Monday, February 20, 2012

እንኳን ለታላቁ ጾም፣ ጾመ ሁዳዴ አደረሳችሁ




ይህ ታላቅ ጻም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ሞቶ ሕይወት ሊሆነን በገዳም ገብቶ የጾመው ጾም ስለሆነ፣ እኛም መላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ ጾሙን የረደኤት የበረከት እንዲያደርግልን እና ለትንሳኤው በዓል በሰላም እንዲያደርሰን እንመኛለን።
ለቅድስት ቤተክርስቲያናችን አብዝተን እንጸልይ፣ የድህነታችን፣ የእኛነታችን መገለጫችን፣ የኢትዮጵያ ሀገራችን የስልጣኔ ምንጭ እና ኩራት የሆነችው የተዋሕዶ እምነታችንን ከአረያም ሆኖ በቃሉ ችግሮችን አስወግዶ አጽራረ ቤተክርስቲያንን አስታግሶ፣ የረቁትን አቅርቦ ያሉትን እንዲያጸናልን የዘወትር ምኞችን ነው።
መልካም ጾም
ቸር ያቆየን
የመላው ዓለም የተዋሕዶ ቤተሰብ

No comments:

Post a Comment