Monday, November 3, 2025

የማኅበራዊ ዘመቻው መካተት ያለባቸው ሐሳቦች 

፩. በኦርቶዶክሳውያን ላይ የጥቃት አድራሹ አካል ከመንግሥት ጋር በመናበብ የሚሠራው ጠቅላይ ቤተ ክህነት እና  ሲኖዶስ ስለሆነ 
ለችግራችን ምንጭ አድርጎ በመቁጠር ድምጽ ማሰማት። 

፪. የጠቅላይ ቤተ ክህነት ወይም ቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ ጉዳቱ ወደ ደረሰበት አካባቢ በመሄድ ወገኖቻችንን እንዲጎበኝና እንዲያጽናና መጠየቅ።

Calling the World Christian Society for help



A Call to Nations and the Oriental Orthodox Church

Stand With Persecuted Orthodox Christians  In Ethiopia

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

ዓለም  የዘነጋዉ  የ ኦርቶዶክሳዉያን  ጭፍጨፋ

በምሥራቅ አርሲ ሽርካ ወረዳ ላይ ከመስከረም 2/2016ዓ.ም እስከ ኅዳር 20/2017 ብቻ (ከዚያ በኋላ የተገደሉትን አያካትትም)

የተገደሉ ኦርቶዶክሳውያን  ስም ዝርዝር ።ለጊዜው የደረሰኝ መረጃ የነዚህ ብቻ ነው።የሌሎችም ሲደርሰኝ የማቀርብ ይሆናል።                 

ሀ)ጥቃቱን ከሌሎች ስፍራ ልዩ የሚያደርገው ሙሉ በሙሉ የኢኦተቤ አማኞች ላይ ያነጣጠረ ነው።ለምሳሌ በሌሎች የኦሮሚያ ክፍሎች አማራ የሆነ ሙስሊሙም ኦርቶዶክሱም ይገደላል  ከዚህ ግን ኦርቶዶክስን ለይቶ  ማጥፋት ነው እየተደረገ ያለው።

ለ) ጥቃቱን የሚፈጽሙት 100% የኦሮሞ አክራሪ የእስልምና እምነት ተከታዮች ናቸው ።

ሐ) ከተገደሉት መካከል 45% የሚሆኑት  ከ2 እስከ 11 የሚደርሱ ቤተሰቦቻቸው ጋር  የተገደሉት ናቸው። 

Saturday, November 1, 2025

ገዳዮቻችን መቼ ይታወቁ ይሆን?

Who is killing us?
በታቀደና በስልት ኦርቶዶክሳውያንን እያጸዳ ያለው አክራሪው ክንፍ ተደጋጋሚ ተግባር እየፈጸመ ‹‹በማይታወቁ ታጣቂዎች›› የሚል ዘገባ ተደጋግሞ ሲነገር ስንሰማ ጥያቄ እናነሳለን መቼ  ነው ‹‹ገዳዮቻችን የሚታወቁት››?  የሚለው የሚመለከታችሁ የቤተ ክህነትና
የቤተ መንግሥት ሹሞች ምላሽ የምንጠይቀው፡፡ 

👉ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በሚል የተዘገቡ የቤተ ክርስቲያን ዘገባዎችን እንደ ማሳያ እንመልከት፡፡
በኦሮሚያ ክልል ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ቤተክርስቲያንን እና ምዕመናንን ዒላማ ያደረጉ ጥቃቶችን በተመለከተ የተለያዩ የዜና እና የቤተክርስቲያን ምንጮች ዘገባዎች አውጥተዋል። ዋና ዋናዎቹ ዘገባዎች እና የሚመለከቷቸው አካባቢዎች የሚከተሉት ናቸው፡ 


ከጥምረት ለቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ ኦርቶዶክሳዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ

ከጥምረት ለቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ ኦርቶዶክሳዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ
“ስለ አንተ ዘወትር ይገድሉናል፤ እንደሚታረዱ በጎችም ሆነናል።” ሮሜ ፰ ÷ ፴፮

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታቀደና በተጠና መልኩ ከሃገር ለማጥፋት ካልሆነም አናሳ ሆና እንድትቀጥል

