Saturday, November 29, 2025

ቆመኽ አንገትኽን ተቆረጥ

የአርሲ ሰማዕታት ደም ይጮኻል 

ዛሬ ባለንበት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መከራ የቀደመ የአስተሳሰባችን ውጤት ነው። በሃገሩ ሽማግሌ አለ፣
መንግሥት አለ ብሎ ያምናል። በዚያም ሲተዳደር የኖረ ነው። በተለይ በሃይማሞት ረገድ ብዙም የከፋ ነገር አይቶ አያውቅም። በብልጽግና ዘመን መከራ አይነቱን ከመቁጠር በዝቶ መስማት ሰልችቶናል። ሰምተን እንዳልሰማን ለመኾን እንሞክራለን። 

አኹን አስተሳሰባችን ሙሉ በሙሉ ነው መቀየር ያለበት። ነጠላ ለብሶ ከበሮ የሚያሽከረክረው እንዲኽ አይቀጥልም። ልፍስፍስ ወጣት ማምረት መቆም አለበት። አራሽ ቀዳሽ ተኳሽ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰ መኾን። የቀደመ አባቶቹን መምሰል ግድ ይላል። 
“አትግደል” ተብሏል እያለ ቆሞ አንገቱን እንደ ሸንበቆ የሚሰጥ ጅል ትውልድ አፍርተናል። ይኽ ነው እያስገደለን ያለው። 

አውሮጳ የሚኖሩ ኢትዮጵያውን፣ ኢትዮጵያ ውስጥ «ይፈፀማል» ያሉትን ግድያ በሠልፍ አወገዙ

ኢትዮጵያውያን በአውሮጳ
ጀርመን እና በአጎራባች የአውሮጳ ሃገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ  ውስጥ በተለይ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ክርስቲያኖች ላይ ይፈፀማል ያሉትን ግድያ፣ ግፍና ማፈናቀል ዛሬ በርሊን-ጀርመን ውስጥ ባደረጉት የአደባባይ ሠልፍ አወገዙ። ሰልፉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት አስተባባሪነት የተጠራ ሲሆን በተለያዩ የጀርመን ከተሞች፤ እንዲሁም በጀርመን አጎራባች የአውሮጳ ሃገራት ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያ ተሳትፈዋል።

ሰልፈኞቹ እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ አካባባቢዎች «በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ» የሚፈፀመውን ግድያና ግፍ እስካሁን ማስቆም አልቻለም። «ኢትዮጵያ ውስጥ በአሁኑ ጊዜ የሚፈጸመው በቃላት ተገልጾ የሚያልቅ አይደለም» ያሉት ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸው ከተሰላፊዎቹ አንዱ የሆኑት በጀርመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መሥራችና የኮሎኝ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል አስተዳዳሪ ሊቀካህናት ዶክተር መርዓዊ ተበጀ፤ «ሰዎች በቋንቋቸው፤ እንደዚሁም በሃይማኖታቸው ተለይተው እየታረዱ፣ እየተጨረሰ ይህን ያህል ግፍ ሲፈጸምባቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ተብዬ ይህን ሰቆቃ ሊያስቆም አልቻለም» በማለት ዛሬ ድምጻቸውን በዓለም ሸንጎ ለማሰማት መውጣታቸውን ገልጸዋል። የሰልፉ ተሳታፊዎች ኢትዮጵያውያን ካህናትና ምዕመናን ብቻ ሳይሆኑ የሌሎች ሃገራት ዜጎችም አብረዋቸው ድምጻቸውን እያሰሙ እንደሆነም አመልክተዋል። በተለይ በኦሮሚያ ክልል አርሲ፤ ጅማ፤ ወለጋ፣ ሻሸመኔ፣ እንዲሁም በሐረር ክርስቲያኖች መገደላቸውን የገለጹት ሊቀካህናት ዶክተር መርዓዊ፤ ባጠቃላይ «በሀገሪቱ ግፍ እየተፈጸመ ነው» በማለት በጀርመንዋ ዋና ከተማ በርሊን ለሰልፍ ያስወጣቸውን ምክንያት ዘርዝረዋል።

ወንጌለ ናዚዝም

የኦሮሙማው ክንፍ
"ብዙዎች ግን ወተታችንን ይወዳሉ ፣ሥጋችንን ይወዳሉ፣ፍየሎቻችንን ይወዳሉ፣በጎቻችንን ይወዳሉ፣በሬዎቻችንን ይወዱታል፣መሬታችንን
ይወዳሉ፣ከተሞቻችንን ይወዳሉ እኛን ግን......???"

ይኽ የናዚዝም  (የጥላቻ የወንጌል ) የሚሰበከው  በዘር ተቋቋመው በወልዳ ዱካ ቡኦታ ማኅበር በተዘጋጀው  መርሐ ግብር ላይ ነው። በአራት ኪሎ።እኝህ ሰው "ምንም ቅልቅል ዘር የሌለባቸው ተንጹህ ኦሮሞ ጳጳስ(Organic Oromo)"  ተብለው የጰጰሱት ነገር ግን አንገታቸው በአክራሪ እስልምና ስለሚቀላው  ኦሮሚኛ ተናጋሪ ኦርቶዶክሶች ትንፍሽ የማይሉ በአንጻሩ ደግሞ የኦሮሞ ብሔርተኝነት ዋና አቀንቃኝ ናቸው።"ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም "የሚል የምንፍቅና ትምህርት አስተምረው "ኦሮሞ በመሆኔ ተዘመተብኝ" ማለታቸውም የሚታወስ ነው።እኔ የሚያዝኑኝ እኝህንና መሰሎቻቸውን "አባት" ብለው እየተከተሉ የመታረጃ ቀናቸውን የሚጠባበቁ ኦሮሞች ናቸው። እባካችሁ ዘረኝነትን እየተጸየፍን በኦርቶዶክሳዊ ኅብረታችንን እንበርታ ።በልዩ ወንጌል በልዩ ትምህርት አንወሰድ። ማንም ይሁን ማን ከምሥራቅ ይምጣ ከምዕራብ፣ከሰሜን ይምጣ ከደቡብ መለያየትን፣ዘረኝነትን የሚሰብክ እንኳንስ አባታችን ኦርቶዶክስ ሊባል አይገባውም።


የሰሜን አሜሪካ ማኅበራት የጋራ መግለጫ

የሰሜን አሜሪካ ማኅበራት የጋራ ማግለጫ
ቀን ኅዳር ፲፩/፳፻፲፰ ዓ/ም (November 20, 2025)

 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 

ምሥራቅ አርሲ በምዕራብ ሐረርጌ እንዲሁም በሌሎች የሀገራችን ክፍሎች በአሰቃቂ ሁኔታ እየተገደሉ እና መከራ እየተቀበሉ ያሉ ኦርቶዶክሳውያንን አስመልክቶ የተሰጠ የጋራ መግለጫ

 

ü    የሰሜን አሜሪካ ካሪቢያንና ላቲን አሜሪካ የሰንበት ት/ቤቶች ኅብረት፣

ü    በኢ/ኦ/ተ/ሰ/ት/ቤ/ማ/መ ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣

ü    በኢ/ኦ/ተ/ቤ የማኅበረ በዓለ ወልድ በሰሜን አሜሪካ

ü    ዋልድባን እንታደግ ሰሜን አሜሪካ

 

Wednesday, November 26, 2025

የዘጸአት ነገረ መለኮት ትርጓሜ

ጉዞ ወደ ከነዓን 

ከነዓን በትርጉሙ ዝቅ ያለ ትኁት የሚል ትርጉም ሲኖረው የሸንበቆ ምድር ማለት ነው የሚልም አለ። ነገር ግን የኖኅ የልጅ ልጆች የካም
ስንቶች ምንደኞች አሉን ይሆን? 

ዘሮች ሲሆን መጀመሪያ የተስፋይቱን ምድር የኖሩ የጥንቷ ከነዓናውያን ሕዝቦች መጠሪያ ነው። በጥቅሉ የተስፋይቱ ምድርን ያመለክታል። በዮርዳኖስና በሜዲትራንያን መካከል ያለ ነው። ዘፍ.9 እና 10

 የነዌ ልጅ ኢያሱ እንጂ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች ዮርዳኖስን እንዳላሻገራቸው እንዲሁ ክርስቶስ ወደ መንግሥተ ሰማያት የሚገቡባትን ጥምቀት ለአዳም ልጆች አልሰጣቸውም ይኽንን መንፈስ ቅዱስ ሰጣቸው እንጂ። ይኽውም ከእርሱ ጋር ያለ የክርስቶስ መንፈስ ነው። (ዘቦቱ ለከ ምስሌሁ ወምስለ ቅዱስ መንፈስ) እንዲል) ሊጦን።

እርሱም ከሁሉም ሐዋርያት ጋር ይኖራል እነዚኽም በእውነት መንግሥቱን እስኪወርሱም ድረስ በዲያብሎስ ሠራዊት ላይ ድል መንሳትን አሸናፊነትን ይሰጣቸዋል። 

