Tuesday, February 14, 2012

በፊኒክስ አሪዞና እርቀ ሰላም ተጀመረ


እርቁ እውነት ይሆን? እርቁን የማይፈልግ ክፍል ይኖር ይሆን?

ዛሬ የካቲት ፮ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. በፊኒክስ አሪዞና የኢትዮጵያው ቅዱስ ሲኖዶስ ተወካዮች

፩ኛ/ ብፁዕ አቡነ ገሪማ የመንበረ ፓትሪያሪክ ልዩ ጸሐፊና የድሬደዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
፪ኛ/ ብፁዕ አቡነ አትናቲዮስ የወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
፫ኛ/ ብፁዕ አብነ ቀወስጦስ የኣዲስ አበባ እና የምዕራብ ሸዋ ሊቀ ጳጳስ (በህመም ምክንያት መምጣት አልቻሉም)

፫ኛ/ ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ
እንዲሁም ከስደተኛው ሲኖዶስ የተወከሉ ደግሞ
፩ኛ/ ብፁዕ አቡነ መልከፄዲቅ የስደተኛው ሲኖዶስ ጸሐፊ
፪ኛ/ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስደተኛው ሲኖዶስ ተወካይ
፫ኛ/ ሌቀ ካህናት ምሣሌ
፬ኛ/ መልአገ ገነት ገዛህኝ ከስደተኛው ሲኖዶስ በኩል በተወካይነት ተወክለው በተጠቀሰው ቦታ ተገናኝተው እርቀ ድርድሩን ለማድረግ ትላንት ጀምረው ተወካዮቹ በፊኒክስ ተገኝተው ዛሬ ረፋዱ ላይ ስብሰባው እንደሚጀመር ይጠበቃል።

ከኢትዮጵያው ቅዱስ ሲኖዶስ የተወከሉት ተደራዳሪዎች ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ለማስጠበቅ እና ለማስከበር እንደ መደራደሪያ ያቀረቧቸው ነጥቦች
  • በስደት ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት ሀገርን እና ቤተክርስቲያንን ጥለው መምጣት ሳያንሳቸው በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ሲኖዶስ ማቋቋም፣ እንደገና ሹመት መስጠት በቤተክርስቲያኒቱ ላይ የተፈጸሙ ከፍተኛ በደሎች ናቸው፥ ከዚህ በተጨማሪ እንደ ሕጋዊ አካል ዶግማ ማሻሻል፣ ቀኖናን ወደጎን መተው ትክክለኛ አካሄዶች እንዳልሆኑ ማስገንዘብ
  • ብፁዕ አቡነ መርቆሪዎስ ሥራቸውን የለቀቁት እራሳቸው በጻፉት ደብዳቤ እንደሆነ ማስገንዘብ፣ ለዚህም በወቅቱ አቃቤ ፓትሪያሪክ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ በጻፉላቸው  ደብዳቤ ማስገንዘብ
  • በአሜሪካን ሃገር መጥተው ቅዳሴው እረዝሟል ይጠር፣ ቤተክርስቲያን ባስፈለገው ሙዚቃ መሣሪያ ያገልግል፣ ቤተክርስቲያን ከምትጠቀምባቸው ፲፬ ቅዳሴያት ሁሉንም ወደጎን ትቶ ቅዳሴ ሐዋርያት እና ቅዳሴ እግዚእ ብቻ እንዲቀደስ ማድረግ፣ ቅዳሴ ማሪያም በተለይ እርዝመቱ ከባድ ነው ብሎ መተው፣ እና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች የሚያነሱ ይገኙበታል።
ከስደተኛው ሲኖዶስ ተወካዮች በኩል እንደመደራደሪያ ነጥብ ያስቀመጧቸው ደግሞ

  • የመንግሥት ጣልቃገብነት በቤተክርስቲያን ላይ ይቁም፣ የታሰሩ የፓለቲከኛ እስረኞች ይፈቱ፣
  • የኢትዮጵያው ቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖና አፍርሷል፣ ሥርዓት አጓድሏል እና ይህን ማመን አለበት
  • የታሰሩት ካልተፈቱ፣ የመንግስት ጣልቃ ገብነት ካላቆመ እርቅና ድርድር የለም ብለው ነው የተነሱት።
በእውነት ለእርቅ እና ለቤተክርስቲያን ሰላም፣ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ሰላም ከተፈለገ ቤተክርስቲያን የፓለቲካ መድረክ አይደለችም ለሕዝቦች ድህነት ሰውና እግዚአብሔር የምታገናኝ ሆና ሳለ የታሰሩት ካልተፈቱ፣ መንግስት ጣልቃ ገብነቱን ካላቆመ ብሎ ድርድር መምጣት፣ መጀመሪያውኑ እንዲሆን ፍቃደኞች አይደለንም ግን ዝም ብለን አደራዳሪዎቹን ለማስደሰት ወይም አበል ለመብላትም ይሁን እሺ እንበል እንደማለት ይመስለናል። መቼም የታሰሩ የፓለቲከኛ እስረኞችን መንግስት እንዲፈታ፣ መንግስት ሕዝብን የማስተዳደሩን ሥራ ብቻ እንዲሰራ እና ከቤተክርስቲያን አስተዳደር ላይ ጣልቃ እንዳይገባ የማይፈልግ ማንም ሰላም ወዳድ ሕብረተሰብ ይኖራል ብለን አናምንም ያንንም ቢሆን ሰላማዊ በሆነ መንገድ መንግስትን በቀጥታ መጠየቅ ሲቻል እኛን እና የያዝነውን ቲፎዞ ይዞ ኢትዮጵያ ለመግባት ብሎ እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስመዝገብ ተገቢ ነው ብለን አናምንም፤ ምክንያቱም መንግስት ጥያቄዎቹን ተቀብሎ ቢስማማ እና የታሰሩትን በሙሉ ቢፈታ እንደውም እስር ቤቶች በሙሉ ወደ ት/ቤትነት ቢለወጡ የሁሉም ሰላም ወዳድ ሀሳብ እንደሆነ እንስማማለን፣ ነገር ግን የማይጋፉትን ባላጋራ እዛ በውጪ ተቀምጦ ይሄ ይሁን ማለት ከእውነታው መራቅ ወይንም እውነታውን እያቀቁ እርቁን አንፈልግም እንደማለን ይመስለናል።

