Tuesday, March 26, 2013

የኮሌጁ መምህራን ደቀ መዛሙርቱን ትምህርት ለማስጀመር እየጣሩ ነው

Dr Aba Hailemariam Melese
ዶ/ር አባ ኀይለ ማርያም መለሰ
(የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ምክትል ዋና ዲን)

  • መምህራኑም ከፍተኛ የአስተዳደር በደል እንደሚደርስባቸው ተናገሩ
  • ፓትርያሪኩ÷ ተጠያቂዎች በጥናት ተለይተው ርምጃ እንዲወሰድ መመሪያ ሰጥተዋል
  • የመብት ማስከበር እንቅስቃሴው የመናፍቃን መጠቀሚያ እንዳይኾን ጥንቃቄ ያስፈልጋል
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህራን÷ ደቀ መዛሙርቱ ትምህርት በማቋረጥና ከምግብ በመከልከል የጀመሩትን አካዳሚያዊ መብትን የማስከበር የተቃውሞ እንቀስቃሴ አቁመው ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የማግባባት ጥረት መጀመራቸው ተገለጸ፡፡
ደቀ መዛሙርቱ ተቃውሞ ያነሡባቸው የኮሌጁ ሁለት ሓላፊዎችና የጠየቋቸው አካዳሚያዊ መብቶች ጉዳይ በቋሚ ቅ/ሲኖዶሱ መታየቱንና በጥልቀት እንዲጠና በፓትርያሪኩ መመሪያ የተሰጠበት መኾኑን ዋስትና በማድረግ ነው መምህራኑ ደቀ መዛሙርቱን የማግባባት ጥረት መጀመራቸው የተመለከተው፡፡

ደቀ መዛሙርቱ ተቃውሟቸው በረኀብ አድማ አጠናከሩ


  • ፓትርያሪኩ ደቀ መዛሙርቱን ለማነጋገር ፈቃደኛ አይደሉም
  • የረኀብ አድማው የፍትሕ ጥያቄያችን እስኪመለስ ይቀጥላል
  • የመንግሥት አካላት ነን የሚሉ ግለሰቦች ደቀ መዛሙርቱን እያስፈራሩ ነው
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት ትላንት ማምሻውን ጀምሮ በረኀብ አድማ ላይ ናቸው፡፡ የረኀብ አድማው ተማሪውንና ሠራተኛውን ፍትሕ ያሳጡት፣ እንደ ግል ቤታቸው በመቁጠር የጥቅም መተሳሰሪያና የንግድ ማእከል አድርገዋል የተባሉት ሓላፊዎች ከቦታቸው እስኪወገዱ ድረስ እንደሚቀጥል ደቀ መዛሙርቱ ገልጸዋል፡፡
ደቀ መዛሙርቱ ምግብ ባለመብላት ተቃውሟቸውን ለማጠናከር የወሰኑት÷ ያቋረጡትን ትምህርት ለመጀመር ፈቃደኛ ካልኾኑ ብርድ ልብስ፣ አንሶላና መታወቂያ አስረክበው ግቢውን እንዲለቁ የኮሌጁ አስተዳደር ያወጣውን ማስጠንቀቂያ ተከትሎ÷ በትላንትናው ዕለት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩን በአካል አግኝተው ለማነጋገር ያደረጉት ሙከራ ባለመሳካቱ ነው፡፡