Monday, November 24, 2025

የነቢያት ጾም- እንኳን አደረሰን።

በዘመነ ብሉይ ነቢያት እግዚአብሔር ወልድ ከንጽሕተ ንጹሐን፤ ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ
ለአዳም የገባለትን ቃል ይፈጽም ዘንድ  ትንቢት በመናገር ለሕዝቡ የምሥራችን ቃል ያበሥሩ ነበር፡፡ አምላካችን ከድንግል ተወልዶ ከእናቱ ጋር ወደ ግብፅ ምድር እንደሚሰደድ፣ በባሕረ ዮርዳኖስ እንደሚጠመቅ፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ሲል መከራና ስቃይ እንደሚቀበል፣ እንደሚሰቀል፣ እንደሚሞት፣ ከሙታን ተለይቶ እንደሚነሣ፣ እንደሚያርግና ዳግም ለፍርድ እንደሚመጣ  በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው አስቀድመው ትንቢት ተናግረዋል፡፡

ነቢያቱም የትንቢቱን መፈጸም በተስፋ ይጠብቁ፣ በጾምና በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ይማጸኑ ነበር፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ አስቀድሞ ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ‹‹ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኃል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች›› በማለትም እንደተናገረ ትንቢት ኢሳይያስ ላይ ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡ (ኢሳ. ፯፥ ፲፬)

Friday, November 21, 2025

ኅዳር ሚካኤል

ቅዱስ ኤጲፋንዮስ “ሚካኤል ሥዩም በዲበ ኃይላት፤ በኃይላት ላይ የተሾምክ ሚካኤል” ሲል ያመሰገነው ቅዱስ ሚካኤል በኃይላት መላእክት ላይ የተሾመ ሊቀ መላእክት እንደመሆኑ በዓለ ሢመቱ ኅዳር ፲፪ ቀን በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ይከበራል፡፡ (መጽሐፈ አክሲማሮስ)
ኃይላት የተባሉት መላእክትም ሰዎች በዓለም ፈተና ውስጥ ሆነው ሰይጣን ሊያደክማቸው ሲፈልግ ኃይልን ብርታትን የሚሰጡ፣ ይህን ዓለም ንቀው በበርሃ ወድቀው ከሥጋ ምኞት ጋር የሚጋደሉትን፣ በከተማም እየኖሩ መንፈሳዊ ትሩፋት የሚያደርጉትን ደግሞ የሚያበረቱ ናቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ “እርሱም ወደ ሰማይ ያረገ እግዚአብሔርም ተቀምጦ ያለ መላእክትና ሥልጣናት ኃይላትም የተገዙለት ነው” ሲል  “ኃይላት” በማለት ያነሣቸው በኢዮር አራተኛይቷ  ከተማ  የሚኖሩትን  ነው፡፡ በእነዚህ ላይ እግዚአብሔር  ቅዱስ ሚካኤልን አለቃቸው አድርጎ ሾሞታል፡፡ (፩ኛጴጥ.፫፥፳፪)
ሊቀ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል

የቅዱስ  ሚካኤል  ሢመት  በነገደ  መላእክት  ላይ ብቻም ግን  አይደለም፤  የእግዚአብሔር  ሕዝብ  በሆኑት  ላይም ጭምር ነው፡፡ ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ትርጓሜ በዕብራይስጥ “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠቅሳሉ፤ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ላይ እንዳሰፈሩት ደግሞ የስሙን ፊደላት በመተንተን እንዲህ ተርጉመውታል፤ ሚ-መኑ፣ ካ-ከመ፣ ኤል-አምላክ፤ “መኑ ከመ አምላክ፤ እንደ አምላክ  ማን ነው”  (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ)
የሰማይ ሠራዊት ሁሉ አለቃቸው  ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ  ይኽ ኃያል መልአክ  ቅዱስ  ሚካኤል በብሉይ  ኪዳን  የእግዚአብሔር  ሕዝብ  የተባሉትን  እስራኤል  ዘሥጋን  ሲረዳና  ሲጠብቅ  እንደነበረ ተጽፎልን  እናገኛለን፡፡  ለምሳሌ  መልአኩ  ቅዱስ  ሚካኤል  ለኢያሱ  በኢያሪኮ  ምድረ  በዳ  እንደተገለጠለት  “… ዐይኑን  አንሥቶ  ተመለከተ፤  እነሆም፥  የተመዘዘ  ሰይፍ  በእጁ የያዘ  ሰው  በፊቱ  ቆሞ አየ፤  ኢያሱም  ወደ  እርሱ  ቀርቦ፥  “ከእኛ  ወገን  ወይስ  ከጠላቶቻችን  ወገን  ነህ?”  አለው፡፡  እርሱም “እኔ  የእግዚአብሔር  ሠራዊት  አለቃ  ነኝ፤  አሁንም  ወደ  አንተ መጥቼአለሁ፡፡” ሲል ተናግሯል፡፡ (ኢያ.፭፥፲፫)
እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነፃ ሲያወጣቸው ይመራቸው የነበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ፥ ወዳዘጋጀሁልህም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ ፥እኔ መልአኬን በፊትህ እልካለሁ”  እንዲል፤  ሹመቱ  በእግዚአብሔር  ሕዝብ  ላይም  በመሆኑ  ስለ  እነርሱ ከእግዚአብሔር ምሕረትን ይለምንላቸው  ነበር፡፡ (ዘፀአት.፳፫፥፳)

“እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ”

“እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ”
  ኢያ.፭፥፲፫

በቅድስና፣ በውዳሴ፣ በኅብረ ቀለም በመላእክት ዝማሬ በደመቀው በዓለመ መላእክት ውስጥ ቅዱሳን መላእክት በነገድ ተከፍለው
መኑ ከመ እግዚአብሔር

ይኖራሉ፡፡ እነርሱም የዘወትር ምግባራቸው እንዲያውም ምግባቸው ፈጣሪን ማመስገን ነው፡፡ ስፍራ ቁጥር የሌላቸው መላእክቱም በሦስቱ የመላእክት ከተሞች ኢዮር፣ ራማ እና ኤረር በአለቃቸው ስር ሆነው ዘወትር አምላክን ያገለግላሉ፡፡ ለዚኽም ድንቅ ሥራው ክብረ ምስጋና ይድረሰውና፣ በኢዮር ከተማ የኃይላት አለቃ አድርጎ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልን ሾሞታል፤ ይኽም የሆነበት ኅዳር ፲፪ ቀን የከበረ በዓል ነው፡፡ ስለዚኽ የዚህን የከበረና የገናና መልአክ በዓሉን እንድናደረግ ቅዱሳን አባቶች ሥርዓት ሠሩልን፡፡

የስሙ ትርጓሜ “ማን እንደ እግዚአብሔር” የሆነው የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል፣ እንደ አምላክ ኃያል፣ ቸርና ርኅሩኅ ነው፤ በቅዱሱ መጽሐፍ ላይ ይኽንን ነገር ራሱ መልአኩ ለነቢዩ ኢያሱ እንዲህ ሲል ገልጾለታል “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ” ኢያ.፭፥፲፫

ሊቀ መለእክት ቅዱስ ሚካኤል፣ ለእኛ ሰዎች አምላጅ ሲሆን ለቅዱሳና ሰማዕታት ደግሞ አጋዣቸው የሆነው ነው፤ በሕይወታቸውና በተጋድሏቸውም እስከ መጨረሻው ይረዳቸዋል።

እግዚአብሔርን የሚወድ  ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የሚስቱም ስም ቴዎብስታ ነው፡፡ እነርሱም ሁልጊዜ ያለማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያደርጉ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ ለቅዱስ ሚካኤልም ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን እስኪያጡ ድረስ ቸገራቸው፡፡ ዱራታዎስም ሸጦ ለመልአኩ በዓል መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱንና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡

Thursday, November 20, 2025

በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ውሃቢያ እና ጂሃዲስት ምን ላይ እንዳሉ ያየም የሰማም የለም




ዛሬ ዛሬ በሃገራችን ኢትዮጵያ ያለው መንግሥትም ሆነ ሕዝቡ በጣም ያልተገነዘበው አንድ ትልቅ አደጋ ለሃገራችንም፣ ለሕዝባችንም ብሎም ለቀጠናው ከፍተኛ የሆነ አደጋ የጋረጠ ነገር ቀስ በቀስ እግር አውጥቶ እየተንሰራፋ ባለበት በአሁኑ ወቅት፤ ከሁሉም በላይ በሃላፊነት ስሜን የሕዝቦችን ደህንነት እና ሁኔታ መጠበቅ ማስጠበቅ፤ የሕግ የበላይነትን ማስፈን ያለበት መንግሥት ቢሆንም ያንን ሥራውን ለሌሎች አሳልፎ የሰጠበት እና ዋናውን ሥራውን ትቶ ብዙ በማይመለከተው እና ባልበላው ቦታ ላይ ገብቶ ሕዝብን ከሕዝብ ሲያጫርስ እና እራሱም መሣሪያ ሆኖ አንድን ማኅበረሰብ ለመጨረስ ወይም ቁጥር ለመቀነስ በሚል ብዙ ድካም ሲደክም እና ነገሮችም ሳይሳኩለት እየታየ ነው፤ ከመንግሥትም አካላት ተው የሚለውም ያለ አይመስልም፤ ለነገሩ ብዙዎቹም የመንግሥት አካላት አብረው ተከትለው እንደ ነፋስ መንፈስ እንጂ ቆም ብሎ የሚያስብ የሚያመዛዝን የጠፋበት ዘመን ነው፤ ብዙዎቹ ገና ሙቀት ላይ ናቸው የተለየ የሚንፈላሰስበት መኪና አለው፣ መንግሥት የሚሰጠው የመኖሪያ ቤት አለው፣ ወጪውንም በሙሰኝነት የለመደው ስለሆነ ኑሮውም አይሰማውም፣ ምቾት ላይ ነው ብዙው በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ያሉት ሰዎች ከሆኑ ሰዎች እንበላቸው እና፤ ሰዎች ከሆኑ ማለት ነው፤ ብዙዎች እየሆነ ያለውን አያስተውሉም፤ "እኔ ከሞላልኝ፤ . . ." በሚል ብሂል ይመስላል ብዙም አይመለከታቸውም፤ እንደ ኢትዮጵያ የሰው ልጅ በየቀኑ እንደ በግ የሚታረድበት ሃገር ያለ እስከማይመስል ድረስ ዛሬ ዛሬ እማ አምስት አሥር ሰው ሲታረድ ወይም ሲገደል ብዙም ቦታ ሰጥቶ የሚያይ ሰው የለም፤ መንግሥትም የመንግሥትም ሰዎች ብዙም አይመለከታቸውም እስከ መቼ ይሆን?

