Friday, February 21, 2014

አባ ሰረቀ ብርሃን ‹‹በታቦት ዝርፊያ›› ክስ ብጹዕ አቡነ ማቲያስ ዘንድ ቀርበው ነበር

  • ‹‹ለዚህ መረጃ አቡነ ማቲያስ ቀድሞ የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ በአሁን ሰዓት 6ተኛው ፓትርያርክ፣ አቡነ ሣሙኤልና አቡነ ኢሳይያስ ህያው ምስክሮች ናቸውና›› መረጃውን የላኩልን የሎሳንጀለስ ምዕመን
  • ‹‹አባ›› ሰረቀ ታቦት ሰርቀው ተይዘዋል፡፡ ከገዛናቸው 12 ጸናጽል ያስረከቡን ስድስቱን ሲሆን  12 መቁዋሚያም 6ቱን ይዘውብን ሄደዋል፡፡
  • ‹‹አቡነ አረጋዊም የሚባል ቤተክርስቲያን የለም፡፡›› ‹‹አባ›› ሰረቀ ብርሃን በአንድ ወቅት የሰበኩት ስብከት
  •  ‹‹በወቅቱ የአሜሪካ ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት አቡነ ማቲያስ ማኅተም ወስደው በነጭ ወረቀት ላይ እያተሙየኔን ፊርማ እያስቀመጡ ሰዎችን ብር እየተቀበሉ ከኢትዮጵያ ወደዚህ ሲያመጡተደርሶባቸው..........››
    በወቅቱ አባ ሰረቀ ከጓደኛቸው ጋር ሲሰሩት የነበረ ሥራ የምዕመኑ ቃል
ከአንድ የሎስ አንጀለስ ምዕመን የደረሰን መልዕክት 


(አንድ አድርገን የካቲት 11 2006 ዓ.ም)፡- በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት ሊካሄድ የታሰበው የአብነት መምህራን የምክክር ጉባኤ በአባ ሰረቀ ብርሃን አማካኝነት ከቅዱስ ፓትርያርኩ በተሰጠ መመሪያ መሠረት ሳይካሄድ መቅረቱ ይታወቃል፡፡ የአባ ሰረቀን  የቀድሞ ተግባር በርካታ ምዕመን ቢያውቀውም  ብጹዕ አቡነ ማቲያስ የሚያውቁትን እና በሎስአንጀለስ ምዕመናን ላይ ያደረሱትን በደል የደረሰንን መልዕክት ለእናንተው ለማድረስ ወደድን፡፡ ‹አባ› ሰረቀን ከአመታት በፊት በታቦት ሌብነት ብጹዕ አቡነ ማቲያስ ዘንድ ቀርበውም እንደነበርም መረጃው ያመለክታል፡፡ ስለዚህ ቅዱስነታቸው አሁን እየሰሩ የሚገኙት ቀድሞ  ለሰሚ ጆሮ የሚከብድ ዝርፊያ በቤተ ክርስቲያን ላይ ካደረገ ሰው ጋር መሆኑን ነው፡፡ እስኪ በወቅቱ የነበሩ ህያው ምስክሮች የላኩልንን መረጃ ይህን ይመስላል፡፡

Saturday, February 15, 2014

የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባን መቃወም የአክራሪነትና ጽንፈኝነት ዝንባሌ ነው ተባለ

