Friday, August 16, 2013

‹‹ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን አሐቲ ቅድስት ጉባኤ እንተ ሐዋርያት ርትዕት በእግዚአብሔር››


 ‹‹ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን አሐቲ ቅድስት ጉባኤ እንተሐዋርያት ርትዕት በእግዚአብሔር›› ብለን የምንታዘዘው በመላውዓለም ላለችው በእምነትና በጥምቀት አንድ ሆነን  በቅዱስ ሥጋውናበክቡር ደሙ ተዋሕደን አንድ የክርስቶስ አካል በሚያደርገን ምሥጢርለሚሳተፉት ሁሉ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የአንዱ አካላችን ብልቶችየሆኑት የግብጽ ክርስቲያኖችና በዚያ ያለችው ቤተ ክርስቲያን በታላቅመከራ መሆኗን እናስብ ፡፡ ከቀደመው ጊዜ ጀምሮ በሶርያ ያሉወንድሞቻችን መከራውን እንደተቀበሉ እናውቃለን፤ አሁንምበመቀበል ላይ ናቸው፡፡ ስለእነዚህ ሁሉ በእውነት ልንጸልይ ግዴታችንመሆኑን በቀኖናው የታዘዘ ቢሆንም በጸሎተ ቅዳሴያችንም ጊዜቢታወጅልንም ኅሊናችን እነርሱን ሁሉ እያሰበ መጸለይ ይገባል፡፡እንገፋለን እንጂ አንወድቅምክርስቲያን እንደ ሚስማር ሲመቱትየሚጠብቅ ነው-እግዚአብሔር አምላክ በሶሪያ ፤ በግብጽ ፤ በኢራቅ  እና በሌሎች የዓለም አካባቢዎች በፅንፈኞችአማካኝነት እየተሰየፉ እና እየተቃጠሉ በሰማዕትነት በክብር ላረፉ ክርስቲያን ወገኖቻችን መንግሥቱንያውርስልን!

Wednesday, August 14, 2013

“በ22 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ያስተዳደረ ሙስሊም የለም” የሙስሊሞች የተቃውሞ ድምጽ


(አንድ አድርገን ነሀሴ 5 2005 ዓ.ም)፡- ባሳለፍነው ዕለተ ሀሙስ በሙስሊሞች የበዓል እለት አዲስ አበባ በብዙ ቦታዎች በተቃውሞ ስትናጥ መዋሏን የተለያዩ መገናኛ ብዙሀን ኢቲቪን ሳይቀር ተቀባብለው መዘገባቸው ይታወሳል፡፡ በተነሳው ግጭት ፖሊስ ብዙዎችን ማረፊያ ቤት ማጎሩም ይታወቃል፡፡ ባሳለፍናቸው 3 ቀናት ፖሊስ ጣቢያዎች የምሳ እና የእራት ሰሀን በያዙ ሰዎች ተከበው ውለዋል፡፡ በወቅቱ የታሰበበትና የተጠና ሰላማዊ ሰልፍ መሆኑን ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ ፤ የባነሮቹ ተመሳሳይነት ፤ የመፈክሮቹ ይዘት ፤ ተቃውሞ የተነሳበት ሰአትና ቦታ ሰልፉ ታሰበበት መሆኑን ያመለክል ፡፡

አዲስ አበባ በለውጥ አመራር ያብባል ገና

  • በምደባ ቅር የተሰኙ ሓላፊዎች በየሆቴሉና ሬስቶራንቱ የዐመፅ ምክክር ይዘዋል
  • ‹‹የቋሚ ሲኖዶሱ ምደባ በአተገባበር በደላሎች ተጠልፏል›› የሚል ቅሬታ አላቸው
  • የረዳት ሊቀ ጳጳሱና ጽ/ቤታቸው ድርሻ የቋሚ ሲኖዶሱን ምደባ ማስፈጸም ብቻ ነው
  • በዘላቂው የሀ/ስብከ መዋቅር ስፍራ የሚኖራቸው በጊዜያዊ ምደባቸው ብቃት ያሳዩ ሓላፊዎችና ሠራተኞች መኾናቸው ተገልጧል
የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ በሚያደርገው ቅድመ ዝግጅት ለዘረጋው የሽግግር ጊዜ መዋቅር የሓላፊዎችና ሠራተኞች ምደባ አካሂዷል፡፡ እስከ ጥቅምት ወር መጨረሻ ፳፻፮ ዓ.ም ድረስ ለሦስት ወራት በሚቆየው የሽግግር መዋቅር 133 የሀ/ስብከቱ ሐላፊዎችና ሠራተኞች በምደባው ታቅፈዋል፡፡ ከእኒህም ውስጥ 57 በሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት፣ 76 ያህሉ ደግሞ ለአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ቅርበት ባላቸው ሰባት የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች የተመደቡ ናቸው፡፡
ምደባውን ያካሄደው በቋሚ ሲኖዶስ የተሠየመውና በመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አባ ኀይለ ማርያም መለሰ የሚመራ መዳቢ ኀይለ ግብር ነው፡፡ ኀይለ ግብሩ ሰብሳቢውን ጨምሮ አምስት አባላት ያሉት ሲኾን እነርሱም የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ አስተዳደር መምሪያ፣ የሒሳብና በጀት መምሪያ፣ ጠቅላላ አገልግሎት ሓላፊዎችንና የቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት ተወካይን በአባልነት የያዘ ነው፡፡ መረጣና ምደባው (selection and placement) የተሠራበት መነሻ በቋሚ ሲኖዶሱ የጸደቀው የሀ/ስብከቱ አስተዳደራዊ መዋቅርና ከእያንዳንዱ የሥራ መደብ ጋራ ተነጻጽሮ የቀረበው ዝርዝር የመመዘኛ መስፈርት ነው፡፡ በመስፈርቱ መሠረት የትምህርት ዝግጅት እና የሥራ ልምድ ዋነኛ መመዘኛ መደረጉ የተገለጸ ሲኾን ‹‹የብሔር ተዋፅኦ››ም ከግንዛቤ ገብቷል ተብሏል፡፡