የቅ/ሥላሴ መ/ኮሌጅ አስተዳደርና ደቀ መዛሙርት ውዝግብ እንደቀጠለ ነው

His Grace Abune Timothy
ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሓላፊ

  • ተማሪዎች÷ አካዳሚክ ምክትል ዲኑ እና የቀን መርሐ ግብር አስተባባሪው ከሓላፊነታቸው ካልተነሡ ያቋረጡትን ትምህርት እንደማይቀጥሉ አስታውቀዋል
  • አስተዳደሩ÷ ተማሪዎች ትምህርት ካልጀመሩ ኮሌጁን ለቀው እንዲወጡ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፤ ለውዝግቡ መባባስ የተማሪዎች መማክርትን ተጠያቂ አድርጓል
  • የቀኑ የመደበኛ ዲግሪ መርሐ ግብር ትምህርት ከተቋረጠ ዐሥረኛ ቀኑን አስቆጥሯል
  • ደቀ መዛሙርቱ አካዳሚያዊና አስተዳደራዊ ሓላፊነቶችን ደራርበው የያዙ መምህራን በሚታይባቸው የማስተማር ዝግጅት ማነስ ተማርረዋል
  • የቀን መርሐ ግብር አስተባባሪው÷ መ/ር ዘላለም ረድኤት÷ በሸውከኛነት (ነገረ ሠሪነት) ኰሌጁን ሰላም በመንሳት ተከሠዋል
  • ለ14 ዓመታት ያህል በኮሌጁ የበላይ ሓላፊነት የቆዩት ሊቀ ጳጳስ ‹‹በቃዎት›› ተብለዋል
  • ውዝግቡ ከመ/ፓ/ጠ/ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሓላፊዎች አቅም በላይ ኾኗል
  • ‹‹ትምህርት የምንጀምረው የዛሬም የሁልጊዜም ጥያቄዎቻችን የነበሩት ችግሮች ተፈተው ተገቢ ምላሽ ስናገኝ ብቻ ነው›› /ደቀ መዛሙርቱ/
  • ‹‹ችግራችሁን እናስተካክላለን፤ ጥያቄዎቻችሁን እንመልሳለን፤ ነገር ግን ወደ ክፍል ገብታችኹ ትምህርታችሁ ቀጥሉ›› /የኮሌጁ አስተዳደር/
በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር እና በመደበኛው የዲግሪ መርሐ ግብር ደቀ መዛሙርት መካከል ዳግመኛ ያገረሸው ውዝግብ ዛሬ፣ መጋቢት 12 ቀን 2005 ዓ.ም. ዐሥረኛ ቀኑን አስቆጥሯል፡፡ ለውዝግቡ መቀስቀስ መነሻ የኾነው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰበት የመጣው የካፊቴሪያው የምግብ አቅርቦት መበላሸት ነው፡፡ ‹‹ጥርስ ላይ ከሚንቀጫቀጨው እንጀራ ጀምሮ ጠቅላላ ብልሽት የሚታየበት የካፊቴሪያው የምግብ አቅርቦት÷ በኮሌጁ ጥቂት የአስተዳደርና የአካዳሚ ሓላፊዎች መካከል ለገነገነው ሙስናና የጥቅም ትስስር ጉልሕ ማሳያ ነው፤›› ይላሉ ደቀ መዛሙርቱ፡፡
ጥያቄያቸው ከምግብ አቅርቦት በላይ የኰሌጁን መሠረታዊ አስተዳደራዊ ችግሮች በተለይም በትምህርት አመራሩ ረገድ የሚታየውን ውስንነት እንደሚያካትት ደቀ መዛሙርቱ ይናገራሉ፡፡ እንደ ደቀ መዛሙርቱ ገለጻ÷ በአሁኑ ወቅት በሓላፊነት ላይ የሚገኘው የኮሌጁ አስተዳደር፣ አንጋፋውን የቤተ ክርስቲያናችን ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ለመምራት ብቃቱም ዝግጁቱም የለውም፡፡
ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮዋን በትውፊታዊ መንገድ ለትውልድ ጠብቃ ካቆየችባቸው የአብነት ት/ቤቶች በተጨማሪ በዘመናዊ አቀራረብ የነገረ መለኰት ትምህርት የሚሰጥባቸው ሦስት መንፈሳዊ ኮሌጆችን አቋቁማለች፡፡ ከሦስቱ ኮሌጆች ቀደምት የኾነው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከተመሠረተ 55 ዓመት አስቆጥሯል፡፡ የተቋሙ ርእይ÷ ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና ትውፊት ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ፤ የክርስቶስን ወንጌል ያልሰሙ እንዲሰሙ፣ የሰሙ በእምነታቸው ጸንተው የሃይማኖት ፍሬ እንዲያፍሩ በመሥራት እግዚአብሔርን የሚፈራ፣ ወንድሙን የሚወድ፣ ለሀገርና ለወገን ዕድገት የሚያስብ ለዚህም የቆመ ትውልድ ተፈጥሮ ማየት›› መኾኑን የኮሌጁ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡

