Sunday, December 28, 2025

የሠለስቱ ደቂቅ የነገረ መለኮት ትርጓሜ

እንኳን ለሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አድረሰን አደረሳችሁ በማለት፤ የነገረ መለኮትን ትርጓሜ በተለይ የሠለስቱ ድቂቅን ታሪክ በፍኖተ አበው የቴሌግራም ገጽ ያገኘነውን ለማጋራት ይሄንን የሚከተለውን ጽሁፍ እንድታነቡ በአክብሮት እንጋብዝዎታለን።

    በሠለስቱ ደቂቅ ምስጋና ሰይጣን የሰው ልጆችን ድል መንሳቱን የእግዚአብሔር ልጅም ወደ ሲኦል መውረዱን በኃይሉም ከችግራቸው 
ሊቀ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል
ስለማዳኑ የገለጠበት ምስጢር ነው። 

    ከአዳም ከተፈጠረ እስከ ክርስቶስ ልደት ድረስ ያለውን ከዚያም እስኪሰቀልና ወደ ሲኦል ወርዶ እስኪያድናቸው በምድር የሚኖርባቸውን ዘመናት ይነግረናል። ይኽም የዳንኤል አራተኛው ራእይ ነው። 
"የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአቄም በነገሠ በሦስተኛው ዓመት የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ከበባት" ት. ዳን 1:1

    የእስራኤል ልጅች በፈርኦን በባርነት መኖራቸው የአዳም ልጆች ለሰይጣናት በባርነት ለመኖራቸው ምሳሌ እንደሆነ እግዚአብሔርን ስለመድፈራቸው ናቡከደነጾር የእስራኤልን ልጆች እንደ ማረካቸው ከቅድስት ሀገራቸው እስከ ሀገሩ ባቢሎን እንዳፈለሳቸው እርሱም ከሠራዊቱ ከከለዳውያን አስገድዶ እንዳስገዛላቸው ነቢዩ ዳንኤል አመለከተ። 

    "ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው። የመለከትንና የእንቢልታን፥ የመሰንቆንና የክራርን፥ የበገናንና የዋሽንትን፥ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፥ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል" ት.ዳን. 3:1-5 

Thursday, December 18, 2025

ጾመ ነቢያት: አስተምህሮ፣ ስብከት፣ ብርሃንና ኖላዊ

የነቢያት ጾም

ጾመ ነቢያት (የገና ጾም)  ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ሲሆን “ጾመ ነቢያት” የተባለበት ምክንያት ነቢያት ስለጾሙት
ልደተ ክርስቶስ

ነው፡፡ “ነቢያት የጾሙት ስለምንድን ነው?”  ቢሉ ለአዳም የተሰጠውን “አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚለውን የተስፋ ቃል በማሰብ ከሰማየ ሰማያት ይወርዳል፣ ከድንግል ማርያም ይወለዳል፣ በሞቱም ሞት የተፈረደበትን የሰው ልጅ ነፃ ያወጣዋል ብለው ነው፡፡ “ይህንን ጾም የትኞቹ ነቢያት ናቸው የጾሙት?” ቢሉ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ፵ ቀን ጾሟል (ዘጸዓት ፴፬ ፥ ፳፯)፤ ነቢዩ ኤልያስም ፵ ቀን ጾሟል (፩ኛ ነገሥት ፲፱ ፥ ፩)፡፡ በተጨማሪም በተለያየ ዘመን የነበሩት ነቢዩ ዕዝራ፣ ነቢዩ ነህምያ፣ ነቢዩ ዳንኤል እንዲሁም ክቡር ዳዊት ጾመዋል፡፡

“ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ብለው ከጾሙ፤ እኛ እርሱ ወርዶ፣ ተወልዶ ተሰቅሎ ካዳነን በኋላ ያለን የሐዲስ ኪዳን ክርስትያኖች ስለምን የነቢያትን ጾም እንጾማለን?” ቢሉ እኛ የነቢያትን ጾም የምንጾመው እንደቀደሙት ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል እያልን ሳይሆን የቀደሙት ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል እያሉ የጾሙትን በማሰብ በመጾማችን ድኅነተ ሥጋ፣ ድኅነተ ነፍስ፣ በረከተ ሥጋ፣ በረከተ ነፍስ እንድናገኝበት ነው፡፡”ጾመ ነቢያት (የገና ጾም)  ከኅዳር ፲፭ ጀምሮ እስከ ታኅሳስ  ፳፰ ቀን (በዘመነ ዮሐንስ እስከ ታኅሳስ ፳፯ ቀን)  ድረስ ለ፵፬ ቀናት (በዘመነ ዮሐንስ ለ፵፫ ቀናት)  ይጾማል፡፡ ከእነዚህም መካከል ፵ ቀናት ጾመ ነቢያት፣ ፫ ቀናት ጾመ አብርሃም ሶርያዊ ሲሆኑ የቀረው ፩ ቀን ደግሞ የገሃድ ጾም ነው (ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፲፭ ቁጥር ፭፻፷፭ ፣ ፭፻፷፯)፡፡ ጾመ ነቢያትን ከኅዳር ፲፭ ጀምሮ ሳይጾሙ የልደትን ዋዜማ ብቻ መጾም የቤተክርስቲያን ሥርዓት አይደለም፡፡

Monday, December 15, 2025

በሰሜን አሜሪካ የሚገኙ አባቶች እና ወንድሞች በአሜሪካን ምክር ቤት ፊት ቀርበው የአርሲ ክርስቲያኖችን ጭፍጭፋ መረጃዎችን አጋርተዋል

"…በብፁዕ አቡነ ሉቃስየተመራ እና መልአከ ጥበባት አባ ገብርኤል ዶ/ር፣ መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ሳሙኤል ግዛው (ኢትዮ ቤተሰብ)፣  እና 
ዲያቆን ፋሲካው ካሳውን ያካተተ አንድ ጠንካራ አይሰበሬ ባለማዕተብ ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች ልዑክ ባለፈው ሣምንት በሀገረ አሜሪካ በዋሽንግተን ከተማ በአሜሪካ የሚኖሩ፣ እዚያው ተወልደው ባደጉ፣ ዜግነትም ባላቸው ኢትዮጵያውያን የተዋሕዶ ልጆች ያላሰለሰ ተጋድሎና ጥረት በኋላ ከአሜሪካ መንግሥት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የመንግሥቱ ባለሥልጣናት ጋር ታሪካዊ የሆነ የመጀመሪያ ደረጃ ፍሬያማና ውጤታማ ውይይት መደረጉን የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል። 

Sunday, December 14, 2025

የሆሮ ጉዱሮ ወለጋ ሃገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ በታጣቂዎች ተገደሉ!!

የሆሮ ጉድሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች ተገድለዋል፤ የሕዳር ጽዮን ማርያምን በዓል በሆሮ ጉድሩ ወለጋ
ሀገረ ስበከት ሥር በምተገኘው በሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ሻንቡ ከተማ መዳረሻ ሲደርሱ መልአከ ኤዶም ቀዲስ ዱጉማ እና በርካታ የህገረ ስብከቱ ሠራተኞችና ወጣት የማሕበራት አገልጋዮች በሕገ ወጥ ታጣቂዎቹ ተወስደው የቆዩ ሲሆን ሌሎቹ ተፈትተው ቆይተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የተመለሱ ሲሆን በትናንትናው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ አፋ እና ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል፤ 
ዛሬም ኦሮዶክሳውያኑ ተደራጅተን እራሳችንን መከላከል ካልቻልን፤ አንድ በአንድ ተለቅመን እንደምናልቅ ጥርጥር የለውም! " Oromoon Oromoo hin Ajjeesu ማለትም ኦሮሞ ኦሮሞን አይገድልም "የሚለው የኦነግ/ብልጽግና ፍልስፍና ለኦሮሞ ኦርቶዶክስ  ሲሆን አይሠራም።ለምን? "ኦርቶዶክስ የአማራ ሃይማኖት ስለሆነ ?"የኦሮሞ ብሔርተኝነትን መስፈርት አያሟላም።እውነታው ይኽ ነው።ዛሬ በወለጋ የተገደሉት ሁለቱም ካህናት ኦሮሞ ናቸው ነገር ግን  ግን ከሞት አላመለጡም።ይኽን በመጻፌ ፖለቲካ ውስጥ ገባህ እባል ይሆን?