  • ሐዋሳው ስብሰባ የተጠበቀው የምዝገባ ዐዋጁ ረቂቅ ለውይይት ሳይቀርብ ቀረ
  • የዐዋጁ ጉዳይ በቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ደረጃ ሊመከርበትና አቋም ሊያዝበት ይገባል
  • የሰላም ዕሴት ግንባታ ሰነዱ በአወዛጋቢ ይዘቱ ለተጨማሪ ግምገማ እንዲዘገይ ተደረገ
Dr. Shiferaw Hawassa
ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም
የሃይማኖት ወይም እምነት ተቋማትን ለመመዝገብና የዕድሳት አገልግሎት ለመስጠት በሚል መዘጋጀቱ የተገለጸውን የዐዋጅ ረቂቅና አሠራሩን በመቃወም የሚካሔድ እንቅስቃሴ የአክራሪነትና ጽንፈኝነት ዝንባሌ መገለጫ መኾኑን የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም ተናገሩ፡፡
ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት፣ በሐዋሳ ለሁለት ቀናት በተካሔደውና የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ‹‹ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ›› ጋራ በመተባበር ባዘጋጀው ዐውደ ትምህርት ላይ ‹‹አክራሪነትና ጽንፈኝነት ከሕገ መንግሥታችን ጋራ ያለው የማይታረቅ መሠረታዊ ቅራኔና መፍትሔው›› በሚል ርእስ ባቀረቡት ጽሑፍ ነው፡፡
ይኸው የሚኒስትሩ ጽሑፍ ‹‹አክራሪነትና ጽንፈኝነት ማብራሪያና መፍትሔዎቻቸው››ተብሎ በስላይድ ታግዞ የቀረበ ሲኾን መንግሥትና የሃይማኖት ተቋማት በሰላምና ልማት ጉዳይ ጭምር መደራረስ የለባቸውም በሚል የሚካሔድ እንቅስቃሴ ስለመኖሩ ይገልጻል፡፡
ይኸው እንቅስቃሴም የአክራሪነትና ጽንፈኝነት ዝንባሌ እንደኾነ የሚኒስትሩ ጽሑፍ ያመለክታል፡፡ ‹‹የአክራሪነትና ጽንፈኝነት ዝንባሌዎች የጋራ ጉዳዮች›› በሚል የጽሑፉ ንኡስ ርእስ ሥር የተካተተው ይኸው የሚኒስትሩ ምልከታ፣ በስም ለይቶ ያነሣው አካል ባይኖርም ‹‹የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባ ጉዳይ እና የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ›› የሚሉ ሁለት ጉዳዮችን በማውሳት ‹‹ለአክራሪነትና ጽንፈኝነት ዝንባሌው›› በማሳያነት ማቅረቡ ተዘግቧል፡፡

ከመመሪያ ወደ ዐዋጅ ከፍ የተደረገው ‹‹የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባና የዕድሳት አገልግሎት›› ረቂቅ በሐዋሳ ለውይይት ይቀርባል

  • የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከ‹‹ኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ›› ጽ/ቤት ጋራ በመተባበር ያዘጋጀውና ከጥር ፴ – የካቲት ፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. በሐዋሳ – ሌዊ ሪዞርት በሚካሔደው ውይይት ላይ፣ በፓትርያርኩ የሚመራ ኻያ ያህል የቤተ ክርስቲያናችን ልኡክ ይሳተፋል፤ ልኡኩ በዛሬው ዕለት ከቋሚ ቅዱስ ሲኖዶሱ የሥራ መመሪያ ይቀበላል፡፡
  • የዐዋጁን ረቂቅ ከውይይቱ አስቀድሞ ለመመልከትና የቤተ ክርስቲያናችንን አስተያየትና አቋም ለመወሰን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የቀረበው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ አላገኘም፡፡
  • ‹‹የሃይማኖት ወይም እምነት ተቋማትን ለመመዝገብና የዕድሳት አገልግሎት ለመስጠት›› በሚል በፓርላማው ጸድቆ እንደሚወጣ የተመለከተው ዐዋጅ÷ የእምነት ተቋማትና ከእምነት ጋራ የተሳሰሩ መንግሥታዊ ያልኾኑ አደረጃጀቶች‹‹ፀረ ሕገ መንግሥታዊ ተግባር ላይ እንዳይሳተፉ ለመከላከልና ተጋላጭ ከሚያደርጉ አሠራሮች እንዲቆጠቡ ለመደገፍ እንዲሁም ሕገ ወጥ የፋይናንስ ዝውውር አካል እንዳይኾኑ ለመጠበቅ ያስችላል›› ተብሏል፡፡
  • የ‹‹ኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ›› አባል ከኾኑ ሰባት የእምነት ተቋማት በተውጣጡ ምሁራን እንደተዘጋጀና በአገር አቀፍ ደረጃ በየአብያተ እምነቱ ተግባር ላይ እንደሚውል የተገለጸው፣ የሃይማኖት ተቋማት የሰላም ዕሴት ማሠልጠኛ መመሪያ ረቂቅም የመጨረሻ ይዘት ተገምግሞ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል፡፡
  • ከፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ጋራ በቅርበት በሚሠራው ‹‹የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ›› የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ፣ የቀበሌና ንኡስ ቀበሌ መዋቅሮች በቋሚነት የሚመደቡ ተወካዮቻችንና ጽ/ቤቱ በሚያዘጋጃቸው የምክክር መድረኮች፣ ዐውደ ጥናቶችና የኅትመት ውጤቶች ላይ የሚሳተፉ ልኡኰቻችን፣ የአስተሳሰብና ሞያዊ ብቃት፣ የውክልና አግባብነትና የተሳትፎ ፋይዳ ከሽርሽር ጉዞ፣ ከፖሊቲካ ቅኝትና አድርባይነት ይልቅ የቤተ ክርስቲያናችንን መብቶችና ጥቅሞች በማስጠበቅ ለአገራዊ የጋራ ጉዳይ ለመሥራት የሚያስችል ስለመኾኑ በጥንቃቄና በጥልቀት መገምገም እንደሚገባው እየተጠየቀ ነው፡፡

