እና ጋሻ ጃግሬነት ወደ ሲያትል ሕዝብ ለማስገባት የሚሞክሩ ካህናት ሥራቸውን ቀጥለውበት በተለይ የቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን አስተዳደር የሕዝበ ክርስቲያኑን ጥያቄ እና አቤቱታ ወደ ጎን በመተው በማናለብኝነት ከፋፋዩን ከነ ጋሻ ጃግሬያቸው ኃይለጊዮርጊስ ጋር ለመስተናገድ ሽር ጉድ እያሉ ይገኛሉ። በዚህም ምክንያት ነው ከዚሁ ከሲያትል አካባቢ የሚገኙ የቤተክርስቲያኒቱ ቁርጠኛ ልጆች ከነዚህ የተሃድሶ አቀናባሪዎች ሕዝቡን ለመታደግ መልዕክቶችን በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ፣ "የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመቱባችሁ ተኩላዎች ተጠበቁ" በማለት ድምጻቸውን እያሰሙ ያሉት። የዝግጅት ክፍላችን መልክቱ ደርሶናል እና ለአንባቢያን አቅርበነዋል። መልካም ንባብ . . .


"ጅብ የማያውቁት ሀገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ ይላል"
                                                                                                               ሰኔ 5 ቀን 2004 ዓ/ም
ከላይ የተጠቀሰው ሀገራዊ አባባል በእንስሳት በላነቱና አጥፊነቱ የታወቀው ጅብ የማይታወቅበት ሀገር ሂዶ የማይገባውን ክብር ወይም የክብር ቦታ ለማግኘት መሞከሩን ያሳያል :: የጅብ ማስመሰል ለመብላት ነው:: ለማጥፋት ለማረድ ነው:: ከሰሞኑም ይህ ነገር በአባ መላኩ /አቡነ ፋኑኤል / ሲያትል ሊደገም ይመስላል :: ጨዋ መስለው አባት መስለው : ሀገር አቅኚ መስለው : ህዝብ ሰብሳቢ መስለው : ሕገ ቤ/ክን አክባሪና አስከባሪ መስለው ሲያትል ቅዱስ አማኑኤልና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ሊመጡ እየተዘጋጁ እንደሆነ ነው የሚሰማው ::

ሰዎች ምን ይላሉ?



፳ የአምባገነንነት፣ የሙስና፣ የዘረኝነት፣ የዝቅጠትና የአድርባይነት ዓመታት
የመጀመሪያ አስተያየት ሰጪ
''አይቴ ለነውር ብሔረ ሙላዱ 
በውስተ ኩሉ ብሔር እስመ ከመ ነግድ ይሄሉ 
ጠይቆተ ዝኒ ነገር ከመ ይትገሀድ ለኩሉ 
ኃጥእ ይሣለቅ ላዕለ ጻድቅ ከመ ዘንጹሕ ወሠናይ ባህሉ፥
እስመ እንዘ ሠርዌ በውስተ ዐይኑ  
እምነ ቢጹ ብሩህ አውጽኦተ ሐሠር ያስተዴሉ።
አይሁድኒ ሐዋርያተ በጽእሎቶሙ ጸዐሉ፥
ጊጉያነ ወአብዳነ ወሐሳውያነ እንዘ ይብሉ፥
ወብእሴ ጻድቀ ዘሀለዎሙ ይስቅሉ፥
እንዘ ውጹኣን እምነ ጽድቅ በጽድቀ ርእሶሙ ይትሌዐሉ። '' 
መወድስ ቅኔ ዘአለቃ ንጉሤ።
አባ ጳውሎስና ተከታይ የሥጋና የግብር ልጆቻቸው ያፈረሱትን እኮ ነው ገነባን የሚሉት። ቀኖና ቤተ ክርስቲያንንአፍርሰው በጦር መሳርያ ሃይል ቀምተው የተቀመጡበትን መንበር ማፍረሻ እንጅ መገምቢያ እንዳላደረጉትየሚታወቀውን ነገር ለራሳቸው ካልሆነ በስተቀር ለማንም ሊሸጡት የማችሉት የረከሰ ሸቀጥ መሆኑን መረዳትየሚያስችል አዕምሮ እንደሌላቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠንቅቆ ያውቃል። ተዋቸው የራሳቸውን ጽድቅ ለራሳቸውእያስተጋቡ ለጊዜው ይቀጥሉ።