Friday, December 12, 2025

በአሜሪካ የሚገኘው የአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ፈተናዎቹ እና ችግሩ አስተዳዳሪው ናቸው

የአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አሜሪካ
ሰሞኑን አንድ ጥቆማ ከባሕር ማዶ አሜሪካ ደርሶን ነበር፤ ይኽውም በአሜሪካን ሃገር የሚገኘው የአቡነ ተክለሃማኖት ቤተክርስቲያን ዙሪያ ባለፉት ጥቂት
አመታት ውስጥ ቤተክርስቲያኒቱ በተለያዩ ሁኔታዎች ክርስቲያኖች ሲገፉ፣ ቤተክርስቲያንን ልክ እንደግል ንብረት የሚያዩ የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ፣ የሰበካ መንፈሣዊ አስተዳደር ጉባኤ፣ ቀሳጢ ዲያቆናት እና ጥቂት ባልቴቶች በሚፈጥሩት አልባሌ ከሕገ ቤተክርስቲያን ውጪ በሆነ መልኩ የቤተክርስቲያኑን አስተዳዳሪ ልክ ከጳጳስ በላይ የማንገስ ብሎም ሰውየው በተለይ ሁኔታ እራሳቸውን ከሕግም፣ ከምዕመናን በላይ እራሳቸውን የተለዩ ልዩ ፍጥረት አድርጎ የማየት አገልግሎት እንኳንስ ለመነኮሴ ለማንኛውም የቤተክርስቲያን አገልጋይ ጠዋት በኪዳን፣ ማታ በነግህ ጸሎት ጽሙድ ሆኖ አገልግሎት መስጠት የተለመደ እና ትክክለኛ ሃይማኑቱ የሚጠይቀው ሆኖ ሳለ ነገር ግን የቤተክርስቲያኑን አስተዳዳሪ ጸሎታቸው የተለየ እና ጽርሐአርያም የሚደርስ አድርጎ አግኖ የማሳየት ሁኔታ በእነዚህ ከላይ በጠቀስናቸው አድር ባይ ካህናት፣ ቀሳጢ ዲያቆናት እና ሥራ ፈት ባልቴቶች በተደጋጋሚ የቤተክርስቲያንን ችግር የሚያባብሱ እና ችግሩን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ የሚወስዱ የቤተክርስቲያን ፈተናዎች እንደሆኑ ከማንም የተደበቀ እንዳልሆነ በተለያዩ ክስተቶች ላይ ስንመለከት ቆይተናል፤ አሁንም በዚህ አጥቢያ የተከሰተው ይሄን አይነት ጉዳይ ነው።

Thursday, December 11, 2025

Press Releases Carter defends Christians against corrupt Ethiopian government in new resolution

WASHINGTON, D.C. – Rep. Earl L. “Buddy” Carter (R-GA) today 
introduced a resolution condemning the
The Ethiopian government for its many human rights violations, including the persecution of Christians, and urging the Secretary of State to use all available diplomatic tools to protect innocent civilians against their abusive, corrupt government. 

 

The resolution condemns Ethiopia for “actions that threaten regional stability, violate fundamental human rights, and undermine the strategic interests of the United States in the Horn of Africa,” citing “acts of war crimes, crimes against humanity, and genocide,” and the targeting by “violence, intimidation, and persecution” of the Ethiopian Orthodox Church and other religious institutions. 

 

“Practicing your Christian faith is not a crime. Terrorists are running Ethiopia into the ground, and with it the lives of countless innocent people, particularly religious minorities. From intimidation to famine and genocide, the Ethiopian government has given the United States no option but to limit its power by using every tool available to hold them accountable for these, and many other abuses,” said Rep. Carter.  