ጥንታዊው የደብረ ብሥራት አቡነ ዜና ማርቆስ ገዳም ተፈታ

  • ገዳሙ ጨርሶ ሳይጠፋ ጉዳያቸው በቅዱስ ሲኖዶሱ እንዲታይ መናንያኑ ጠይቀዋል
  • በገዳሙ ህልውና ላይ የተጋረጠው አደጋ በሀ/ስብከቱ የተንሰራፋው ችግር የከፋ መገለጫ ነው
(አዲስ አድማስ፤ ጥር ፳፬ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀ/ስብከት ሞረትና ጅሩ ወረዳ የሚገኘው የመካከለኛው መቶ ክፍለ ዘመን የደብረ ብሥራት አቡነ ዜና ማርቆስ አንድነት ገዳም ተፈትቶ፣ መናንያኑና መነኰሳቱ መበተናቸውን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ገለጹ፡፡
ጥንታዊውን ገዳም ለመፈታት፣ ማኅበረ መነኰሳቱንም ለመበተን ያበቃቸው፣ በአካባቢ ተወላጅነት የገዳሙን መሬት በተለያዩ ጊዜያት ተቆጣጥረው ለግላቸው ይጠቀሙ ከነበሩ ግለሰቦች ጋር ተፈጥሮ የቆየውና በተለያዩ ምክንያቶች እየተካረረ የመጣው አለመግባባትመኾኑን ምንጮቹ ተናግረዋል፡፡
በኅዳር ወር 2006 ዓ.ም መጀመሪያ ላይ ገዳሙን ለቀው የወጡት በቁጥር ከ50 – 80 የሚገመቱ መናንያኑ ከተለያዩ አህጉረ ስብከትና ክልሎች የተሰባሰቡና በጸሎት ተወስነው የራስ አገዝ ልማት እያለሙ በአንድነት የኖሩ መነኰሳትና መነኰሳዪያት ሲኾኑ በሀገረ ስብከቱ ውሳኔ ከአስተዳዳሪነት የተነሡትን አበምኔቱን መ/ር አባ ተክለ ብርሃን ሰሎሞንን ጨምሮ ከፊሎቹ በአሁኑ ወቅት በደነባ በኣታ ለማርያም ገዳምተጠልለው እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ፣ የወረዳው መንግሥታዊ አስተዳደር፣ ከእነዋሪና ደነባ ከተሞች የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ገዳማውያኑንና ግለሰቦቹን በተለያየ ጊዜ በማገናኘት ለአለመግባባቱ የመፍትሔ ሐሳብ ሲሰጡና ውሳኔ ሲያሳልፉ እንደቆዩ ያስታወሱት መነኰሳቱ፤ ‹‹ተሰዳጅና መጤ›› ከሚል በቀር ግለሰቦቹ በገዳሙ አበምኔትና በመናንያኑ ላይ የሚያቀርቧቸው ክሦች መሠረተ ቢስ መኾናቸው ተረጋግጧል ብለዋል፡፡