ሁለተኛ አስተያየት ሰጪ
በአባ ጳውሎስ ዘመነ ሥልጣን ቤተክህነት የደረሰባትን አስተዳደራዊና መንፈሳዊ ውድቀት ለሚረዳ ሰውእውነትም ኮሜዲ ነው:: የሚገርመው ውጤትን በምን መስፈርት ቢለኩ ነው እንዲህ ለማለት የቻሉት:: መቼስየቤተክርስቲያንን አተዳደራዊ እድገትና የምእመናንን በሐይማኖት መጠንከር ሳይሆን ፓትርያርኩንና ግብረአበሮቻቸው በግል ያካበቷቸውን ንብረቶች ቆጥረው ከሆነ ከልብ ያሳዝናል:: ምክንያቱም ፓትርያርኩ ሱሾሙየተሰጣቸው ኃላፊነት ይህ አይደለምና:: በጣም እንዳላዝን የሚያደርገኝ ነገር ቢሮር እንዲህ ብለው የጻፉ ሰዎችትናንትና ሐውልት ያቆሙላቸው ግለሰቦች ስለሚሆኑና ሐውልት ከማቆም የበለጠ ቀልድ ስለሌለ ነው::ለማንኛውም 20 ዓመታት እናት ቤተክርስቲያን ተጎድታ ቆይታለችና ለቀጣይ 20ዓመታት ተመሳሳይ ፈተናእንዳያጋጥማት የሁል ጊዜ ምኞቴ ነው:: እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን::

ሶስተኛ አስተያየት ሰጪ (  ሐመረ ኖህ )
እኛ ዝም እስካልን ድረስ በተዋህዶ እምነታችንንና በኛም ላይ ገና ብዙ ግፍ ይሰራል  የኑፋቄ የውርደትየዘረኝነት የመከፋፈል የአምባገነንነት የሙስና የዝቅጠት የአድርባይነት የፈተና ሁሉ ፈተና የቅንጦተኞችዘመን አሳልፈናል አሁንም ዝም ካልን ይቀጥላል ሌላው ሁሉ ይቅርና ማለትም ዘርዝረን ስለማንጨርሰውየለበሱት ልብስ ለ፳ኛ ሲመታቸው ይሆን እጅግ በጣም ውድ ነው ስንት በገዳም የሚጋኙ በቀን አንዴመመገብ ላልቻሉ ለታረዙ መነኮሳትና የአብነት ተማሪዎች ለዓመት ቀለብ ይሆን ነበር እኔስ ከአሕዛብበእምነታቸው ሳይሆን በትግላቸው ቀናሁ ከሞተ አንበሳ ሕይወት ያላት ትሻላለች
ከአኖነመስ
20 አመታት የቤተክርስቲያን የፈተናና የወደኋላ ጉዞ ዘመናት!
ሰው ግን እስከመቼ ነው ለሆዱ የሚኖረው? እውነት ከልባቸው ነው ግን "20 ውጤታማ አመታት" ብለው የጻፋት?
ከደጀ ሰላም የተወሰደ

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

Monday, July 16, 2012

በጀርመን ስለ ዋልድባ ተጠርቶ የነበረ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይካሄድ በፓትርያርኩ ታገደ


ስኬቱ በምን ይሆን?? በማፍረስ እና በመከፋፈል??
(ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 9/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 16/ 2012/ READ NEWS IN PDF)፦ በዋልድባ ገዳም ክልል ውስጥ መንግሥት  እሠራዋለሁ ያለውን የስኳር ፋብሪካ ግንባታ በመቃወም በጀርመን ያሉ ማኅበረ ካህናት እና ማኅበረ ምእመናን በፍራንክፈርት ከተማ ሐሙስ ሐምሌ 12/2004 ዓ.ም (ጁላይ 19/2012) በኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ተገኝተው የተቃውሞ ድምፃቸውን እንዲያሰሙ በጀርመን የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ኃላፊ ሊቀ ካህናት ዶ/ር መርዓዊ ተበጀ  አስተላለፈውት የነበረው የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አግባብነት እንደሌለው እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ወደ ሰልፉ እንዲወጣ የማድረጉ ጥረት እንዲገታ ቅዱስ ፓትርያርኩ  ጥብቅ መመሪያ አስተላለፉ።
ሊቀ ካህናት መርዓዊ
ከአምባሳደር ፍሥሓ ጋር

 በቅዱስነታቸው በተፈረውና ሊቀ ካህናት ዶ/ር መርዓዊ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራታቸውን የሚያወሳው ይኸው ደብዳቤ “ሁሎችም የዚሁ ሰላማዊ ሠልፍ ተባባሪዎች እንዲሆኑ በልዩ ልዩ መንገድ እያስገደዱ መሆንዎን ከደረሰን ሪፖርት መረዳት ችለናል፤ ይህም ኢ-ቀኖናዊ የአሠራር ሒደት ዲሞክራሲያዊ አሠራር እንዳልሆነ ልንገልጽልዎ እንወዳለን በማለት ሌሎቹ ካህናት በነፃ ያሰቡበት ሳይሆን በሊቀ ካህናቱ አስገዳጅነት እየሆነ ያለ እንቅስቃሴ መሆኑን ፍራንክፈርት ከሚገኘው የቆንስላ ጀነራል ጽ/ቤቱ የደረሳቸው መረጃ እንዳለ አመልክቷል። 