 

Good News፦ ትግሉ ተቀጣጥሏል

The U.S. lawmaker tables a resolution condemning rights violations in Ethiopia, calls for global Magnitsky sanctions 

A United States lawmaker has introduced a new congressional resolution condemning what it describes as widespread human rights violations by the Ethiopian government, with a particular focus on abuses against Christians and other religious communities.  

The measure, introduced by Rep. Earl L. “Buddy” Carter (R-GA), urges the U.S. Secretary of State to deploy all available diplomatic tools, including targeted sanctions, to protect civilians and hold Ethiopian officials accountable. 

The resolution sharply criticizes the Ethiopian government for actions it says “threaten regional stability, violate fundamental human rights, and undermine the strategic interests of the United States in the Horn of Africa.” 

Friday, December 5, 2025

መምህር ዲ/ን ዮሴፍ ዛሬም በግፈኞች እሥር እንዲቀጥል ተደጓል! እግዚኦ ለዳኝነት!!

መምህር ዮሴፍ ዛሬም አልተፈታም፡፡ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ የተቀጠረ የነበረ ቢሆንም አሁንም ፖሊስ ይግባኝ በማለቱና ወንጀል
መምህር ዲ/ን ዮሴፍ

ሊያገኝበት ስላልቻል ለቀጣይ ማክሰኞ ቀጥረውታል፡፡ ለቀጣይም ዮሴፍ ላይ ወንጀል ማግኘት አይችልም፡፡ የማራዘሚያ ዘልዛላ ምክንያት ግን ይፈበርክ ይሆናል፡፡

ዮሴፍ እንዳይፈታ እየታገለ ያለው ታጋይ የሚባለው ቤተ ክርስቲያንን ይታገልና ሥርዓቱን ያገለግል ዘንድ በቤተ ክርስቲያን ስም የሆነ ተቋም ''እመራለሁ'' የሚል ሰው ነው፡፡ 

ምንም እንኳን አሁን እንደተገለጠው ዮሴፍ አንድ ታጋይ የሚባል የቀድሞ ደረሳ እስረኛ ቢሆንም ለዮሴፍ መንገላታት ግን ዋና ተጠያቂው የቤተ ክርስቲያን ጠላት የሆነው ሥርዓቱ ነው፡፡ እንደ ታጋይ ያሉ አረመኔዎች የግል ታሳሪዎቻቸውን ያለ ምንም ወንጀል በመንግሥት ማረሚያ ቤት የሚያጉሩ ከሆነ ተጠያቂው ሥርዓቱ ነው፡፡ 

ይኸ ሥርዓት ገና ከጥንስሱ የቤተ ክርስቲያን ጠላትነቱን ያስመሰከረና ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጥራዝ ነጠቆችን፣ ሆዳሞችንና ከሐዲዎችን በመሰብሰብ በራሷ ልጆች በሚመስል መልኩ በተደጋጋሚ እያቆሰላት ይገኛል፡፡ ሥርዓቱን የሚያገለግሉ፣ ቋንቋዋን የሚናገሩና አልባሳቷን የሚለብሱ ሰዎችን የሚፈልጋቸው ከውስጥ ያለውን መከራ ለማጽናት ነው፡፡ 

Thursday, December 4, 2025

✍️መንግሥት በወንድማችን ዮሴፍ አንጻር ቤተ ክርስትያን ላይ የሚያደርገውን ቀልድ ቀጥሎበታል፡፡

ሁላችንም እንደምናውቀው መምህር ዮሴፍ የታፈነው ዕለተ ቅዳሜ ከሥራ ገበታው ላይ እጅግ አጸያፊ በሆነ መልኩ፣ መታሰሩን እንኳን
ዲ/ን ዮሴፍ ፍሰሐ 

ለቤተሰብ እንዲናገር ሳይፈቅዱለት ነበር፡፡ ከዚያም በወንድሞች የየማጎሪያ ቤት ዳሰሳ ከብዙ ድካም በኋላ በማእከላዊ የቶርቸር ቻምበር ውስጥ ለብቻው ጨላማ ክፍል ውስጥ አስረውት የከረሙ መሆኑ ተደረሰበት፡፡ በጨለማ ቤት ባሰሩባቸው ቀናት ማንም ሳያውቅ ፍርድ ቤትም አቅርበውትም ነበር፡፡ ልብ አድርጉ! ያንን ያደረጉት ጠበቃ እንዲቆምለትም ሳይፈቅዱ፣ ቤተሰብ እንዲጠይቀውም ሳያደርጉ ነበር፡፡ 