ሥርዓታዊ ጥቃት እየደረሰባት ትገኛለች። በተለይም ከ ፳፻፲ ዓ.ም. ጀምሮ ከሰሜን አስከ ደቡብ፤ ከምዕራብ እስከ ምሥራቅ በአራቱም መዓዘን ካህናቱ ምእመናኑ ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ አብያተ ክርስቲያናት ይቃጠላሉ። “ኦርቶዶክስን ከኦሮሚያ ማጽዳት” የሚለው የቆየ የመንግሥት እቅድ የመተግበር አካል ነው።
ሰሞኑን ጥቅምት ፲፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሥር ባሉ የተለያዩ አካባቢዎች “ማንነታቸው ያልታወቁ” በሚባሉ ነገር ግን አገዛዙ እና ሌሎች አጽራረ ቤተ ክርስቲያን ኃይላት በሚያሰማሯቸው ታጣቂዎች ሃያ አምስት ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች መገደላቸውን እና ከሞት የተረፉትም ለከባድ የአካል ጉዳት መዳረጋቸውን በተለያዩ ሚዲያዎች መዘገቡ ይታወቃል።
በእነዚህ ጥቃቶች የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ወንድማማቾች እና እህታማቾች እንዲሁም ከሁለት ዓመት ሕፃን እስከ ሰባ ስድስት ዓመት አረጋዊ ሽማግሌ የግፍ ግድያው ሰለባ መሆናቸው ታውቋል። በያዝነው ዓመት መስከረም ፯፣ ጥቅምት ፲፬፣ እና ጥቅምት ፲፰ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በጉናና መርቲ ወረዳዎች፤ በሸርካ ወረዳ፤ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ከሃያ አምስት በላይ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ተገድለዋል። በዚሁ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሽርካ ወረዳ ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ ፻፲፭ (አንድ መቶ አራ አምስት) ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል። ከአሥራ ስድስት በላይ አብያተ ክርስቲያናት ተዘግተዋል።

What would the world say about Arsi mass killing on Orthodox Christians?

Here is a summary report of publicly-documented information regarding attacks on Christians — especially members of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) — in the Arsi Zone (Oromia Region,


Ethiopia). Please note that there are serious gaps, conflicting claims, limited independent verification, and some of the details you asked about (e.g., “mutilated, stoned, burned alive inside the church”, perpetration by a named individual “Mr. Ibrahim Kadir”, a figure labelled “government-led Muslim fanatics”, exact counts like 1,850 victims) do not appear in credible independent sources. Hence, the account that follows is carefully qualified.

በአርሲ ዞን ለደረሰው ጭፍጨፋ እነዚህ ሃገረ ስብከቶች የሃዘን እና የአጋርነት መግለጫዎችን ልከዋል

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሁለት ወረዳዎች በታጣቂዎች ከተገደሉት ምዕመናን መካከል አምስቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት እንደሆኑና
ጥቂቅ ሃገረ ስብከቶች ሃዘናቸውን እና ከአርሲ ክርስቲያኖች ጋር ቆመዋል


ከዚህ ቀደምም በጀጁ ወረዳ በታጣቂዎች የታገቱ ሰዎች እንዳልተመለሱ የዞኑ ሀገረ ስብከት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ምሽት ገልጿል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሀገረ ስብከት በሰጠን ቃል፣ በሰሞንኛው ጥቃት መርቲ እና ጉና ወይም አባጀማ በተሰኙት ሁለት ወረዳዎች ላይ የሟቾች ቀብር መፈጸሙን ገልጿል። 


የኖላዊው አባት ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ አርአያነት ያለው ሥራ በምሥራቅ አርሲ

የብፁዕ አቡነ ይስሐቅ አርአያነት ያለው ተግባር
=========
ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ  በአርሲ ሀገረ ስብከት በኖኖ ጃዊ ቀበሌ  ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ከተገደሉት ውስጥ በእግዚአብሔር
የኖላዊው አባት ብፁዕ አቡነ ይሥሐቅ አርአያነት ያለው ሥራ

ቸርነት ለተረፈው ሕፃን 70,000 ብር የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ ።

(EOTCMK TV ጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም)

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ከሰሙበት ጊዜ ጀምሮ እጅግ ማዘናቸውን እና ለሞቱት እረፍተ መንግሥተ ሰማያት፤ ቤተሰባቸውን ላጡ መጽናናትን እንዲሰጥ ተመኝተዋል ።