Wednesday, November 19, 2025

" ሦስት ዓመት ተከራክረን በፍርድ ቤት ያስወሰንነውን ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ወረዳው ለመክፈል ፈቃደኛ አልሆነም " - ጤና ባለሙያዎች

ውዝፉን በአንዴ ለመክፈል በጀት የለውም ወረዳው " - የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ 
የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ


በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ሃላሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ያሉ 128 ጤና ባለሙያዎች በፍርድ ቤት የወሰነላቸው #ከ3_ሚሊዮን ብር በላይ የትርፍ ሰዓት ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

ጤና ባለሙያዎቹ ምን አሉ ?

" ወላይታ ዞን ሃላሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለሶስት ዓመት ሙሉ ተከራክረን በፍርድ ቤት ያስወሰንነውን 17 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ ወረዳው ለመክፈል ፈቃደኛ አልሆነም።

Tuesday, November 18, 2025

ቅዱስነታቸውን በተመለከተ የሚሰማው ምንድነው?

"…ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ በቅዱስነታቸው ጤንነት ዙሪያ እንዲህና እንዲያ ሆነ እያተባሉ የሚወሩ ወሬዎችን በሰማሁ ጊዜ በቀጥታ ወደ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ

ወፎቼ ነው የደወልኩት። ወፎቼም እዚያና እዚህ ገብተው አገኘነው ያሉትን መረጃ እነሆ ጀባ ብያችኋለሁ። 

• የሆነው እንዲህ ነው ይላሉ ወፎቼ… 

"…የጥንታዊቷ፣ የቀኖናዊት፣ ሐዋርያዊቷና ብሔራዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛው ፓትርያርክ የሆኑት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በገጠማቸው ድንገተኛ አደጋ ምክንያት በሕክምና ላይ እንደሚገኙ ታማኝ የመረጃ ምንጮቼ የሆኑት ወፎቼ ከአዲስ አበባ መረጃውን አድርሰውኛል። 

"…ቅዱስነታቸውን ለሕክምና ያበቃቸውም ጉዳይ የመረጃ ምንጮቼ እንደነገሩኝ ከሆነ "በማረፊያ ክፍላቸው ዎክ ሲያደርጉ የታጠፈ የመሬት ምንጣፍ ጠልፎ ስለጣላቸው በድንገት ወድቀው" እንደሆነ እና በዚህም ምክንያት ድንጋጤ ተጨምሮበት በአደጋው በአንደኛው እግራቸው ዳሌ ላይ ስብራት እንደረሰባቸውና በዚህም ምክንያት በሀኪሞች በተደረገላቸው ከፍተኛ ርብርብ ቀዶ ጥገና ተደርጎላቸው ሕክምና እየተከታተሉ መሆናቸውን ነው የመረጃ ምንጮቼ የሚገልፁት። በአደጋው ወቅት በተጨማሪ የአልጋ ጠርዝም ሆነ ሌላ አደጋውን ከፍ የሚያደርግ ተጨማሪ ምት ስላልገጠማቸውና ሙሉ ለሙሉ ከመሬቱ ላይ ብቻ በመውደቃቸው የደረሰባቸው አደጋ ቀላል ባይባልም ነገር ግን ለክፉ የማይሰጥ በመሆኑ በዚህ ሁለትና ሦስት ቀናት ውስጥ ወደ መንበረ ፓትርያርክ ማረፊያ ቤታቸው እንደሚመለሱም ነው የወፎቼ መረጃ የሚያመለክተው። 

በምስራቅ አርሲ አዋሳኙ በምዕራብ ሐረርጌ የሰባት ልጆች እናት መገደላቸውን ስምዓ ተዋሕዶ ዘገበ፡፡

የኦርቶዶክሳውያኑ ደም መፍሰስ በአስቸኳይ ይቁም!!
ምዕራብ ሐረርጌ ዶባ ወረዳ ኢፋ ጀነቴ ቀበሌ ላይ ታግተው ከአንድ ቤተሰብ 4 ሰው አባት አቶ ደበበ እና እናት ወ/ሮ ገነት (የሰባት ልጆች እናት)፣ ወንድ ልጃቻው እና የልጃቸው ባል አግተው ከወሰደዋቸው በኃላ ብዙ ድብደባና እንግልት ደርሶባቸዋል::  ከእነዚህ ኦርቶዶክሳውያን ውስጥም በድብደባው ምክንያት ሕይወታቸው ያለፈው የሰባት ልጆች እናት የሆኑት ወ/ሮ ገነት  ስርዓተ ቀብራቸውም  በዶባ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል። 

ኦርቶዶክሳውያኑን ሲያሰቃዩ የነበሩ አጋቾች በድካም እንቅልፍ ላይ መሆናቸውን እንደአጋጣሚ  በመጠቀም ከታጋቾች መካከል የነበሩት አቶ አበበ አምልጠው በመውጣትና ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው  በአካባቢው የሚገኙ ፖሊሶች ባደረጉት ጥረት አስከሬን ለማንሳትና  እና የቀሩ ታጋቾችን ለማዳን መቻሉን ከአካባቢው የደረሰን ጥቆማ ያመለክታል፡፡  ይሁንና አሁንም በእገታ ውስጥ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የ3.5 ሚሊዮን ብር ካሳ ተጠይቆባቸዋል ።

የኦርቶዶክሳውያን ሞት ይቁም!!!

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

Sunday, November 16, 2025

የምዕራብ ሐረርጌ ኦርቶዶክሳዊየ ሥጋት ላይ ናቸው።

ምዕራብ ሐረርጌ አደጋ ላይ ናቸው!

 የአርሲው ኦርቶዶክሳዊ ግድያ ወደ ሐረርጌ የተሻገረ ይመስላል ።
 ለማንኛውም ሁላችንም ኦርቶዶክሳዊያን ባለቹበት መሰባሰብ መደራጀትይጠበቅብና ! 
በምዕራብ ሐረርጌ ዶባ ወረዳ አንድ (1 )ኦርቶዶክስ ሲገደል  አራቱ (4)ደግሞ ታፍነው ተወስደዋል ። በዳሮለቡ ወረዳ  የተገደሉት ተገድለው ከቀያቸው ተፈናቅለው የቀሩት በሰቀቀን  ነው ያሉተ። ሰዎች እንዳያስጠጋቸው በፖሊስ ለሁሉም ታዝዘዋል። ስጋት ውስጥ ያሉት ወረዳዎች ዳሮለቡ ፣ አንጫር ጭሮ ወረዳ ለሞት የታጩ ናቸው።

በአሰቦት ገዳም አካባቢ እንደሚታወቀው በአክራሪ ዋሃቢያውያን የተከበበ እንደሆነ ይታወቃል፤ በተለያየ ጊዜ ተደጋጋሚ ጥቃት ግድያ ማዋከብ እያደረሱ እንደሆነ ይታወቃል፤ በተደጋጋሚ ለአካባቢው የመንግሥት ተቋማት ጥቆማው ተሰጥቶ ነበር፤ ከመከላከል ይልቅ ሁኔታዎችን አቅልሎ የመመልከት እና ጉዳቱ እንዲባባስ እና እንዲከፋ የሚያደርጉት ብዙ ነገሮች እንዳለ አብዛኛው ኦርቶዶክሳዊ የሚረዳው ነገር ነው፤ ላለፉት በርካታ ዓመታት የእርሻ ቦታቸው ላይ መነኮሳት ተገልዋል፣ የአብነት ተማሪዎች በጥይት ተደብድበዋል፣ ሌሎችም ብዙ በርከት ያሉ ጥቃቶችን በገዳሙ ላይ ሲያደርሱ ቆይተዋል፤ እንደተባለው በአርሲ፣ በወለጋ፣ በምዕራብ ሐረርጌ፣ በአሰቦት፣ በምዕራብ አርሲ በሁሉም አካባቢዎች ብቸኛው አማራጭ መደራጀት እና እራስን መከላከል ብቸኛው እና አይነተኛ አማራጭ መሆኑን ልብ ይሏል፤ "የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም" እንደሚባለው የሄ መንግሥት በምንም መልኩ መፍትሄ ያመጣል ብሎ መጠበቅ "ከዝንብ ማር " እንደመጠበቅ ነው



የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

አርሲ የሰቆቃ ምድር

ወንድማችን ዲያቆን ዮሴፍ ከተማ ና ወንድማችን ጸጋየ ክፍሉ ትናንት #የኦሮሚያ ኦርቶዶክሳውያን ፍጅት በሚል መርሐ ግብር በኢትዮ

ቱንቢ ሚዲያ ካቀረቡት እጅግ ውስጤን የነካኝና ሁሉም ኦርቶዶክሳዊና ባለ አእምሮ ኢትዮጵያዊ ሊሰማው የ
ይገባዋል ብዬ ያመንሁባቸውን ሁለቱን ላቅርብላችሁ፦

፩  እኝህ በፎቶ የምታዩአቸው ካህን ቄስ  አሳልፈው መኩሪያ ይባላሉ።በምሥራቅ አርሲ ዞን መርቲ ወረዳ አቦምሳ መድኅን ዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ናቸው።ለትንሳኤ ዋዜማ (2017) ምሸት ውስጣቸው ይረበሽና ልጄን ይገድሉብኛል ብለው በመስጋት ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ።ልክ ቤታቸው ሲሄዱ እሳቸው እንደሰጉት አልቀረምና አራጆቹ ልጆቸውን ለመውሰድ ቤቱን ከበዋል። ልጃቸውን አሰመለጡ ራሳቸው ግን ማትረፍ አልቻሉም ታፍነው ተወሰዱ።500ሺ ብር ተጠየቀባቸው።አመለሸጋ ሰው አክባሪ ዝምተኛ  ተናግረው የሚሰሙ ሰው አስታራቂ ሴለሆኑ ማኅበረሰቡ እንደምንም ብሎ ተሯሩጦ 500ሺ ብሩን ያዘጋጃል።አራጆቹ ገንዘቡን ወሰዱ ነገር ግን አልለቀቁአቸውም  ስምንት ወር ሆኖአቸዋል ይኑሩ ይሙቱ አይታወቅም ባለቤታቸው ግን "ካህኔ እንደ ወጣ ቀረ" ብላ በለቅሶ ልትሞት ደርሳለች።ሰው ሰላምታ ሲጠይቃትም የምትመልሰው  መልስ "ካህኔ እንደ ወጣ ቀረ"የሚል ነው።

አባ!!! ምን አሉ? ልናሻግራችሁ ነው ወይስ አስክሬናችሁን ረብርበን ልንሻገርባችሁ? እስቲን ይድገሙት።

ስንት ዓመት ነው የምትቀልዱት? ከደርግም፣ ከወያኔም፣ ከኦነግም፣ ከብልጽግናም ጋር ተቃቅፎ  ተራ በተራ እየተኙ ዘመናትን 
ማስቆጠር ለክርስቶስ ምስክር ያስብላል? ባይሆን  እንኳንስ "እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ" የሚለውን ይዞ የመጋደል የአዲስ ኪዳን ፍጹምነት ለፍጥረታዊ ሰው የተሰጠውን አታመንዝር የሚለውን ኦሪታዊ ቃል ሻራችሁ አያድንም?

Thursday, November 13, 2025

ታሪክ ራሱን ደገመ!!

ታሪክ ራሱን ይደግማል!
ታሪክ ራሱን አይደግምም ነገር ግን ተመሳሳይ ክስተት ኾኖ ይደገማል። ታሪኩ ቤተክህነት ማኅበረ ቅዱሳን ፌደሬል ጉዳዮች የሠሩት ነው። የዛሬው ለወጥ የሚለው የፌደራል ጉዳዮች ወይም የሰላም ሚኒስቴር በሃይማኖት ተቋማት መተካቱ ብቻ ነው። እንዲኹም በዚኽ
ቡድን ማኅበረ ቅዱሳን አጣሪ ኾኖ አለመግባቱ ነበር። 

ሕወሃት ዋልድባ ገዳምን ለስኳር ልማት ፕሮጀክት ብሎ ገዳሙን ሊያነሣው ፈልጎ ማረስ ሲጀምር ከፍተኛ ቁጣ ይቀሰቀሳል። ይኽንን የነደደ ቁጣ ለማብረድ ተብሎ ከጠቅላይ ቤተክህነት፣ ከማኅበረ ቅዱሳን ከፌደሬል ጉዳዮች የተውጣጣ ቡድን መጋቢት 25- 30 ቀን 2004 ዓ.ም. ወደ ዋልድባ ይላካል። ሙሉ ወጩው የተሸፈነው በማኅበረ ቅዱሳን በኩል ነበር። 

በኦሮሚያ ክልል በከፍተኛ ሁኔታ እየተባባሰ የመጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስቆም የክልሉም ሆነ የፌደራል የመንግስት አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ኢሰመጉ ጠየቀ

ረቡእ፣ ሕዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ሰላማዊ በሆኑ ዜጎች ላይ ያነጣጠሩ እና ለሞት፣ ለአካል
አርሲ የደም ምድር!

ጉዳትና ለእገታ የዳረጉ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ማረጋገጡን ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። በክልሉ በከፍተኛ ሁኔታ እየተባባሰ የመጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስቆም የክልሉም ሆነ የፌደራል የመንግስት አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡም ጠይቋል።

በምስራቅ አርሲ የተፈጸሙ የተለያዩ የመብት ጥሰቶችን መመርመሩን ያስታወሰው ኢሰመጉ፤ “በእነዚህ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በቂ ትኩረት እንዲሰጣቸው እና ድርጊት ፈጻሚዎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ መግለጫ ማውጣታችንና ጥሪ ማቅረባችን የሚታወስ ነው” ብሏል።

በዚህም ኢሰመጉ ባሰባሰበው መረጃ መሰረት በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በጉና መርቲ ሸርካ እና በሆሎንቆ ዋቢ ወረዳዎች ጥቅምት 14 ለ 15 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሁም በ 18 ለ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ብዛት ያላቸው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች፣ የእስልምና እምነት እንዲሁም የተለያዩ የሌሎች እምነት ተከታዮች በታጠቁ አካላት የተገደሉ መሆኑን እና የተወሰኑትም ታግተው የተወሰዱ መሆኑን ገልጿል።

Monday, November 10, 2025

የመንግሥት ባለሥልጣን ሆነው ሕዝብን የሚያስጨርሱትን በሙሉ አጋልጥ !!! መረጃው ለሁሉም እንዲደርስ አጋሩት

በምሥራቅ አርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ከ 200 በላይ ኦርቶዶክሳውያን በአክራሪ እስልምና ታጣቂዎች ተገድለዋል። ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ኦርቶዶክሳውያን ከቀዬአቸው ተሰደዋል። ገጠሩ ክፍል ከኦርቶዶክሳውያን ጸድቷል።ይኽን እልቂት ሲያስተባብሩ የነበረሩት የወረዳው
ባለሥልጣናት ናቸው ።  ከእነዚህ መካከል ለ ዛሬ ሦስቱን አቅርብላችኋለሁ።እነርሱም፦


1  ሬድዋን ጀማል =የጀጁ ወረዳ አስተዳዳሪ

2) ሚስባሁ ሰይዳ= ም/አስተዳዳሪ ፣የአርብቶ አዳሮችና  የእርሻ ባለ ሥልጣን

"ኦርቶዶክሳውያን ተለይተው አልተገደሉም" የሚለው የነቀሲስ ታጋይ ታደለ መግለጫ የኦርቶዶክሳውያን ግድያ እንዲቀጥል የተፈቀደበት ደብዳቤ አድርጌ ወስጄያለሁ።

መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ (ግብረ በላው ካህን)

እግዚኦ ለዳኝነት ፤ እነዚህ ካህን ተብለው ነው በምሥራቅ አርሲ ስንት ካህናት አንገታቸው ሲቀላ፣ ከሁለት ዓመት ሕጻን እስከ 70 ዓመት አረጋዊ አባት በአጠቃላይ ወደ 170 የሚጠጉ ክርስቲያኖች የተጨፈጨፉት "ፖለቲካዊ አንድምታ ያለው ግድያ ነው" አንተም ካህን ትባላለህ፤ እውን ካህን ለመሆኑም በእጅጉ ያጠራጥራል? እረ እንደው ምን ያክል ቢከፍሉህ ነው በእነዚያ ምስኪን ክርስቲያኖች ደም ላይ የተዘባበትከው? እውነት አንተም የንሰሃ ልጆች አሉህ? ቀድሰህ ታቆርባለህ? እግዚኦ ለዳኝነት!!!!! 