ከሳንንት እንግልት በኋላ ቤተሰብ እንዲጠይቀው ፈቀዱ፣ ከዚያም የታሰረበትን ወሕኒ ቤትና የፈርድ ቤት ቀጠሮው ከታወቀ በኋላ ጠበቆች ቆሙለት፡፡ ባለፈው ፍርድ ቤት አቅርበውት ምንም በደል ስላላገኙበት ፖሊስ ተጨማሪ 10 ቀናት ያስፈልገኛል በማለቱ ለታኅሳስ 2 ቀጥረውት ነበር፡፡

 የታሰረው በፌስቡክ በለጠፈው ሆኖ ሳለ ሌላ በደል ፍለጋ ትርጉም የማይሰጥ ስለሆነ ቀጠሮው ማጠር አለበት የሚል ይግባኝ ጠበቆቹ ስላስገቡ ትናንት ከቀኑ ሰምንት ሰዓት ላይ በድጋሜ ፍርድ ቤት ቀርቦ ነበር፡፡ አሳፋሪው የፖሊስ መከራከሪያ 'ላይክና ሼር ያደረጉ አባላቱን እያፈላለኩ ነውና ከወጣ ተፈለጊዎቹን ይሰውርብኝል' የሚል በዐለም ላይ ተሰምቶ የማይታወቅን ደደብ ካልሆንክ ብቻ ልትናገረው የማትችለውን መከራከሪያ ቢያቀርብም ፍርዱ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ 8፡30 ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር፡፡ 

ወልዲያ ከተማ ውስጥ የሚገኙ በርካታ የዓብነት ተማሪዎች ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ታፍሰው መወሰዳቸው ታወቀ

DEC 01, 2025
የጠለፋ ወንጀል በኢትዮጵያ ተባብሷል
(መሠረት ሚድያ)- በቅርብ ወራት በበርካታ ከተሞች ውስጥ ወጣቶች ከየመንገዱ እና ከስራ ቦታ እየታፈሱ ለስልጠና ወደ ካምፖች እየገቡ 
እንደሆነ በተደጋጋሚ ያወጣናቸው መረጃዎች ጠቁመዋል። 
አሁን ከወደ ወልዲያ የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው በርካታ የዓብነት ተማሪዎች ባሳለፍነው ሳምንት ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ታፍሰው ተወስደዋል። 
ስልካቸውን ከተቀሙ በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት በሚሊሻዎች የተወሰዱት የዓብነት (የቤተክርስቲያን) ተማሪዎቹ በወልዲያ ከተማ የሚገኘው የቲንፋዝ ደብረ በረከት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርሰቲያን እና የሌሎች ቤተክርስቲያኖች ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል። 

"ዓራት ዓይናው ታላቁ አባት መላከ ገነት አምደብርሃን የኔታ ይባቤ በላይ ትላንት ምሽት ለዛሬ ሌሊት አጥቢያ አርፈዋል " - ቤተክርስቲያኗ

➡️ " የስኳር ህመም በፊትም አለባቸው፤ ግን አሞኝም ብለው ከጉባዔ አልወረዱም፤ ከተኙ በኋላ ነው ገደማያውያኑ 'ምን ነው'? 
መልአከ ገነት አምደብርሃን የኔታ ይባቤ በላይ

ሲሏቸው ማውራት አልቻሉም' ነው ያሉን" - የሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት

በሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት፣ "ክብረ ደናግል ናዳ ቅድስት ማርያም ገዳም" አበምኔት፣ የአራቱ ጉባዔያት መምህር መላከ ገነት አምደብርሃን የኔታ ይባቤ በላይ ማረፋቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ረፋድ ገልጻለች።

የቤተክርስቲያኗ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ መላከሰላም ሰለሞን ቶልቻ በሰጡን ቃል፣ " ዓራት ዓይናው ታላቁ አባት መላከ ገነት አምደብርሃን የኔታ ይባቤ በላይ ትላንት ምሽት ለዛሬ ሌሊት አጥቢያ አርፈዋል " ብለዋል።

በምዕራብ ሐረርጌ የታፈነው ጩኸት እና በአርሲ የቀጠለው ዘር ፍጅት!