ብፁዕነታቸው የሰው ልጅ ሰው ሆኖ ከመኖር ይልቅ አውሬ እየሆነ ያስቸገረበት ዘመን ላይ መድረሳችን እጅግ የሚያሳዝን ነው ብለዋል። 





ከሻሸመኔ እስከ አርሲ ጭፍጭፋ ተጠያቂው ሰው አቶ ኢብራሂም ከድር ለፍርድ መቅረብ አለበት

ግፉዓን ይትመሐፀንዋ ለመንግስተ ሰማያት 😭😭😭
ገዳይም አስገዳይም ኢብራሂም ከድር ነው
አቶ ኢብራሂም ከድር ለፍድ ይቅረብ
በመጀመሪያ በግፍ ለተገደሉ ወገኖቻችን ነፍስ ይማር እንላለን 🤔
ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን እንመኛለን 😭
ነገሩ የትናንቱ እንደ አዲስ መሰለን እንጂ ስንቱ ነው በሰማይ በድሮን 
በታች በምድር በታንክ 
በዲሽቃ እየተጨፈጨፈ ያለው?
እየተፈናቀለ ያለው ማነው ብለን ከጠየቅን መንግሥት ነው፤
መንግሥት ሲባል ደግሞ በስም ዝርዝር 
በሻሸመኔ ከተፈጸመው ጭፍጨፋ እስከ አርሲ በተደረጉት ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያኖችን ከማጽዳት ጋር በተያያዘ ብዙ ሰዎች ስማቸው ሲነሳ
ቆይቷል በተለይ በአሁን ሰዓት በአርሲ በተፈጸመው ጭፍጭፋ ክርስቲያኖችን የማጽዳቱን ሥራ በዋናነት ከሚመሩት ሰዎች ሥምሪት ከሚሰጡት ስዎች ግንባር ቀደሙ አቶ ኢብራሂም ከድር ዋነኛው ነው፤ 

Friday, October 31, 2025

በአርሲ የእልቂት ድግሱ እንደቀጠለ ነው፤ ለማን አቤት ይባል???

አርሲ በኦርቶክስት ደም ታጥባለች ፤ 

በምሥራቅ  አርሲ  ሽርካ  ወረዳ ሄላ  ዘባባ ቀበሌ  ከሚኖሩ ኦርቶዶክሳዊያን ሦስቱ መገደላቸው እና አራቱ መታገታቸው ተሰማ፡፡

በወረዳው ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ115 በላይ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውና ከ16 በላይ ዐብያተ ክርስቲያናት መዘጋታቸው ታውቋል።

ጥቅምት ፲፱/፳፻፲፰ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ 

ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን በደረሰው መረጃ ጥቅምት  17 ቀን 2018  ዓ.ም ከለሊቱ 4:00 ሰዓት አካባቢ በምሥራቅ አርሲ ሽርካ ወረዳ ሄላ ዘባባ ቀበሌ አርሴማ አጥቢያ የሚኖሩ ምእመናን በታጠቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ሦስቱ መገደላቸው እና አራቱ ደግሞ መታገታቸው ተገልጿል።

ከተገደሉት ምእመናን ውስጥ የአንዱ ሟች አባትና ወንድም መታገታቸው በመረጃው የተገለጸ ሲሆን ታፍነው የተወሰዱት ምእመናን ስለሚገኙበት  ሁኔታ አይታወቅም ተብሏል፡፡

በመረጃው እንደተነገረው የሞቱት ሦስቱ ኦርቶዶክሳውያን በትላንትናው ዕለት ጥቅምት 18  ቀን  2018  ዓ.ም  ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል፡፡

ላለፉት ሁለት ዓመታት ማለትም ከ2016 ዓ.ም መስከረም 02 ጀምሮ  እስከ  2017 ዓ.ም  ድረስ ያለማቋረጥ በወረዳው ከ115 በላይ ምእመናን የተገደሉ  ሲሆን  27  ኦርቶዶክሳዉያን  ደግሞ አሁንም  ድረስ  ታግተው  ያሉበት  እንደማይታወቅ  ነዋሪዎቹ  ለጣቢያችን  ገልጸዋል።

በግድያ  ያላበቃው  መከራና  ስቃይ  በሽርካ  ወረዳ  ብቻ  በዘጠኝ  ቀበሌዎች  በሺዎች የሚቆጠሩ  ኦርቶዶክሳዉያን  መፈናቀላቸውንም በመረጃው ተጠቅሷል፡፡

Thursday, October 30, 2025

አትነሳም ወይ፤ ኦርቶዶክሳዊ አይደልህም ወይ?

የመጣብንን የአላውያን ጦር በመስቀሉ እንሰብራለን፤
"አትነሳም ወይ? " 

አንተ የተዋሕዶ ልጅ ሆይ
ማንቀላፋቱ አይበቃም ሆይ!
መዘናጋቱስ አይበቃም  ወይ
አይገድህም ወይ!
አትነሳም ወይ
እያለቀ ያለው ወገንህ አይደለም ወይ!