ዛሬ ሰኞ በምሥራቅ አርሲ 3 ኦርቶዶክሳውያን ተገደሉ፣ ሕዝቡ እየሸሸ ነው


=====
(EOTCMK TV ኅዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም)

ዛሬ ኅዳር 01 ቀን 2018 ዓ.ም ልዩ ቦታው ጠለታ ቅዱስ ገብርኤል በተባለ  አካባቢ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ገደማ ሦስት ኦርቶዶክሳውያን በአውድማ ላይ እህል እየወቁ ባሉበት በጥይት ተደብድበው በግፍ መገደላቸው ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመላክታል ።

ከተገደሉት ምእመናን መካከል ዲ/ን ኢዮብ እጅጉ፣  ጥላሁን ቦጌ  እና ሕፃን ጻድቃኔ ሠራዊቱ  የተባሉ ኦርቶዶክሳውያን ይገኙበታል ።
   
ሥርአተ ቀብራቸው በጠለታ ቅዱስ ገብረኤል ቤተክርስቲያን ዛሬ ኅዳር 01 ቀን 2018 ዓ.ም  ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል።

ከቤቲ ወ/ሐዋርያ ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ ........


'ዘማሪ' ቴዎድሮስ ዮሴፍ (በስም የጠቀስኩህ የፖስቱ ስክሪን ሻት እንደሚደርስህ ስለማውቅ ነው!) ምናልባት ዕውቀቱ ከሌለህ በኮ'ሚኒስታዊ
ዘማሪ ቴዎድሮስ 

ሥርዓት ዘመን በራሽያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን.....የሀገሪቱ ኦርቶዶክሳውያን ቤተ ክህነታቸው ውስጥ የነበሩ በሞታቸውና በተነፈጋቸው መብት ሲሳለቁ የነበሩ የገዛ ጳጳሳት ነን ባዮቻቸው ላይ ምን እንዳደደረጉ ገለጥ ገለጥ አርገህ ማንበብ ነው!
በዕርግጥ እኔ ''ሰው አርገኝና ሰው ይግረመው'' የሚልን ዘፈን መዝሙር ነው ብሎ ካወጣ ዘማሪ ነኝ ባይ ከዚህ የተለየ የረቀቀ ሀሳብ ብዙ አልጠብቅም..... ለዩቲዩብ ቪው ማድመቂያነት ካልሆነ በስተቀር በቀራንዮ ተሰቅሎ ወደ ሰውነት ክብር የመለሰን ዓምላክ ፊት እንዴት ይሄንን የረከሰ ወሬ የምስጋና መስዋዕት ነው ብለን ልናቀርብ እንችላለን??? ''የአጋዘን አስተሳሰብ ስላለኝ ወደ ሰውነት መልሰኝ'' ከሚል የግል ምኞት ለይቼ አላየውም!!
ለማንኛውም:-
የቤተሰብ ሙሉ አባላትን ጨምሮ ብዙ ኦርቶዶክሳውያን በሚሰቀጥጥ ሁኔታ በገ*ጀራ ሲታረዱና በጥይት ሲጨፈጨፉ፣ አንድ ነፍስ ያላወቀ የ4 አመት ህፃን ልጅ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን በመሆኑ ብቻ በጥይትና በገጀራ ሙሉ ቤተሰቡ ተጨፍጭፎ ተገ*ድሎ..እሱ በተዓምር ቢተርፍም በዚሁ ጭፍጨፋ በደረሰበት ጉዳት በህፃንነቱ ሊቦርቅበት የሚገባው

Saturday, November 8, 2025

ገዳያችን ማን ነው?

ወገን ተገደልን ብለን መጮኻችን ብቻውን በቂ አይደለም።ገዳይችንን ለይተን ማወቅ ይኖርብናል።በአርሲ የኦርቶዶክሳውያንን ዘር

እያጠፋ ያለው  "ኦሮሚያን የኢስላም ሀገር አድርጋታለሁ" የሚለው የጽንፈኛ ወሀቢያ ቡድን ነው። ኦነግ ሸኔ የሚባል  ታጣቂ ቡድን አርሲ ውስጥ የለም።እየመረረንም ቢሆን ይኽን እውነት ተቀብለን  የመዳኛ መንገድ እንፈልግ።እንደ፦ ሊቢያ፣ ሰሜን አፍሪካ፣ቱርክ  ከመጥፋታችን በፊት የምንችለውን እናድርግ።ገዳያችን  ወሀቢያ ነው።አንተ ስማቸውን መጥራት ስለፈራህ እነርሱም አይራሩልህም  የሚቀርልህ መከራም የለም።

16 ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ 9ኙን ገድለው የጣሉባቸው የምስራቅ አርሲ ዞን የጀጁ ወረዳ አንጎደቼ፣ ጉሬ፣ወሸባ፣ተሬ አሚኛ ቀበሌዎች ዛሬም በርካቶችን አፍነው መውሰዳቸውን መንክር ሚዲያ መዘገቡን አጋርቻለሁ፡፡ 

እኛ በጮህን ቁጥር 'ይውጣላቸው' በሚል እልህ በሚመስል ሁናቴ አፈናውንና ግድያውን በየቀኑ አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡

እኛስ?

አለቃው መነኩሴ ብቻ 

መቼስ የቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለች ክፋት መንፈሳዊነት ወይም ጥቅስ ማልበስ የተለመደ ስልት ነው። ምእመኑን አይጠይቅም እልልል
እውን ቤተ ክርስቲያንን መነኩሴ ነው የሚያስተዳድረው?

ማለት ይቀናዋል። ለምን እንዴት ብሎ መጠየቅ ነው ማሰብ የሚባለው። የሚጠይቅ ሰው ለውጥ ፈላጊ ነው። 

ከዚኽ በፊት “ደብር ወገዳም” የሚል ስም አስገርሞኝ ነበር። አኹን ደግሞ “አስተዳዳሪው መነኩሴ ብቻ” የምትለዋ ሌላ ቅጥፈትን እንመልከት። 

በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ካህን ነው። ካህን መነኩሴም ቄስም ሊኾን ይችላል። መነኩሴ ብቻ፣ ቄስ ብቻ የሚል ካለ ሌላ ድብቅ ተንኮል ይዟል ማለት ነው። እንደ ዛሬው ምንኩስና የከተማ ከመኾኑ በፊት ቤተ ክርስቲያንን የመሩት ካህናት (ቄሶች) ናቸው። 

የደጃዝማቾችና የራሶች ንሰሐ አባት በተለይ በንጉሡ ጊዜ ንሰሐ አባቶቻቸው መነኮሳት እየኾኑ ወደ አስተዳዳሪነት መምጣት ጀመሩ። 

Thursday, November 6, 2025

አንዳች አይነት ህብረት ያስፈልገናል

አንዳች አይነት ህብረት ያስፈልገናል። ይህ ህብረት ዋነኛ ዓለማው አድርጎ የሚንቀሳቀሰው የኦርቶዶክሳዊያንን ሰቆቃ በተገቢውና በተደራጀ
አርሲ የደም ምድር!

መልክ መረጃ ማሰራጨት፣ በጽሁፍ በምስልና ድምጽ ሰንዶ ማስቀመጥ፣ ኦርቶዶክሳዊያንን በተለያየ መልኩ Mobilize ማድረግ ሲገባ ይህንን ማቀናጀት የሚያስችል፣  ከተለያየ ሙያ መስክ የተውጣጡ ኦርቶዶክሳዊያን ያሉበት ህብረት ያስፈልጋል። 

አሁን እያደረግን ባለው እንቅስቃሴ የታዘብኩት ለብዙ ሰው Tweeter እና Email Campaign ማድረግ እንኳ ቀላል እንዳልሆነ ነው። የተዘጋጁ ትዊቶችን  Copy Paste Complex እየሆነባቸው እንዴት እናድርገው የሚሉ እልፍ ናቸው። አስቀድሜ እንዳልኩት ይህ ህብረት ቢኖር የIT ባለሙያዎች በቅጽበት የሚከተሉትን ዘመናዊ መፍትሄ በመጠቀም የብዙሃኑን ችግር መፍታት ይቻል ነበር። ቀላል የ Campaign Blog/website ሰርተውልን የሚያስፈልጉ ጽሁፎችና ፎቶዎች እዛ ላይ እየተቀመጡ በአንድ "Single Button Click"  ብቻ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኦርቶዶክሳዊያን Email ወይም Tweet እንዲልኩ የሚያስችል Automated System መዘርጋት ይቻላል። 

ይህን በግላችን የIT ባለሙያ ጓደኞቻችንን በአንድ ቀን ሰርተው ዝግጁ ማድረግ እንደሚችሉ ነገረውኛል፤ ነገር ግን እንደዚህ አይነት እንቅስቃሴችን ''በግል'' ለማድረግ መሞከር ዃላ የግል አመለካከትን በቤተክርስቲያን ጉዳይ እያስታከክን ማስኬድ ሊያመጣ ስለሚችል ነው ህብረት ያስፈልጋል ያልኩት።

የዘመኑ የትግል ዘዴ ቅንጅት፣ ስልታዊ ዕቅድ እና ቴክኖሎጂን በአግባቡ መጠቀምን ይጠይቃል። ይህን ህብረት በመመሥረት፣ ከግለሰባዊ ጥረት ወጥተን ጠንካራ፣ ውጤታማ እና ዲጂታላይዝድ የሆነ ንቅናቄ መፍጠር እንችላለን!