የቅ/ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደርና ደቀ መዛሙርት ውዝግብ ተካሯል


  • ተማሪዎች÷ አካዳሚክ ምክትል ዲኑ እና የቀን መርሐ ግብር አስተባባሪው ከሓላፊነታቸው ካልተነሡ ያቋረጡትን ትምህርት እንደማይቀጥሉ አስታውቀዋል
  • አስተዳደሩ÷ ተማሪዎች ትምህርት ካልጀመሩ ኮሌጁን ለቀው እንዲወጡ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፤ ለውዝግቡ መባባስ የተማሪዎች መማክርትን ተጠያቂ አድርጓል
  • የመደበኛ ዲግሪ መርሐ ግብር ትምህርት ከተቋረጠ ዘጠነኛ ቀኑን አስቆጥሯል
  • ደቀ መዛሙርቱ አካዳሚያዊና አስተዳደራዊ ሓላፊነቶችን ደራርበው የያዙ መምህራን በሚታይባቸው የማስተማር ዝግጅት ማነስ ተማርረዋል
  • የቀን መርሐ ግብር አስተባባሪው÷ መ/ር ዘላለም ረድኤት÷ በሸውከኛነት (ነገረ ሠሪነት) ኰሌጁን ሰላም በመንሳት ተከሠዋል
  • ለ14 ዓመታት ያህል በኮሌጁ የበላይ ሓላፊነት የቆዩት ሊቀ ጳጳስ ‹‹በቃዎት›› ተብለዋል
  • ውዝግቡ ከመ/ፓ/ጠ/ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሓላፊዎች አቅም በላይ ኾኗል
  • ‹‹ትምህርት የምንጀምረው የዛሬም የሁልጊዜም ጥያቄዎቻችን የነበሩት ችግሮች ተፈተው ተገቢ ምላሽ ስናገኝ ብቻ ነው›› /ደቀ መዛሙርቱ/
  • ‹‹ችግራችሁን እናስተካክላለን፤ ጥያቄዎቻችሁን እንመልሳለን፤ ነገር ግን ወደ ክፍል ገብታችኹ ትምህርታችሁ ቀጥሉ›› /የኮሌጁ አስተዳደር/
Source: http://haratewahido.wordpress.com/

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

Monday, March 11, 2013

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ የዐቢይ ጾም መልእክት

His Holiness Abune Mathias
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለማስጠበቅ በየጠረፉ የቆማችኹ፤
በሕማም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችኹ፤
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ኾናችኁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤
እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የ2005 ዓ.ም መዋዕለ ጾም በሰላም አደረሳችኹ፡፡

‹‹እብለክሙ በመንፈስ ሑሩ ወፍትወተ ሥጋክሙ ኢትግብሩ››
‹‹በመንፈስ ተመላለሱ እንጂ የሥጋችኹን ምኞት ከቶ አትፈጽሙ እላችኋለኹ››
የተወደዳችኹ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን!

Thursday, March 7, 2013

ፓትርያሪኩ ‹‹ቅዱስ ሲኖዶስ በራሱ መተማመን አለበት›› አሉ

Image
  • ቋሚ ሲኖዶሱን ለማገዝ የተቋቋመው ‹‹ሥራ አስፈጻሚ›› የሥራ ጊዜ አበቃ
  • አዲስ የቋሚ ሲኖዶ አባላት ተመርጠዋል
  • ፓትርያሪኩ ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ሠራተኞች ጋራ ትውውቅ አደረጉ
  • ‹‹ቅድስና፣ ንጽሕና፣ ታማኝነት በተለይም ደግሞ ሃይማኖትን ይዞ መገኘት ያስፈልጋል›› /ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ ለሠራተኞች ከሰጡት ማሳሰቢያ/
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከማንኛውም የሥልጣን መዋቅር ሁሉ የበላይ አካልና የመጨረሻው ከፍተኛ ሥልጣን ባለቤት በመኾን ሕጎችን፣ ልዩ ልዩ ደንቦችንና መመሪያዎችን የሚያወጣው ቅዱስ ሲኖዶስ ‹‹በራሱ መተማመን አለበት››ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያሪክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አሳሰቡ፡፡ ቅዱስነታቸው ማሳሰቢያውን የሰጡት ስድስተኛ ፓትርያሪክ በመኾን ሥርዐተ ሢመታቸው በተፈጸመበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡
ፓትርያሪክ (ርእሰ አበው) ኾነው የተመረጡበትን ሓላፊነት የቅ/ሲኖዶሱን አባላት በመያዝ በጋራ እንደሚወጡት ያላቸውን ተስፋ የገለጹት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ቅዱስ ሲኖዶሱ እንደ አንድ ልብ አሳቢ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾኖ በሥምረት ከሠራ ችግር ይኖራል ብለው እንደማያምኑ ተናግረዋል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እንደገለጹት፣  በመንፈስ ቅዱስ የሚመራውና የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ የኾነው ቅ/ሲኖዶስ በራሱ መተማመንና ቤተ ክርስቲያኒቱን የመጠበቅ ግዴታ አለበት፡፡