ወገን ሲታረድ እንደ በግ ጠቦት
ደሙ ሲፈስ እንደ ውኃ ጅረት
አየነው አየነው እረፉ ባይ ጠፋ
ሞት ታውጆብን ከምድር እንድንጠፋ

       አየገባህም ወይ
        አትነሳም ወይ
       በግፍ የሚገደለው ሕዝብህ አይደለም ወይ

       መንግሥት አለ ብለህ እንዳትጃጃል
አባት አለ ብለህ እንዳትጃጃል
እግዚአብሔርን ይዘህ ተነስ ለ ትግል
ወደ ፊት ሩጥ እንጂ ወደ ኋላ አትበል

           አይበቃም ወይ
            አያሳዝንም ወይ
            አትነሳም ወይ
      በግፍ የሚታረደው
       ሕዝብህ አይደለም ወይ
ወገን በሃይማኖቱ በግፍ ሲገደል
ሬሳው እንኳ  ሳይቀር በእሳት ሲቃጠል
አያሳዝንም ወይ እየሆነ ያለው
ተነሳ ወጣት ሆይ  መፍትሔው 
መነሳት ነው

ሌላው አጀንዳ በራሱ ድምፃችንን የሚያጎላ ሳይሆን ድምፅ የሚቀንስ ነው!

የሚያሳዝነኝ ዛሬ መሞታችን ብቻ ሳይሆን ሞታችን እንዳይቀጥል አንድ አይነት ድምፅ ማውጣት አለመቻላችን ነው ሌሎች እንኳን ሲሞቱ ይቅርና ሲታመሙ እንኳን የሚያወጡት ድምፅ አንድ አይነት ነው እኛ በሞታችን ሳይቀር ዥንጉርጉር ነን ድምፃችንን አንድ አድርገን መኖር ይፈቀድልን ለምን እንገደላለን ከሚል ጩኸት ይልቅ ሞታችንን እንከፋፈልበታለን እነ እገሌ አብረውን አልቅሰዋል እነ እገሌ በደንብ አልጮሁም የእነ እገሌ አለመጮህ ወዘተ እያልን ድምፅ መቀነሳችን ልዩነት መፍጠራችን ወደ ፊት እንኳን ለገዳዮቻችን አንድ ሆነን እንደማንቆም እየነገርናቸው ነው😭😭 ኦርቶዶክስ ናቸው ተብለን እየተገደልን ሞታችን ውስጥ ብዙ ነገር መሥራታችን ሞታችንን በልዩ ልዩ ምንዛሬ ማየታችን እጅግ ያሳዝናል መግደል ባይደክማችሁ እንኳን መሞት ደክሞናል ይበቃል እንበል የተከፋፈለ ሐሳብና የግል አመለካከት ከመሰንዘር ወጥተን ሞታችንን እናስቁም ገዳዮቻችንን እናውግዝ ዝምተኞችን እንቀስቅስ ተናጋሪዎች ንግግራቸው ትክክለኛ ሐሳብ ላይ ያነጣጠረ እንዲሆን እንምከር ሞታችንን ለልዩ ልዩ ፍጆታ የሚጎትቱትን በወንድምና እህት በልጅ በእናትና አባት ሞት ገብያ አትክፈቱ እንበል ያ ካልሆነ በስተቀር ለጊዜው ተነቃቅፈን ተወጋግዘንና ተነቋቁረን ተመልሰን ደግሞ ዝም እንላለን ሞቱም መቀጠሉ አይቀርምና አንድ ሆነን እንቁም ሞታችን ውስጥ በመከራችን የምድጃ እሳት ላይ የግል ነገራችንን ለማብሰል የግል ድስት አንጣድ!😭

በምሥራቅ አርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በሚፈጸመው መንግሥት መር ኢስላማዊ ጅሃድ

