Monday, February 20, 2012

በአሪዞና የተጀመረው እርቅ በመልካም ጅምር ተጠናቀቀ

በሀገር ውስጥ ባለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ እና በውጪ በሚገኘው ሲኖዶስ በካከል ባለፈው ሳምንት የተጀመረው ድርድር እግዚአብሔር በፈቀደው በጥሩ ሁኔታ መጠነቀቁ ከሥፍራው በደረሰን ዜና ለመረዳት ችለናል። ከባለፉት

ድርድሮች ሁለቱም ወገኖች በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው ንግግር አድርገው አያውቁም ነበር፣ ሌላው ቀርቶ ሰላምታ እንኳን መለዋወጥ የቻሉበት ጊዜ እንዳልነበረ ስናስታውስ የአሁኑ ዙር በእውነቱ ትልቅ እና ብዙ ጉዞዎችን ያደረጉበት ነው ብለን እናምናለን፣ በማንኛውም ቦታ እና ዓለም የሚገኙ የሰላም ወዳድ ሀይሎች ለዚህ ለሃያ ዓመታት የዘለቀው የጠላትነት ጊዜ አብቅቶ፣ ቃለ ውግዘቱ ተነስቶ አንድ የሚሆኑበት እና እንደገና በአንድ መቅደስ የምናገለግልበት ጊዜ እሩቅ እንደማይሆን እንገምታለን።
የተጀመረውንም የጾም ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ሰላም የናፈቀውን የተዋሕሶ ቤተሰብ እንደገና ሰለም እንዲያሳየን አብዝተን እንድንጸልይ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።
የጋራ መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ


 የመላው ዓለም የተዋሕዶ ቤተሰብ

No comments:

Post a Comment