ልክ እንደ ከዚህ በፊቱ ለውይይት ከመምጣታችን በፊት የአቋም መግለጫ አዘጋጅቶ መምጣት ምን የሚሉት ድርድር ነው፣ መጀመሪያ ውይይቱ ሳይጀመር ምን ዓይነት መልክ እንደሚኖረው ሳይታወቅ፣ ግራ ቀኙን ተመልክቶ ለቤተክርስቲያን በማሰብ፣ የሕዝበ ክርስቲያኑን በለያየት በማሰብ፣ ይልቁንም የራቀውን ለማቅረብ እና የተጣላውን ለማስታረቅ ሱባኤ ይዞ፣ ጾም ጸሎት ተደርጎ ነበር እግዚአብሔርን እንዲሁም ቅዱሳኑን አጋዥ በማድረግ ለወይይት ይመጣል እንጂ ምኑም ሳይታወቅ የአቋም መግለጫ አዘጋጅቶ መምጣት ለሰላሙ ያልተዘጋጀ ክፍል እንዳለ ያሳያል። ምናልባት የተወሰነው ክፍል ጭንቅ የሆነበት ክፍል ያለ ይመስለናል ምናልባት ዲያብሎስ ይፈር፣ የአምላካችን ስም ይክበር ተብሎ እርቁ ቢፈጸም የሚጎረብጣቸው ክፍሎች እንደሚኖሩ ምንም ጥርጥር የለውም፥ ለዚህም አይነተኛ ምሳሌዎች ከላይ እንደገለጽነው
  • ለእርቅ ሲመጣ ቅድሚያ ጸሎት እና ሱባኤ እንጂ የአቋም መግለጫ ማዘጋጀት ባላስፈለገ፤
  • ለእርቅ ሲመጣ ቅድሚያ እስረኞች ይፈቱ ብሎ ድርድር መምጣት ባላስፈለገ ነበር፤
  • ለእርቅ ሲመጣ ቅድሚያ በምን መልኩ መልክተኞችን እናስተናግድ ወይም እጃችን ላይ ያለውን የሰላም ጥሪ እከሌ ካለ ድርድር የለም ባልተባለ ነበር፤
  • ለአባቶችም ብትውናቸው፣ ለምዕመናንም ቤተክርስቲያናቸው ብቸኛ መፍትሄ መሆኑ ማመን እና መዘጋጀት ያስፈልጋል።
እንደ ክርስቲያን ይልቁንም እንደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆች የተጀመረው እርቅ ወደ ሰላም እንዲያመራ እና የአንዲት ቤተክርስቲያን ልጆች በተለያየ ሥርዓትና መቅደስ መቀደሳቸው አቁሞ በአንድነት ለሃያሉና መድኃኒዓለም ክርስቶስ በአንድነት እንድንጸልይ፣ እንድናመልክ፣ ቅዱስ ሥጋውን እና ክብር ደሙን ለመቁረብ እንዲያበቃን የዚህ ዝግጅት ክፍል መልካም ምኞቱን ይገልጻል።
የደረስንበትን ዜና እየተከታተልን እናቀርባለን
ቸር ወሬ ያሰማን
አሜን

የመላው ዓለም የተዋሕዶ ቤተሰብ

3 comments:

  1. From American Senodos, I just don't get the point of mentioning issue number one.

    First, i agree on the idea of the government not involving into relegiouse issues. However, asking the release of politician people is a political issue not a religious issue. So,please stop compromizing issues unless u don't want one Ethiopia!

    ReplyDelete
  2. abetu kidus fekadih yihun

    ReplyDelete
  3. enate zegaby nachu weys yeandbudne degafey yaum yahgerbetun kidus eyalchu yewchum abune yemtetru asasfachu krstinan yazle aymeslem, eserejoch yeftu belo metyke yecherche tyake aydelem nger gyne mengyst haymanot talkagebnetun aldgyfem.
    betchale metyne selyu ewntyn yazu

    ReplyDelete