ብፁዕ አቡነ ያሬድ የምሥራቅ አርሲ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ

በምሥራቅ አርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ  በሚፈጸመው  መንግሥት መር ኢስላማዊ ጅሃድ የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ክፍል ሠራተኞች እልቂቱ ወደ ተፈጸመበት ወረዳ ደውለው ከአንድ ኦርቶዶክሳዊ መረጃ ይቀበላሉ።መረጃ ሰጪው ኦርቶዶክሳውያን ያሉበት አሳሳቢ መሆኑንና የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አባ ያሬድም ለ ጉዳዩ ትኩረት አለመስጠታቸውን ይናገራሉ።ማኅበሩም ድምፁን በሚዲያው ያወጠዋል።ይኽን የሰሙት አቡን ያሬድ ቪድዮው ከሚዲያው  እንዲወርድ በማስፈራሪያ ጭምር አዘዙ። በ ሞቱ ኦርቶዶክሳውያን ሥርዐተ ቀብር ላይ የሚገኙ የሀገረ ሰብከቱ ሠራተኞች ላይም ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደርግም ቀጭን ትእዛዝ ወጥቷል።ይኽ ብቻ አይደለም ከዚህን በፊት "በሀገረ ስብከትዎ ስለሚሞቱት ኦርቶዶክሳውያን ለምን ዝምታን መረጡ "ሲባሉ "ኦርቶዶክሳውያን መሞታቸውን እርግጠኛ አይደለሁም" እስከ ማለት የደፈሩ ሰው ናቸው።እንግዲህ ቤተ ክርስቲያን በእንደነዚህ ዓይነት ሰዎች እጅ ላይ ነው የወደቀችው።#EOTC  የገዳያችንን የብልጽግና ገጽታ የሚገነባ ስለ ኮሪደር ልማት ካልሆነ በቀር ሙሉ በሙሉ ስለ ኦርቶዶክሳውያን እልቂት አይዘግብም።ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የአዳነች አቤቤ የቅርብ ሰው የሆኑት አባ ሄኖክsilent mood ላይ ቢያስገቡትም አልፎ አልፎም ቢሆን መከራችንን ይዘግባል።#Mktv  ገዳዮቻችንን  በስም እንዳይጠሩአቸው  "ያልታወቁ ኀይሎች" እያሉ እንዲዘግቡ  የሚያደርጉት የ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ  እሾኾች ናቸው።

Tuesday, October 28, 2025

ሁለተኛው አሳዛኝ የእልቂት ዜና





በአርሲ ሀገረ ስብከት በኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ። 

ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ] 

በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን መገዳላቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያሳያል። 

በደረሰን መረጃ መሠረት በቀበሌው የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን ከለሊቱ 6:00 ሰዓት አካባቢ በዕለተ ረቡዕ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ለ14 አጥቢያ  ከተኙበት ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሲሆን ስድስቱ ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፈት ቀድመው ታፍነው ተወስደው ነበር ተብሏል። 

የተገደሉት ምእመናን የዕድሜ ክልላቸው ከ2 ዓመት ጀምሮ እስከ 76 ዓመት አዛውንት እንደሚገኙበት መረጃው ይገልጻል። 

በተጨማሪም ሁለት ሰዎች በጥቃቱ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ለተሻለ ሕክምና ወደ አቦምሳ  ከተማ  ሪፈር  መሄዳቸውን በመረጃው ተያይዞ ተነግሯል፡፡ 

ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በቀበሌው ውስጥ የሚኖሩ 8 ኦርቶዶክሳውያን ሌሊት ላይ ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን በደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል።  

የተነሳው አወዛጋቢው ነገር ምንድነው? መፍትሔውስ ምን ሊሆን ይችላል ከኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

የምንሰውማ ጉድ ምንድነው? 

አዲስ የተገዛው የ8 ሚሊዮን የቅድስ ተ/ኃይማኖት ቤ/ክ አሜሪካ
በቨርጂኒያ ቅዱስ ተክለኃይማኖት ቤተክርስቲያን አጥቢያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከበድ ያለ ጭቅጭቅ እና ንትርክ የሚመስል ነገር ተነስቷል ፤ ከብዙ የብሎጎች እና የቴሌግራም ግሩፖች እንደተረዳነው፤ ይሄ ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረት ከአሥራ ሁለት ወይም ሦስት አመት በላይ በአገልግሎት እንደቆየ ይነገራል ፤ ነገር ግን ቦታው ከተገዛ ቅርብ ጊዜ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ ጣልቃ ገብነት በተለይ ከባሕርዳር ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ አብርሃም በቀጥታ ጣልቃ በመግባት በቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ እና በቤተክርስቲያኑ ምዕመናን ጋር የተነሳውን አለመግባባት ለማስማማት ሳይሆን ያልተፈጠረውን ታሪኩን በማጣመም ሌላ እንደሆነ አድርገው በማቅረብ በምዕመናኑ እና በቤተክስቲያኑ ምዕመናን መካከል ከፍተኛ አምባጓሮ አይነት መነሳቱን እና ፖሊስ ተጠርቶ እንደነበር የታሰሩ ምዕመናን እንዳሉ ግን የድረሰን መረጃ ባይኖርም፤ ፖሊሶች ግን በቦታው ላይ መጥተው ወደ ቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ገብተው እንደነበር መረጃዎች ደርሰውናል፤ በኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ ለመረዳት እንደቻልነው፤ የሚከተለውን መረጃ ለዚህ ሚዲያ ቤተሰቦች ለማድረስ ፤ ነው፤ 
በቀጣይነት ያሉትን እየተከታተልን እንዘግባለን፤ በዚህ አጥቢያ ያሉትንም ምዕመናን መረጃውን ብታደርሱን በሚዲያችን ለማስተናገድ እንደምንችል ከወዲሁ ለማስታወስ እንድወዳለን፤ 

