ደብር ወገዳም
መልካም ቃላት የሚበዙት ክፉት ሲበዛ ነው። ሰው መልካም ሥራ ሲርቀው ክፋቱን ሊደብቅ ሲል መልካም ስም ማዕረግ ይደረድራል። መልካም ቃላት ጋጋታ ይጠቀማል። የዘንድሮን የመንፈስ እርቃንነት መቋቋም ያልቻለ ስው ግማሹ በስም ግማሹ ባሸበረቀ ካባና ቀሚስ እንደ ሞዴል በሚቀያየር አልባሳት ያጌጣል።
ቀደም ባለው ጊዜ የቆየው ባሕል ሊቃውንት ብቻ የሚጠሩበት ሥም አለ። እንደየ ትምህርታቸው እንደ ደብሩ ትልቅነት የአለቃ ስም ይሰጣል። ዛሬ ግን ስም ያልወሰደ የለም። የማይንቆለጳጰስ የለም።
 |
| ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕርዳር እና የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስበከት ሊቀ ጳጳስ |
ሰላም በሌለበት ደብር የመልአከ ሰላም አበዛዙ፣ የተማረው የተመገበው ሳይኖር የመጋቤ ሐዶስና ብሉይ አበዛዙ ግርም ይላል።
መልአከ ከዋክብት፣ መልአከ ጨረቃ፣ መምህረ መምህራን፣ ርዕሰ ርዑሳን፣ ርዕሰ ባሕታውያን፣ ቆሞስ ሞቆሳት …..ሊቀ ሐዋርያት፣ መጋቤ ሰማእታት… ምኑ ቅጡ። አምፓል ለቀጠለ ኹሉ መልአከ ብርሃን።
አቡነ አብርሃም ደግሞ ሰሞኑን አንዲት ስም አስተዋውቀዋል። ደብር ወገዳም የምትል። የዶላር ስም ናት መሰለኝ። መቼስ ለብር ቤተ ክርስቲያን እንዲኽ ያለ ስም አይወጣም።