Wednesday, November 23, 2011

ጥቅምት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የተቃውሞ

ጥቅምት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የተቃውሞ ሰልፍ እይታዎች ሙሉዉን ቪሲዲ አቅርበንላችኃል

video


ጥቅምት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያሪክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ያደረጉትን የተቃውሞ ሰልፍ የሚያሳይ የ 20 ደቂቃ ቪሲዲ ለዛሬ አቅርበንላችኋል ሙሉውን ታሪክ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

በሰልፉ ላይ በአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት ከሚገኙ የ131 ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ያላቸውን የደንብ ልብስ(ዩኒፎርም)እና ነጠላ በመልበስ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምቱ ጉባዔው በተሐድሶ መናፍቃን ላይ እርምጃ እንዲወስድ ሲያሳስቡ ይታያል፡፡ ወጣት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎቹ ተቃውሞአቸውን በአደባባይ ከማሰማታቸው በፊት ቀደም ባሉት ጊዜያት መዋቅራቸውን ጠብቀው ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትና ጉዳዩ
በቀጥታ ለሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላት የተሐድሶ መናፍቃንን ማንነት የሚያጋልጥ ባለ 261 ገጽ የጽሑፍ ሰነድና 14 የምስል እና የድምጽ(VCD) ሰነድ በማስረጃነት ማቅረባቸው ቢታወቅም አደባባይ ለመውጣት እነዳላሰቡ ሆኖም ግን እነ በጋሻው፣ትዝታው፣አሰግድ፣ናትናኤል፣ያሬድና ሌሎችም የተሐድሶ ሎሌዎች ስማችን ጠፋ፣ መድረክ ተከለከልን፣ ተሐድሶ የሚባል የለም ፣ወዘተ….በማለት በለመዱት የግራ ዐይን የአዞ እንባቸው ሕዝቡን ለማሳሳት ሰልፍ እንወጣለን ብለው በማወጃቸው ምክንያት ወጥተው ተቃውሞአቸውን እንዳሰሙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ቪሲዲው፦
• “የዘማሪ” ትዝታው ሳሙኤልን መደብደብና መዋከብ ኋላም በድንጋጤ ጥግ ላይ ተደብቆ ጥርሱን እየነከሰ መንቀጥቀጥን፣
• የተሐድሶ መናፍቅ አሰግድ ሳህሉን ተንኮሳና መንቀዥቀዥ ኋላም መደንገጥና መሸማቀቅን፣
• የ“ዘማሪት” ቅድስት ምትኩንና “ዘማሪት” የትምወርቅን ድፍረትን፣
• የመናፍቁ ናትናኤል ታምራት በፍርሃት ታጥሮና ጥግ ይዞ መታየትን፣
• የ“መምህር” ተረፈን የመሃይም ድፍረትና በኋላም ቅሌትና ውርደት፣
• የሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴንና የቅ/ማርያም ገዳም አስተዳዳሪ አላዋቂነትና አድርባይነትን፣
• የአዲስ አበባን ሰንበት ት/ቤቶች በወኔ የታጀበ ጠንካራና የተደራጀ ተቃውሞን፣
• የቅዱስ ፓትርያርኩን ብስጭትና ወገንተኛነት፣
• የአዲስ አበባና የፌዴራል ፖሊሶችን የተረጋጋ፣ሕጋዊና ሰላማዊ የጸጥታ ማስተባበር ሥራን፣
• የአዲስ አበባ ምዕመናንን እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን ቅናት ወዘተ…..በአንጻሩ ደግሞ የተሐድሶ መናፍቃንን ድፍረትና አይን አውጣነት ያሳያል፡፡
• የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ቤተ ክርስቲያናችን በተሐድሶ መናፍቃን አትወረርም የሚል አገር አቀፍ ብሎም ዓለም አቀፍ የሆነ አጀንዳ ይዘው ታይተዋል፤
ቪሲዲው ከ“ዘማሪያኑ” እነ ትዝታው ሳሙኤል፣የትምወርቅ፣ቅድስት ምትኩ፣ምርትነሽ ጥላሁን፣ሃብታሙ ሽብሩ፣ሐዋዝ ተገኝ፣…..ከ“መምህራን” ናትናኤል ታምራት፣አሰግድ ሣህሉ፣ተረፈ፣ጋሻዬ መላኩ፣ስንታየሁ፣በፈቃዱ፣ታሪኩ አበራ….ነበሩበት፡፡የአዲስ አበባ ምዕመናን “ፍንዳታ”እያሉ የሚጠሯቸው የመነኩሴ ቆብ ያጠለቁ የተሐድሶ መነኮሳትም ነበሩበት፡፡
እነበጋሻውና ያሬድ አደመ ከመጋረጃው ጀርባ ሆነው ማስተባበርን መርጠዋል፡፡ማንነታቸው እንዳይታወቅ ፊታቸውን በሰፊ መነጽር ለመሸፈን የሞካክሩ ኮረዳዎችም በሰልፉ ነበሩበት
ቪሲዲው ኤዲት ስለሚጎድለውና ስለ ድምፁ ጥራትም ይቅርታ እንጠይቃለን። 
እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያናችንን ይጠብቅ አሜን።
ምንጭ : ከደቂቀ ናቡቴ የተገኘ

የመላው ዓለም የተዋሕዶ ቤተሰብ

No comments:

Post a Comment