📝የሚሰማው ምንድን ነው ? 

👉በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው  በቅርቡ ስምንት ሚሊዮን ዶላር (8Million $) ወጥቶበት  የተገዛው የምሥራቀ ጸሐይ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን  ቨርጅኒያ በመሀከላቸው ምንድን ነው የተፈጠረው ?

"ደብር ወገዳም"

ደብር ወገዳም 

 መልካም ቃላት የሚበዙት ክፉት ሲበዛ ነው። ሰው መልካም ሥራ ሲርቀው ክፋቱን ሊደብቅ ሲል መልካም ስም ማዕረግ ይደረድራል። መልካም ቃላት ጋጋታ ይጠቀማል። የዘንድሮን የመንፈስ እርቃንነት መቋቋም ያልቻለ ስው ግማሹ በስም ግማሹ ባሸበረቀ ካባና ቀሚስ እንደ ሞዴል በሚቀያየር አልባሳት ያጌጣል። 

ቀደም ባለው ጊዜ የቆየው ባሕል ሊቃውንት ብቻ የሚጠሩበት ሥም አለ። እንደየ ትምህርታቸው እንደ ደብሩ ትልቅነት የአለቃ ስም ይሰጣል። ዛሬ ግን ስም ያልወሰደ የለም። የማይንቆለጳጰስ የለም። 
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕርዳር እና የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስበከት ሊቀ ጳጳስ

ሰላም በሌለበት ደብር የመልአከ ሰላም አበዛዙ፣ የተማረው የተመገበው ሳይኖር የመጋቤ ሐዶስና ብሉይ አበዛዙ ግርም ይላል። 

መልአከ ከዋክብት፣ መልአከ ጨረቃ፣ መምህረ መምህራን፣ ርዕሰ ርዑሳን፣ ርዕሰ ባሕታውያን፣ ቆሞስ ሞቆሳት …..ሊቀ ሐዋርያት፣ መጋቤ ሰማእታት… ምኑ ቅጡ። አምፓል ለቀጠለ ኹሉ መልአከ ብርሃን። 

አቡነ አብርሃም ደግሞ ሰሞኑን አንዲት ስም አስተዋውቀዋል። ደብር ወገዳም የምትል። የዶላር ስም ናት መሰለኝ። መቼስ ለብር ቤተ ክርስቲያን እንዲኽ ያለ ስም አይወጣም። 

Wednesday, August 19, 2015

ልብ ያለው ልብ ይበል


ሰሞኑን በአንድ የፌስ ቡክ ግድግዳ ላይ ተለጥፎ ያየነው ነገር ዓይናችንን ስቦት ትንሽ ነበብ ስናደርገው እንዲህ ይላልኢየሱስ ሳያቆስል የማረካቸውይላል ዝርዝሩን ለመመልከት ጓጓን እና ወደ ውስጥ ገባ ብለን ማንበብ ቀጠልን እንዲህ ይላል
የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብርቅዬ ልጆች የወንጌል ዘማቾች ሰባኪያን ባንድ ዝርዝር ዘማርያን በሌላ ዝርዝር ተዘርዝረው ተመለከትን እንደእውነቱ ከሆነ ሰውየው ጥሩ መረጃዎችን ለኦርቶዶክሳውያኑ የሰጠን ይመስለናል ምክንያቱም ሰውየው ሲዘረዝር ዋናዋናዎቹን ብቻ ነበር የምናውቃቸውብርቅዬዎቹንማለታችን እንደሆነ እንዲሰመርልን እንፈልጋለን ነገር ግን አብዛኛው ኦርቶዶክሳዊ ጋሻ ጃግሬዎቹን ወይንም ተከታዮቹን እንደ ግንባረ ቀደሞቹ ለመሆን የሚጣጣሩን እታች ያሉትን እስከ ዛሬ አናውቃቸውም ነበር ነገር ግን ሰፋ የለ መረጃ ስለሰጠን ቃለ ሕይወትን ያሰማልን እያልን እነዚህን ዝርዝሮች ጎላ አድርገን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ምዕመናን ለማሳወቅ ወደድን በዚህም ይህንን ትንሽ ክታብ ጨምረን ለማቅረብ ተዘጋጀን እነሆ ጋበዝናችሁ ዝርዝሩን ይመልከቱን

