Tuesday, December 4, 2012

ስለ “አባቶች እርቅ” ጉዳይ ፊርማ ማሰባሰብ ተጀመረ



  •    ምእመናን ፊርማቸውን በኢንተርኔትም ሆነ በየአጥቢያቸው በወረቀት እንዲያሰባስቡ ተጠይቀዋል፤
(ደጀ ሰላም ኅዳር 25/2005 ዓ.ም፤ ዲሴምበር4/2012/ READ THIS NEWS IN PDF):- የቤተ ክርስቲያን አባቶችን እርቀ ሰላም ለማገዝና የምዕመናን ሙሉ ድጋፍ ለማሳየት “የተማኅጽኖ ፊርማ” (ፔቲሽን) ማሰባሰብ ተጀምሯል። ምእመናን የዳር ተመልካች ሆነው ቤተ ክርስቲያን ከአንድ ችግር ወደ ሌላ ችግር ስትሸጋገር መመልከት ብቻ ሳይሆን እነርሱም በፈንታቸው “የእርቁ አካል” በመሆን አባቶችን መርዳት እንደሚገባ የሁሉም እምነት ነው። ደጀ ሰላምም ለረዥም ዓመታት ስታደርግ እንደነበረው አሁንም ምእመኑ ይህንን የፊርማ ዘመቻ በመካፈል ድምጹን ማሰማት አለበት።  በኢንተርኔት መፈረም ለምትፈልጉ (ይህንን በመጫን) ፊርማውን ማከናወን ይቻላል። የ “ፌስቡክ ተጠቃሚዎች” በፌስቡክ አማካይነት በቀላሉ መፈረም ያስችላችኋል።

በየአጥቢያችሁ ፊርማውን በመፈረም ሌሎችንም እንዲፈርሙ ማድረግ ለምትፈልጉ ደግሞ (ይህንን ፒ.ዲ.ኤፍ) “ዳውንሎድ” በማድረግ መጠቀም ትችላላችሁ።

ቸር ወሬ ያሰማን፤
አሜን፡፡

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

No comments:

Post a Comment