Mariamawit Henok


የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

የጸሎት እና የምኅላ መርኅግብር በዋሺንግተን ዲሲ ማርያም ቤተክርስቲያን ተጠርቷል


በመላው ዋሺንግተን አካባቢ ለምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ በነገው እለት ማለትም November 7, 2025 at 5:00 pm ጀምሮ በደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በምሥራቅ አሩሲ አባባቢ ለተጨፈጨፉት በመንግሥት መር እሥላማዊ አክራሪዎች ደማቸው ለፈሰሱት ንፁሐን ኢትዮጵያውያን ኦርቶዶክሳውያን የጸሎተ ፍትሃት ይደረጋለ ተብሎ መረጃው ደርሶናል፤ ይሄንንም ዜና በአካባቢው ለሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ለማድረስ ለዝግጅት ክፍላችን በተላከልን መሠረት ለማዳረስ እና ለማስታወስ እንወዳለን፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ሃገራችን በተለይ አሩሲ ላይ የደም ጎርፍ ሃገሪቷን እያጠባት ነው፤ ቤተክርነቱም ቤተምንግሥቱም ትንሽ እንሰሳ እንኳን የሞተባቸው አይመስልም በሚያሳዝን መልኩ
እነዚህ የቤተመንግሥቱም ይሁኑ የቤተክርነቱ ሰዎች ይሄው የሚጨፈጨፈው ኦርቶዶክሳዊ ነው ለቤተክህነቱ አሥራት በኩራት፣ ሙዳየ ምጽዋት በማለት ይከፍላል፤ ሲሞት ግን ፍትሃት እንኳን አያደርጉለትም በእጅጉ ይዘገንናል።
ቤተመንግሥቱም ቢሆን ይሀው የሚገደለው ሰው ነው ታክሱን የቄሳርን ለቄሳር እያለ ግብሩን እየከፈለ የሚኖረው ፤ ነገር ግን ሲጨፈጭፉት እና ሲያስጨፈጭፉት እንኳን ትንሽ ሃዘኔታ ወይም ትንሽ ሪሞርስ የላቸውም ፤ አንድ ቀን ዓለምም ሕዝምብ ይፋረዳችኋል የጊዜ ጉዳይ ነው፤





የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

Wednesday, November 5, 2025

የተለያዩ ክርስቲያኖች ድምጻቸውን በሶሻል ሚዲያ እያሰሙ ነው፤ እኛስ? በተለይ አባት የተባልን?


ደግሜ ልንገርህ ስማኝማ…!

Jihadis Threat in Ethiopia
"…የትዊተር ዘመቻው ጥሩ ነው። ዓለም ሕዝብ ሆይ እኛ ኢትዮጵያውያን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች በጽንፈኛ የወሀቢይ እስላሞች 
መገደላችንን፣ መታረዳችንን፣ መፈናቀላችንን ዕወቁልን ብሎ በተገኘው አጋጣሚ ሁላ መጮሁ፣ ማመልከቱ፣ ምስክር መጥራቱ ጥሩ ነው አልነቅፈውም። በርቱ ነው የምለው።

"…ነገር ግን የገጠመን ጠላት የትዊተር ዘመቻ አያስደነግጠውም። አያስፈራውም፣ መቶ ሺ መግለጫም አያስደነብረውም። ሚልዮን ሆነህ ሰልፍ ብትወጣ እሱ ደንታው አይደለም። 

"…አራጁ ወሀቢያ መንግሥት ሆኗል። የሚደገፈው አንተ ስሙን፣ ድረሱልን በምትላቸው ኃያላን ጭምር ነው። እነርሱ ራሳቸው ስጋት ላይ ናቸው። ጣልያን ሰሞኑን ኢማሙን ከሀገራ ያባረረችው እዚያው ጣልያን ሆኖ ጅሀድ ስላወጀባት ነው። እንግሊዝ ተበብራለች፣ አሜሪካ ኒውዮርክ እየሆነ ያለውን መታዘብ ነው። 

"…ነገርኩህ መጽሐፍ ቅዱስም የሚለው "ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" መዝ 68፥ 31 እንጂ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ አሜሪካ፣ አውሮጳና፣ ራሺያ፣ ቱርክና ቻይና አይልም። ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ከውስጥ የተነሣን አራጅም ሆነ ከውጭ የመጣባትን ወራሪ ያደባየችው እጆቿን ወደ ሰማይ ወደ እግዚአብሔር ዘርግታ ነው። ዓድዋ እንዴት እንደዘመተች፣ ማንን ይዛ እንደዘመተችም ጠይቅ።

"እናቴን አምጡ" የሕፃኑ ታምራት አውግቸው ተማፅኖ።

እናትና  አባት  ከተጋቡ  ወደ  አስር  ዓመት   ገደማ  እንዳስቆጠሩ   የቅርቦቻቸው  ይናገራሉ።  
እነሆ በረከት ከሕፃን ታምራት!


ኑሯቸው  በምሥራቅ አርሲ  ዞን  በጉና  ወረዳ ኖኖ  ጃዌ  ቀበሌ  ነውና  እንደ  ሀገር  እና አካበቢ ማኅበረሰብ  ሁሉ  የዕለት  ጉርስ  የዓመት  ቀለብ  የሚያገኙት  ደረቁን  መሬት  አለስልሰው  ፣  ከብቶች  አርብተው  ባገኙት  ጥሪት  ነው። የሕጻን ታምራት  አውጋቸው  ወላጆች።

የዚህ  ብላቴና  ቤተሰቦች  በክርስትና  ሕይወታቸውም  ቢሆን ቤተክርስቲያንን  ሳይሱሙና  የፈጠራቸውን  ሳይማልዱ  ውለው  አያድሩም።  እንደ  ቅድስት  ቤተክርስቲያን  አስተምህሮ  መጾም  ፣ መጸለይና ማስቀደስ ግዴታ  መሆኑን በተግባር  መፈፀማቸውንም  መረጃውን  ከነገሩን  ከቅርቦቻቸው  ሰምተናል።

የታምራት  ቤተሰቦች  በቀያቸው  በነበሩበት  ወቅት  በትዳር  አንድ  ወንድና  አንድ  ሴት  ልጅ  አፍርተዋል ።

አበው  እንደሚሉት  የቀንም  ጎዶሎ  አለና  በምሥራቅ አርሲ  ዞን  በጉና  ወረዳ  ኖኖ  ጃዌ  ቀበሌ   በሚገኘው  የመኖሪያ   ቀያቸው  ሐሙስ  ጥቅምት   13 ቀን  2018  ዓ.ም  ለ14  አጥቢያ  ሀገር  ሰላም  ቀየው  አማን  ብለው  በተኙበት  ሰዓትን  ቆጥሮ  ለመግደል  የሚፋጠን  እግርና  እጅ  ከለሊቱ   6:00  ላይ  ወደ  ኦርቶዶክሳዉያኑ  ቤት አመራ።

በመላው ዓለም የምንገኝ ኢትዮጵያውያን ኦርቶዶክሳውያን፤ ሙስሊም፣ ፕሮቴስታንት፣ እና ካቶሊካውያን በእምነትም ያለእምነትም የምትኖሩ በሙሉ ኢትዮጵያውያን

የተወደዳችሁ የኢትዮጵያ ልጆች ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች፣ ፕሬቶስታንቶች፣ ካቶሊኮች፣ እንዲሁም እምነት ያላችሁ ወይም የሌላችሁ፤ ሁላችንንም አንድ የምታደርገን ሃገራችን ኢትዮጵያ በእጅጉ ሕመም ላይ ነች፤ ህመሟንም ሁላችንም ሳንረዳ አንቀርም እናውቀዋለን፤ እንረዳዋለን፤ ዛሬ በኢትዮጵያ የብዙ ኢትዮጵያውያን ደም በእብሪተኛው ዓብይ አሕመድ ጦር፣ በአክራሪ እስላማውያን፣ አክራሪ የሃይማኖት ሰዎች ብዙ ኢትዮጵያውያን በሚያውቁትም በማያውቁትም ክቡር ሕይወታቸው እየተቀጠፈ ይገኛል፤ ይሄንን ዜና ለማንችንም ዜና እንዳልሆነ እንረዳለን፤ ነገር ግን ማንኛውምይ የሃይማኖት ተቋም ይሄንን ግድያ እና ደም መፍሰስ በጎን ቁጭ ብለን ከመታዘብ ባሻገር ለማስቆም ወይም ለማስታገስ ጥረት ስናደርግ አንታይም፤ 

ባለፈው ሳምንት የእስምና መሪዎች አንድ መግለጫ አውጥተው ተመልክተናል፤ ነገር ግን ለበጣ በሚመስል መልኩ የእስልምና እምነት ተከታዮችም ተገድለዋል እና የእነሱንም ነፍስ ይማር በሚል ጩኸቴን ቀሙኝ በሚመስል መልኩ ሞታችንን ሲያቃልሉ ተመልክተናል ይሄ አያቀባብረንም፤ ኢትዮጵያ ለሁላችንም የምትበቃ ሃገር ሆና ሳለ አሁን በአሩሲ ያሉ ጂሃዲስት እጅግ በሚዘገንን መልኩ የክርስቲያኖችን ሕይወት ዘወትር ሲቀጥፉ እየታዩ ነው፤ ፦

A Cry for Justice: The Ongoing Massacre of Orthodox Christians in Oromia

The bloodshed in Eastern Arsi, Oromia, Ethiopia has not stopped — it grows worse each day. After the horrific slaughter of 25 Orthodox Christians in October 2025, the killing continues unchecked. The most vulnerable 
children, women, and the elderly are paying the highest price.