Thursday, July 16, 2015

የስልጤ – ቂልጦ ቅድስት ማርያም አስተዳደር እና ምእመናን: ‹‹የድረሱልን ጥሪ››ው በድረ ገጽ መሰራጨቱ ‹‹ከፍላጎታችን ውጭ ነው፤ አውግዘነዋል›› አሉ


  • የሰበካ ጉባኤው እና የሕንፃ አሠሪ ኮሚቴው 6 አባላት የሐሰት ወሬ ማሰራጨት በሚል ተከሠዋል
  • ከ11-14 ቀናት እስር በኋላ በዋስ ቢወጡም ሊቀ መንበሩ የማርያም ወርቅ ተሻገር እንደታሰረ ነው
  • ‹‹ችግሩን ከሥሩ ለማድረቅ›› በቤተ ክህነት እና በመንግሥት አካላት ‹‹ጥረት እየተደረገ ነው››
  • የሰላም ጉባኤ በማካሔድ የቤተ ክርስቲያኑን ቅዳሴ ቤት ለማክበር መዘጋጀቱን ሀ/ስብከቱ አስታውቋል
*          *          *Silte01
  • ‹‹ድረሱልኝ ጥሪ››ው፣ የጥንቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተቃጥሏል መባሉ ያልተረጋገጠ ነው
  • የስልጤ ዞን የምሥራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ፤ ዜጎች በመግባባት እና በፍቅር የሚኖሩባት ናት፤ በጽሑፉ ሊቢያን እንደ ንጽጽር መጠቀማችን ተገቢ አልነበረም፤
  • የወረዳ፣ የዞን እና የክልል አመራሮች ከሀገረ ስብከቱ፣ ከወረዳ ቤተ ክህነቱ፣ ከሃይማኖት ፎረም እና ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር ችግሩን ከሥሩ ለማድረቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው፤
  • ‹‹ድረሱልኝ ጥሪ›› ከደብሩ ምእመናን፣ ከሰበካ ጉባኤው እና ከሕንፃ አሠሪ ኮሚቴው ዓላማ እና ፍላጎት ውጭ ሐራ ዘተዋሕዶ በተባለው ድረ ገጽ በመለቀቁ ድርጊቱን አውግዘነዋል፡፡

Tuesday, June 16, 2015

ሰበር ዜና - ከእዚህ በፊት በሰጣቸው ትምህርቶቹ በርካታ ጥያቄዎች የተነሱበት በጋሻው ደሳለኝ ሉንድ፣ስዊድን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሌላ ትልቅ ውዝግብ ፈጠረ።።''በጋሻው ስዊድን የገባው በአውሮፓ የምትገኘውን፣በሀገር ቤትም ሆነ በውጭ አባቶች የምትመራውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ለማወክ ያለመ ተልኮ ይዞ ነው'' አውሮፓ የሚኖሩ አባቶች እና ምዕመናን።(የደብዳቤ እና የፎቶ ቅጅዎች ተያይዘዋል)