Tuesday, February 4, 2014

የሐመረኖህ ኪዳነ ምህረት በላስቬጋስ የተደበቀና የደረስኩበት የውስጥ ችግር

 አንድ የዘወትር አንባቢያችን ከላስቬጋስ አካባቢ በተለይ በሐመረ ኖሕ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ በመሆን እያገለገሉ ስላሉት መነኮስ እና ሥራቸው መጠነኛ የሆነ መረጃዎችን ልኮልናል። ምዕመን የማወቅ መብት አለው ብለን ስለምናምን ይኛም የመጣልንን መረጃ እንደወረደ ለእናንተው አቅርበነዋልና ተከታተሉ። መልካም ምንባብ እንዲሆንላችሁ ከወዲሁ እንመኛለን።
መላከ ሰላም አባ ገብረ ኪዳን ሽፈራው
በጥቂት ምዕመናንና በአንድ ቄስ የዛሬ ስምንት አመት የተቋቋመው የሐመረኖህ ቤተክርስቲያን በመናፈሻ ፣በላይብረሪ ‘በሰርቢያንቸርች ፍላሚንጎና ጆንስ፣ቶሮፓይንስና ትሮፒካና በሚገኘው የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ፣በመጨረሻም አሁን ባለበት ቤተክርስቲያን በብዙ ድካምና ትጋት ሲገለገል ቆይቷል አራት ወራት ያህል በካህን እጦት ከዲሲ፣ከሎሳንጀለስና ከሳንዲያጎ ፣ከዳላስ ቴክሳስ ካህናት እየተመላለሱ ሲያገለግሉ ቆይተዋል እለዚህ ቤተክርስቲያኑን በየሳምንቱ እየተመላለሱ ሲያገለግሉ የነበሩት ባለውለታ ካህናት ቀሲስ ከፈለኝ፣ አባ ሀይለስላሴ፣አባ ገብረ ማርያም፣አባ ገብረ መድህን ፣ቀሲስ ብርሀኑ፣ቀሲስ ሰብስቤ በመሀል ስማቸውን የረሳኋቸው የመጡ ካህናት ይኖራሉ እነዚህ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ በባእል ቀን ሲያገለግሉን ነበር ከአራት ወር በኋላ በአቡነ ማትያስ ሽዋሚነጽ ዲ/ሳሙኤል ደጀኔ ቅስና ተቀብለው ለአራት አመታት ያህል ብቻቸውን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ አንድምቀን አገልግሎቱ ሳይቋረጥ ከአራት አመት በኋላ ዲ/ዮሐንስን ቅስና ከአቡነ ማርቆስ ተሸሙ ቀሲስ ሳሙኤልን እያገዙ ብዙም ሳይቆይ አባ ገብረኪዳን መጡ አንድ ሆነው በፍቅር በሰላም ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ አዲስ የሰበካ ጉባኤ ከተመረጠ ወዲህ ሰለም እየደፈረሰ መጣ በጉባኤው ውሰት አባ ገብረ ኪዳንን ጨምሮ ሦስት የማህበረ ቅዱሳን አባላት አሉበት እንደምንሰማው ውሳኔዎች በግሩፕ መወሰን ጀመሩ በሞቀበት ፈላ የሆነው ዲ ምስክርም ወደሞቀበት ሲያጫፍር ቆየ ይህ በእንዲህ እንዳለ አባ ገብረ ኪዳን ለአራት ወር ወደሀገርቤት ሲሄዱ