Little Tamrat, just four years old, was shot three times. Doctors now must amputate his leg to save his life. Sentayehu, only eight, still lies in a hospital bed after surviving both gunfire and a vicious machete blow to the head. Families are fleeing in terror, leaving behind their homes, churches, and memories.

On November 3, 2025,  six more innocent lives were taken in Abomsa Village. Yet the Zone Administrator, Ibrahim Kedir, denied the massacre in an interview with BBC Amharic — denying the pain, the bodies, the truth.

"አታልቅሽ ተመልሰው መጥተው ይገሉሻል..."የእናት ማሳሰቢያ ***


እንደ ህልም በእዛች በተረገመች ምሽት የተደረገውን አሰቃቂ ግድያ ታስታውሰዋለች። 

3 ወንድም እህቶቿን ፣እናቷን እና ሌሎች ቤተሰቦችን ጭምር ይዘው ከእነከብታቸው ስም አልባ የሞት አበጋዝ የሆኑ ታጣቂዎች
ልጇን የምትቀብር እናት እንዴት ትዘን?

ነድቷቸው ከአንድ ጫካ ላይ ወስደው አሳረፏቸው። 

ከመኖርያ ቤታቸው አርቀው ጫካ ላይ ከወሰዱ በኃላ  ሁሉም እንዲንበረከኩ አደረጉ። በያዙት መሣርያ ያለርህራሄ አርከፈኩባቸው ።ከተስማው የመሣርያ ጥይት ድምጽ በኃላ ሁሉም ጸጥ አሉ።

ከጸጥታው ውስጥ ግን የሚጣጣር እና የሚያቃስት ሰው ድምጽ በትንሽ በትንሹ ይሰማል። እንደ ቤተሰቧ ይህቺ የ8 ዓመት ህጻን በትከሻዋ አከባቢ እና በጎድኗ በኩል ሁለት ጥይት በስቷት አለፈ። 

በአፈሙዝ ያልሞቱትን በገጀራ ለመጨረስ ሁሉንም መከታተፍ ጀመሩ። ይህችንም ህጻን ልጅ መሃል አናቷን ሰነጠቁ። በጎድኗ እና ትከሻዋ በኩል ዘልቆ ከገባው የመሣርያ ቀለሀ በተጨማሪ ሰይፍ ለእዚህች ህጻን በአናቷ ታዘዘላት። 

ይህን ድርጊት ከፈጸሙ በኃላ ታጣቂዎች ከስፍራው ሄዱ።ይህች ህጻን ግን ከትንሽ ደቂቃ በኃላ ገላዋ በደም ረስርሶ ነቃች። ባልጠነከረ የስምንት ዓመት ገላዋ ላይ የገባው ቀለሃ እና ሰይፍ ድምጽ አውጥታ አስለቀሳት። 

Tuesday, November 4, 2025

ዛሬም በአርሲ ሌላ እልቂት ሌላ ግድያ 5 ክርስቲያኖች ታረዱ

 በትላንትናው እለት በክርስቲያኖች ደም በጨቀየችው በደም ምድሯ አርሲ ሌሎች አምስት ክርስቲያኖች ተጨፍጭፈዋል፤ የሚሰማም
ሲኖዶስ እና የንፁሐን ግድያ

መንግሥት የለም፤ የሚናገር አባትም የለም፤ የእምነቱ ተከታዮች እንኳን በትንሹ እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው በአሁን ጊዜ፤ ነገር ግን ከቤተ መንግሥቱም ሆነ ከቤተ ክህነቱ በኩል ምንም አይነት ነገር እንዳልተፈጠረ በሰላም እና በመረጋጋት ላይ ናቸው ፤ ይሄ ደግሞ ለአንድ ሃገር ሰላምዊ የሆነ የሕዝቦች የኑሮ እና የቀን ተቀን ማኅበራዊ መስተጋብር ጭምር በእጅጉ ፈታኝ የሆነ ሁኔታ ተፈጥሮ እያለ ፤ ነገር ግን መንግሥታችንም ሆነ የቤተ ክህነቱ ተጠሪዎች የዶሮ ነፍስ እንኳን የጠፋ በማይመስል መልኩ ዝምታቸውን ቀጥለዋል፤ ክርስቲያኖችስ በዚህ መጠን እየተጨፈጨፉ ዝምታን መምረጥ ነገ ክርስቲያኖች አባቶቻችን ብለው ሊነሱ ወይም አብረዋቸው ሊቆሙ የሚችሉበት ሁኔታ ይኖራል? ግብረ መልሱ በእጅጉ አስደንጋጭ እና አስፈሪ እንደሚሆን ከወዲሁ መገመት አያዳግትም፤ 
የራሳችን የሚባሉ አብቶች ቢያንስ እኳን ዘለላ እንባ ማፍሰስ ቢያቅታቸው ወጥተው ማጽናናት ማንን ገደለ? ተነስተው ግደሉ እንዲሉ አንጠብቅም ነገር ግን በጸሎታቸው በአደባባይ ወጥተው ይሄ ግድያ ወደአልተፈለገ ነገር ውስጥ እንዳይወስደን በማለት ለምን አልተናገሩም፤ የነገው ሁኔታ በእጅጉ ያሳስባል አሁን ላይ እየሆነ ያለው ፤ እርግጥ ነው እያንዳንዱ ግድያ እና ጭፍጨፋ በመንግሥት በሚሰጡ መመሪያዎች እንደሆነ ብዙ ነገሮች ግልጽ እየሆኑ ነው፤ የሕዝበ ክርስቲያኑ ምላሽ ቆይቶ ጥሩ ላይሆን እንደሚችል የተገነዘቡት አልመሰለንም፤ ይሆነ ሆኖ ነገን የምናየው ነው፤ ነገር ግን ዛሬ ላይ እያለቅን ነው ብለን እንኳን እንድንጮች ጥሪያችንን እናቀባለን።

Monday, November 3, 2025

An Urgent Appeal for the Orthodox Christians of the East Arsi Zone, Oromia, Ethiopia

=========

Your Excellencies, Distinguished Leaders, Human Rights Organizations, and People of Goodwill,

Priest Ephream Eshete Ephream

I, a priest of the Ethiopian Orthodox Tewahido Church, pleading on behalf of the beleaguered Orthodox Christian community in the East Arsi Zone of the Oromia Regional State in Ethiopia, write to you today with a heavy heart and a desperate plea for intervention. We are facing a systematic and brutal campaign of persecution that threatens our very existence, and our cries for help within our own country have gone unheeded.

The situation on the ground is not merely one of isolated incidents but a coordinated campaign of violence and terror. The most harrowing evidence of this is the chilling statistic that, on average, at least seven or eight of our faithful are killed in the region daily. These are not casualties of a generalized conflict; they are targeted assassinations, extrajudicial killings, and massacres aimed at cleansing the land of its ancient Orthodox Christian presence.

በመላው ዓለም የምንገኝ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ዘመቻውን እንድትቀላቀሉ በአክብሮት እንጠይቃለን!!


Crime Against Humanity led by Ethiopian Government Officials on Ethiopian Orthodox Christians.

https://www.aljazeera.com/wp-content/uploads/2023/02/2023-02-10T110825Z_1360883397_RC2HTY9LM5UG_RTRMADP_3_ETHIOPIA-CHURCH.jpg?resize=1920%2C1440
The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) is one of the oldest Christian institutions in the world, tracing its roots back to the early centuries of Christianity in Ethiopia and the Axumite Kingdom. It is a defining cultural and religious institution in Ethiopia: in addition to its spiritual role, it has historically been a central part of the country’s language, art, calendar, and identity.