           አቶ በጋሻው ዛሬም የውዝግብ ማዕከል ሆኗል
 


  • ወደ ሉንድ፣ስዊድን የገባበት ሰነድ በራሱ አወዛጋቢ ሆኗል፣
  • ሉንድ፣ስዊድን የሚገኘው ቴዎሎጂ ዩንቨርስቲ የግለሰቡን ወደ ስዊድን መምጣት እንደሚያውቅ ተደርጎ የተገለፀውን ደብዳቤ ሐሰት መሆኑ እየተነገረ ነው፣
  • ዩንቨርስቲው ስለጉዳዩ እንደማያውቅ ለማወቅ ተችሏል፣
  • በአውሮፓ የሚኖሩ በሀገር ቤትም ሆነ በውጭ አባቶች ስር የሚገኙ አጥብያ አብያተ ክርስቲያናት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የበጋሻውን አወዛጋቢ የሀገር ቤት ታሪክ የሚያውቁ አባቶች እና ምዕመናን በብርቱ እያስጠነቀቁ ነው፣
  •  ''ከሀገር ቤት አቡነ ማትያስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ እና ቋሚ ሲኖዶስ እንዳስተምራችሁ ፍቃድ ሰጥተውኛል'' በጋሻው ለሉንድ፣ስዊድን ምዕመናን የነገራቸው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በበርካታ የቤተክርስቲያኒቱ ጉባኤያት ላይ ሁከት በመፍጠር፣በአደባባይ የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶች በማጥላላት እና በአስተማራቸው ትምህርቶች አፅራረ ቤተ ክርስቲያን ይዘት ከሐዋሳ እስከ ጎንደር ከአዲስ አበባ እስከ ሐረር ባሉ አያሌ አጥብያ አብያተ ክርስቲያናት በሚገኙ  አባቶች ከመድረክ ላይ እንዳያስተምር በሀገረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት፣የደብር አለቆች እና ምዕመናን የታገደው በጋሻው ደሳለኝ ስዊድን፣ሉንድ አንድ ሰንበት በተጭበረበረ መንገድ መድረክ በግድ ነጥቆ ማስተማሩ ምእመናንን በእጅጉ አስቆጥቷል።

በጋሻው መድረኩን በጉልበት ከነጠቀ በኃላ መድረክ ላይ ቆሞ 

ሉንድ፣ስዊድን ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከሁለት ሳምንታት በፊት የግንቦት 21 የደብረ ምጥማቅ የቅድስት ድንግል ማርያምን በዓል ለማክበር ዝግጅት ይጀምራሉ።በእዚህ መሰረት ከስዊድን እና ኖርዌይ የሚገኙ አባቶች በአቡነ ኤልያስ ተመድበው ለአገልግሎት ይሄዳሉ።ጉባኤው ሲካሄድ ቀደም ብሎ በጋሻው በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ በማገልገል ላይ በሚገኘው ዲ/ን ያሬድ አማካይነት የግብዣ ደብዳቤ ተልኮለት ስዊድን ገብቶ ነበር።ሆኖም ግን ምእመኑን በመፍራት በዕለቱ በቦታው ዝር ሳይል ይቆያል።

በሳምንቱ ግን በቦታው የዶክትሬት ዲግሪውን በመስራት ላይ በሚገኘው እና ያለውን ትርፍ ጊዜ በሙሉ በቤተ ክርስቲያኒቱን በነፃ በቅዳሴ፣በማስተማር እና ምዕመናንን በመምከር የሚያገለግለው ቀሲስ መንግሥቱ በቦታው የዕለቱን ትምህርት ለመስጠት ሲዘጋጅ ከበጋሻው በኩል ትዕቢት በተሞላበት እና የቤተ ክርስቲያንን ስርዓት ፈፅሞ በተፃረረ መልክ ካህኑን እላፊ ንግግሮችን ከመናገሩም በላይ መርሃ ግብሩን የሚመራው እና ቀደም ብሎ በጋሻውን ለማስመጣት ደብዳቤዎችን መላኩ የተነገረለት ዲ/ን ያሬድ የድምፅ መናገርያውን ከካህኑ ነጥቆ ለበጋሻው ሲሰጥ እና ቀሲስ መንግስቱ እና ምዕመናን ቤተ ክርስቲያኑን ጥለው እያለቀሱ ሲወጡ ተስተውሏል።ይህ ጉዳይ የበርካታ ምእመናንን ልብ ያሳዘነ ከመሆኑም በላይ ጉዳዩ በእዚህ ሳይቆም  ለቅዳሜ ሰኔ 6/2007 ዓም አሁንም በድጋሚ ምእመናንን የሚጠራ ፖስተር ተዘጋጅቶ እንዲሰራጭ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።

Sunday, June 14, 2015

“ሃይማኖታዊ ግጭት ለማስነሣት ተንቀሳቅሳችኋል” የተባሉ የሰበካ ጉባኤ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ





  •   ፖሊስ10 ቀንየምርመራጊዜጠይቆባቸዋል

    
በደቡብ ክልል የስልጤ ዞን ምሥራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ፣ የቂልጦ ጎሞሮ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤና የደብሩ ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ አባላት “ሃይማኖትን ከሃይማኖት ለማጋጨት ተንቀሳቅሳችኋልበሚል በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