Friday, July 13, 2012

የላስ ቬጋስ ኪዳነ ምሕረት ወቅዱስ ሚካኤል ቤተ ከርስቲያን ከአቡነ ፋኑኤል ጋር እንደማይሠራ በድጋሚ አረጋገጠ



  • የደብሩ ማኅበረ ካህናት የፈረሙበትን ደብዳቤ ተመልከቱ

(ደጀ ሰላም፤ ሰኔ 14/2004 ዓ.ም፤ ጁን 21/ 2012/ READ THISARTICLE IN PDF)፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ በምዕራብ አሜሪካ የካሊፎርኒያ ሀ/ስብከት ሥር የሚገኘው የላስ ቬጋስ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ወቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን “ከብፁዕ አቡነ ፋኔኡል ጋር እንደማንሠራ እና የሸቱትንም ሾመት የማንቀበል መሆኑን” እንገልጻለን ባለበት መግለጫው አቡነ ፋኑኤል “ከዚህ በፊት ለአህጉረ ስብከቱ ተመድበው አባታዊ መመሪያ እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ይሰጡ ከነበሩት አባቶች በተለየ መልኩ በመጓዝ ካህናት እና ምዕመናንንን በማሳዘን ለመናፍቃን በር የሚከፍት የቤተ ክርስቲያን መዋቅር እና ሥርዓት ባልጠበቀ እና ባልተከተለ መንገድ መመሪያ በመስጠት እና በተግባርም በመፈፀም የግል ጥቅምን ብቻ በሚያስጠብቅ አካሄደ በመጓዛቸው በሚሠጡት የተሣሣተ እና ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የወጣ አመራር ጋር አብሮ መጓዝ ተገቢ ባለመሆኑ ከዚህ በፊት ያለንን አቋም/ አቋማችንን እንገልጻለን” ብሏል።

ጠቅ/ቤተ ክህነት “ጉባኤ አርድእት” ነን ባዮች በመንበረ ፓትርያርኩ እንዳይሰበሰቡ አገደ


·         እገዳው የተላለፈው መንግሥት ለአባ ጳውሎስ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ ነው ተብሏል።
·         በአባ ጳውሎስ ቀጥተኛ ይኹንታ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርኩ ለቀናት በኅቡእ ሲሰበሰብ የቆየው ቡድኑ÷ ከፊል መሥራች አባላቱ ከሸሹትና የስብሰባ እገዳ ከተጣለበት በኋላ÷ ለቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት የ‹ዕወቀኝ› ጥያቄ ማቅረቡ ተነግሯል።
·   የቅ/ሲኖዶስ እና የጠቅ/ቤ/ክህነት ጽ/ቤቶች÷ ቤተ ክርስቲያን “ጉባኤ አርድእት” የተሰኘውን ኅቡእ ቡድን እንደማታውቀው ገልጸዋል።
·     የኅቡእ ቡድኑ አስተባባሪ ፕሮቴስታንታዊው ኀይለ ጊዮርጊስ ጥላሁን በአባ ጳውሎስ ትእዛዝ የያዘውን የጠ/ቤ/ክህነቱን መኪና እንዲያስረክብ ተደርጓል።
·   አባ ጳውሎስ የእምነት ንጽሕናቸውን በቅ/ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ያላረጋገጡትንና ከቡድኑ ቀንደኛ አስተባባሪዎች አንዱ የኾኑትን አባ ሰረቀን በመንፈሳዊ ዘርፍ ም/ሥ/አስኪያጅነት ለመሾም ማሰባቸው ተሰምቷል።
·    “ለቤተ ክርስቲያን ደኅንነት ሲባል የቡድኑን ኅቡእ እንቅስቃሴ በጥብቅ እየተከታተልነው ነው” /የጠ/ቤ/ክ መመሪያ ሓላፊዎች/።
·     “ከጉባኤው አስተባባሪዎች አብዛኞቹ በሚሠሩባቸው ቦታዎች ተቀባይነት ያጡ ግለሰቦች ናቸው” /የቋሚ ሲኖዶስ ምንጮች/።
 (ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 4/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 11/ 2012/ READ IN PDF)፦ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ራሱን “ጉባኤ አርድእት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ” በሚል መጠሪያ ሰይሞ ከቤተ ክርስቲያን ማእከላዊ አስተዳደር ዕውቅናና ፈቃድ ውጭ ከፓትርያርኩ ባገኘው ቀጥተኛ ይኹንታ የአባ ጳውሎስን ዐምባገነንት ለማጠናከር፣ መንፈሳውያን ማኅበራትን ለማፈራረስ፣ የግል እና የቡድን ጥቅሞቹን ለማስጠበቅ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርኩ መሽጎ ሲዶልት የቆየው ቡድን በየትኛውም የመንበረ ፓትርያርኩ አዳራሾች እና ቢሮዎች ለመሰብሰብ እንደማይፈቀድለት አስታወቀ፡፡