Key features and significance

  • The EOTC holds a very large following: while exact percentages vary, it is reported to be the largest Christian church in Ethiopia. Ethiopia Insight+1

የማኅበራዊ ዘመቻው መካተት ያለባቸው ሐሳቦች 

፩. በኦርቶዶክሳውያን ላይ የጥቃት አድራሹ አካል ከመንግሥት ጋር በመናበብ የሚሠራው ጠቅላይ ቤተ ክህነት እና  ሲኖዶስ ስለሆነ 
ለችግራችን ምንጭ አድርጎ በመቁጠር ድምጽ ማሰማት። 

፪. የጠቅላይ ቤተ ክህነት ወይም ቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ ጉዳቱ ወደ ደረሰበት አካባቢ በመሄድ ወገኖቻችንን እንዲጎበኝና እንዲያጽናና መጠየቅ።

Calling the World Christian Society for help



A Call to Nations and the Oriental Orthodox Church

Stand With Persecuted Orthodox Christians  In Ethiopia

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

ዓለም  የዘነጋዉ  የ ኦርቶዶክሳዉያን  ጭፍጨፋ

በምሥራቅ አርሲ ሽርካ ወረዳ ላይ ከመስከረም 2/2016ዓ.ም እስከ ኅዳር 20/2017 ብቻ (ከዚያ በኋላ የተገደሉትን አያካትትም)

የተገደሉ ኦርቶዶክሳውያን  ስም ዝርዝር ።ለጊዜው የደረሰኝ መረጃ የነዚህ ብቻ ነው።የሌሎችም ሲደርሰኝ የማቀርብ ይሆናል።                 

ሀ)ጥቃቱን ከሌሎች ስፍራ ልዩ የሚያደርገው ሙሉ በሙሉ የኢኦተቤ አማኞች ላይ ያነጣጠረ ነው።ለምሳሌ በሌሎች የኦሮሚያ ክፍሎች አማራ የሆነ ሙስሊሙም ኦርቶዶክሱም ይገደላል  ከዚህ ግን ኦርቶዶክስን ለይቶ  ማጥፋት ነው እየተደረገ ያለው።

ለ) ጥቃቱን የሚፈጽሙት 100% የኦሮሞ አክራሪ የእስልምና እምነት ተከታዮች ናቸው ።

ሐ) ከተገደሉት መካከል 45% የሚሆኑት  ከ2 እስከ 11 የሚደርሱ ቤተሰቦቻቸው ጋር  የተገደሉት ናቸው። 

Saturday, November 1, 2025

ገዳዮቻችን መቼ ይታወቁ ይሆን?

Who is killing us?
በታቀደና በስልት ኦርቶዶክሳውያንን እያጸዳ ያለው አክራሪው ክንፍ ተደጋጋሚ ተግባር እየፈጸመ ‹‹በማይታወቁ ታጣቂዎች›› የሚል ዘገባ ተደጋግሞ ሲነገር ስንሰማ ጥያቄ እናነሳለን መቼ  ነው ‹‹ገዳዮቻችን የሚታወቁት››?  የሚለው የሚመለከታችሁ የቤተ ክህነትና
የቤተ መንግሥት ሹሞች ምላሽ የምንጠይቀው፡፡ 

👉ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በሚል የተዘገቡ የቤተ ክርስቲያን ዘገባዎችን እንደ ማሳያ እንመልከት፡፡
በኦሮሚያ ክልል ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ቤተክርስቲያንን እና ምዕመናንን ዒላማ ያደረጉ ጥቃቶችን በተመለከተ የተለያዩ የዜና እና የቤተክርስቲያን ምንጮች ዘገባዎች አውጥተዋል። ዋና ዋናዎቹ ዘገባዎች እና የሚመለከቷቸው አካባቢዎች የሚከተሉት ናቸው፡ 


ከጥምረት ለቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ ኦርቶዶክሳዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ

ከጥምረት ለቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ ኦርቶዶክሳዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ
“ስለ አንተ ዘወትር ይገድሉናል፤ እንደሚታረዱ በጎችም ሆነናል።” ሮሜ ፰ ÷ ፴፮

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታቀደና በተጠና መልኩ ከሃገር ለማጥፋት ካልሆነም አናሳ ሆና እንድትቀጥል

ሥርዓታዊ ጥቃት እየደረሰባት ትገኛለች። በተለይም ከ ፳፻፲ ዓ.ም. ጀምሮ ከሰሜን አስከ ደቡብ፤ ከምዕራብ እስከ ምሥራቅ በአራቱም መዓዘን ካህናቱ ምእመናኑ ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ አብያተ ክርስቲያናት ይቃጠላሉ። “ኦርቶዶክስን ከኦሮሚያ ማጽዳት” የሚለው የቆየ የመንግሥት እቅድ የመተግበር አካል ነው።
ሰሞኑን ጥቅምት ፲፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሥር ባሉ የተለያዩ አካባቢዎች “ማንነታቸው ያልታወቁ” በሚባሉ ነገር ግን አገዛዙ እና ሌሎች አጽራረ ቤተ ክርስቲያን ኃይላት በሚያሰማሯቸው ታጣቂዎች ሃያ አምስት ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች መገደላቸውን እና ከሞት የተረፉትም ለከባድ የአካል ጉዳት መዳረጋቸውን በተለያዩ ሚዲያዎች መዘገቡ ይታወቃል።
በእነዚህ ጥቃቶች የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ወንድማማቾች እና እህታማቾች እንዲሁም ከሁለት ዓመት ሕፃን እስከ ሰባ ስድስት ዓመት አረጋዊ ሽማግሌ የግፍ ግድያው ሰለባ መሆናቸው ታውቋል። በያዝነው ዓመት መስከረም ፯፣ ጥቅምት ፲፬፣ እና ጥቅምት ፲፰ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በጉናና መርቲ ወረዳዎች፤ በሸርካ ወረዳ፤ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ከሃያ አምስት በላይ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ተገድለዋል። በዚሁ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሽርካ ወረዳ ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ ፻፲፭ (አንድ መቶ አራ አምስት) ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል። ከአሥራ ስድስት በላይ አብያተ ክርስቲያናት ተዘግተዋል።

What would the world say about Arsi mass killing on Orthodox Christians?

Here is a summary report of publicly-documented information regarding attacks on Christians — especially members of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) — in the Arsi Zone (Oromia Region,


Ethiopia). Please note that there are serious gaps, conflicting claims, limited independent verification, and some of the details you asked about (e.g., “mutilated, stoned, burned alive inside the church”, perpetration by a named individual “Mr. Ibrahim Kadir”, a figure labelled “government-led Muslim fanatics”, exact counts like 1,850 victims) do not appear in credible independent sources. Hence, the account that follows is carefully qualified.

በአርሲ ዞን ለደረሰው ጭፍጨፋ እነዚህ ሃገረ ስብከቶች የሃዘን እና የአጋርነት መግለጫዎችን ልከዋል

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሁለት ወረዳዎች በታጣቂዎች ከተገደሉት ምዕመናን መካከል አምስቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት እንደሆኑና
ጥቂቅ ሃገረ ስብከቶች ሃዘናቸውን እና ከአርሲ ክርስቲያኖች ጋር ቆመዋል


ከዚህ ቀደምም በጀጁ ወረዳ በታጣቂዎች የታገቱ ሰዎች እንዳልተመለሱ የዞኑ ሀገረ ስብከት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ምሽት ገልጿል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሀገረ ስብከት በሰጠን ቃል፣ በሰሞንኛው ጥቃት መርቲ እና ጉና ወይም አባጀማ በተሰኙት ሁለት ወረዳዎች ላይ የሟቾች ቀብር መፈጸሙን ገልጿል። 


የኖላዊው አባት ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ አርአያነት ያለው ሥራ በምሥራቅ አርሲ

የብፁዕ አቡነ ይስሐቅ አርአያነት ያለው ተግባር
=========
ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ  በአርሲ ሀገረ ስብከት በኖኖ ጃዊ ቀበሌ  ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ከተገደሉት ውስጥ በእግዚአብሔር
የኖላዊው አባት ብፁዕ አቡነ ይሥሐቅ አርአያነት ያለው ሥራ

ቸርነት ለተረፈው ሕፃን 70,000 ብር የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ ።

(EOTCMK TV ጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም)

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ከሰሙበት ጊዜ ጀምሮ እጅግ ማዘናቸውን እና ለሞቱት እረፍተ መንግሥተ ሰማያት፤ ቤተሰባቸውን ላጡ መጽናናትን እንዲሰጥ ተመኝተዋል ።


ብፁዕነታቸው የሰው ልጅ ሰው ሆኖ ከመኖር ይልቅ አውሬ እየሆነ ያስቸገረበት ዘመን ላይ መድረሳችን እጅግ የሚያሳዝን ነው ብለዋል። 





ከሻሸመኔ እስከ አርሲ ጭፍጭፋ ተጠያቂው ሰው አቶ ኢብራሂም ከድር ለፍርድ መቅረብ አለበት

ግፉዓን ይትመሐፀንዋ ለመንግስተ ሰማያት 😭😭😭
ገዳይም አስገዳይም ኢብራሂም ከድር ነው
አቶ ኢብራሂም ከድር ለፍድ ይቅረብ
በመጀመሪያ በግፍ ለተገደሉ ወገኖቻችን ነፍስ ይማር እንላለን 🤔
ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን እንመኛለን 😭
ነገሩ የትናንቱ እንደ አዲስ መሰለን እንጂ ስንቱ ነው በሰማይ በድሮን 
በታች በምድር በታንክ 
በዲሽቃ እየተጨፈጨፈ ያለው?
እየተፈናቀለ ያለው ማነው ብለን ከጠየቅን መንግሥት ነው፤
መንግሥት ሲባል ደግሞ በስም ዝርዝር 
በሻሸመኔ ከተፈጸመው ጭፍጨፋ እስከ አርሲ በተደረጉት ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያኖችን ከማጽዳት ጋር በተያያዘ ብዙ ሰዎች ስማቸው ሲነሳ
ቆይቷል በተለይ በአሁን ሰዓት በአርሲ በተፈጸመው ጭፍጭፋ ክርስቲያኖችን የማጽዳቱን ሥራ በዋናነት ከሚመሩት ሰዎች ሥምሪት ከሚሰጡት ስዎች ግንባር ቀደሙ አቶ ኢብራሂም ከድር ዋነኛው ነው፤