Tuesday, November 18, 2025

በምስራቅ አርሲ አዋሳኙ በምዕራብ ሐረርጌ የሰባት ልጆች እናት መገደላቸውን ስምዓ ተዋሕዶ ዘገበ፡፡

የኦርቶዶክሳውያኑ ደም መፍሰስ በአስቸኳይ ይቁም!!
ምዕራብ ሐረርጌ ዶባ ወረዳ ኢፋ ጀነቴ ቀበሌ ላይ ታግተው ከአንድ ቤተሰብ 4 ሰው አባት አቶ ደበበ እና እናት ወ/ሮ ገነት (የሰባት ልጆች እናት)፣ ወንድ ልጃቻው እና የልጃቸው ባል አግተው ከወሰደዋቸው በኃላ ብዙ ድብደባና እንግልት ደርሶባቸዋል::  ከእነዚህ ኦርቶዶክሳውያን ውስጥም በድብደባው ምክንያት ሕይወታቸው ያለፈው የሰባት ልጆች እናት የሆኑት ወ/ሮ ገነት  ስርዓተ ቀብራቸውም  በዶባ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል። 

ኦርቶዶክሳውያኑን ሲያሰቃዩ የነበሩ አጋቾች በድካም እንቅልፍ ላይ መሆናቸውን እንደአጋጣሚ  በመጠቀም ከታጋቾች መካከል የነበሩት አቶ አበበ አምልጠው በመውጣትና ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው  በአካባቢው የሚገኙ ፖሊሶች ባደረጉት ጥረት አስከሬን ለማንሳትና  እና የቀሩ ታጋቾችን ለማዳን መቻሉን ከአካባቢው የደረሰን ጥቆማ ያመለክታል፡፡  ይሁንና አሁንም በእገታ ውስጥ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የ3.5 ሚሊዮን ብር ካሳ ተጠይቆባቸዋል ።

የኦርቶዶክሳውያን ሞት ይቁም!!!

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

No comments:

Post a Comment