አስመራጭ ኮሚቴው አጠቃላይ የሥራ ሪፖርቱን ለቅ/ሲኖዶሱ አቀረበ

Asmerach Com Meetings
  • የምርጫው ሂደት በይፋ ተዘጋ
  • ‹‹ቅ/ሲኖዶሱ ያወጣውን ሕገ ደንብ መፈጸምና ማስፈጸም የማይችል ከኾነ ቤተ ክርስቲያን ለከፋ ፈተና ትጋለጣለች›› /የምእመን ተወካይ/
  • ‹‹ኮሚቴው ባቀረበው ሪፖርት መሠረት የተደረገው ሁሉ ትክክለኛ ነው›› /ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ/
ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያሪክ በመኾን በትላንትናው ዕለት ሥርዐተ ሢመት የተፈጸመላቸው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ÷ ቅዱስ ሲኖዶሱን በርእሰ መንበርነት የመሩበትን የመጀመሪያ ስብሰባ በዛሬው ዕለት በማካሄድ አገልግሎታቸውን ጀምረዋል፡፡

Monday, March 4, 2013

ፓትርያሪኩ የዕርቀ ሰላም ጥረቱ እንደሚቀጥል አሳሰቡ

The 6th Patriarch Enthronmentየብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያሪክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሥርዐተ ሢመት ዛሬ፣ የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል፡፡ ለበዓለ ሢመቱ አፈጻጸም በወጣው መርሐ ግብር መሠረት በካቴድራሉ ተገኝተው የቅዱስነታቸውን ሥርዐተ ሢመትና ሥርዐተ ጸሎት ያከናወኑት በሹመት ቀደምት የኾኑ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት÷ ዐቃቤ መንበሩ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ፣ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል እና ብፁዕ አቡነ ማትያስ ዘካናዳ ናቸው፤ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩም ቃለ መሐላ ፈጽመዋል፤ ከዐቃቤ መንበረ ፓትርያሪኩ ጋራ ጸሎተ ቅዳሴውን (ቅዳሴ ሐዋርያት) መርተዋል፡፡

Saturday, March 2, 2013

የስድስተኛው ፓትርያሪክ በዓለ ሢመት ዝግጅት


  • ፓትርያሪኩ ቃለ መሐላ ይፈጽማሉ
  • የኮፕቱ ፖፕ የማይገኙት በደብዳቤ አጻጻፍ ስሕተት ምክንያት ነው
  • ዐራተኛውን ፓትርያሪክና አብረዋቸው የሚገኙ አባቶችን የተመለከቱ ዝርዝር ሰነዶች የያዘ ኅትመት በበዓለ ሢመቱ ላይ ይሰራጫል
የስድስተኛው ፓትርያሪክ ሥርዐተ ሢመትና ሥርዐተ ጸሎት ነገ የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም ይፈጸማል፡፡ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በሚፈጸመው የ፮ው ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ በዓለ ሢመት አከባበር÷ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ ለመላው ካህናትና ምእመናን ርእሰ አበው መኾናቸውን (የአባትነት ሓላፊነታቸውን)፣ መሠረተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅና ለማስጠበቅ ያለባቸውን ሓላፊነት የተመለከተ ቃለ መሐላ እንደሚፈጽሙ ይጠበቃል፡፡Patriarch - Elect - Abune Matyas