ምዕራብ ሐረርጌ ዞን፣ ጭሮ ወረዳ፣ ላሎ ጉዶ ቀበሌ፣  ኢፈ ባስ (ifabaas) በምትባል የገጠር መንደር ውስጥ በኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም 
እናት ፓርቲ

ከምሽቱ 3:00 እልፌ ተስፋ ወሌ የሚባሉ እናት በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል። በዚኹ ቀበሌና በአጎራባች ቀበሌዎች ያብዶ ሸንበቆ፣ ረብሱ፣ ሼክ አደም፣ ሉጎ በርካታ ሃይማኖትና ማንነትን ማዕከል ያደረጉ ጭፍጨፋዎች የሚካሄዱባቸው ናቸው። ብንናገርም ሰሚ የለም። ሕዝቡና ሚዲያውም እኛን ረስቶናል ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች በምሬትና በፍርኃት ተውጠው። 

በወረዳው በቅርቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት የኾኑ ተፈሪ መንገሻ ከነ ባለቤቱ ቀለሟ በለጠ ጋር፣ ባለው መንገሻ፣ አሳምነው አባይነህ የተባሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በአሰቃቂ ኹኔታ በስለትና በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል። ግድያውን የሚፈጽመው በአካባቢው ሰዎች አጠራር ኦነግ ሸኔ(ራሱን ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል) ነው። 

ይኽን መረጃ እያጣራን ባለንበት አፍታ በአርሲ ዞን በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፣ በቀቅሳ ቀበሌ በአጨዳ ላይ የነበሩ ከ19 በላይ ገበሬዎች ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ታፍነው መወሰዳቸውን ከቦታው ለማረጋገጥ ችለናል። በዚኹ አካባቢ በቅርቡ ወንድማማቾችን ጨምሮ ሦስት ንጹሓን እንደተገደሉ ይታወሳል። 

Wednesday, December 3, 2025

ይድረስ ለኦርቶዶክሳውያን ሚዲያዎች



ይኽ ሰው አብደላ አማን(አብደላ ማይክሮ) ይባላል።በምሥራቅ አርሲ ዞን የ ሽርካ ወረዳ የምክር ቤት አባል ነው።የሽርካ  የኦርቶዶክሳውያን

ላይ በሚፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀል ከወረዳው አስተዳዳሪ እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉ ካድሬዎች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጃቸው እንዳለበት የታወቀ ነው አቶ አብደላ ግን ትልቅ ሚና ያለው ሰው ነው፦

፩  አራጁን ቡድን(የኦሮሞ ኢስላማዊ መንግሥት ታጣቂዎችን) የሚያንቀሳቅሰው እርሱ ነው

፪  መቀመጫውን ባሌ በረሃ ካደረገው አል ሸባብ  Al shabab ቡድን  ጋር በቀጥታ ግኑኝነት አለው

Tuesday, December 2, 2025

“ ስንዴውን እየሸከፈ ነው”

      “ስንዴውን እየሸከፈ ነው”

ጌታ ራሱን ከመሰለበት ምሳሌዎች ንጹሕ ዘር በሚዘራ ገበሬ ነው።እርሻውም ይህ ዓለም፣ ዘሩንም ወንጌል ነው።እንክርዳድም ክፉት
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ 

ዘሪውም ዲያብሎስ ነው።እንክርዳዱም የሚዘራው  ሰዎቹ ሲተኙ ነው። ሰዎቹ ያላቸው ታላላቁ የእግዚአብሔር ሰዎች ናቸው። ማንቀላፋታቸው ዕረፍታቸው ሲሆን ሰዎቹ ሲተኙ እንክርዳድ መዘራቱ ታላላቆቹ ሲያርፉ በዲያብሎስና ግብር አበሮቹ አዲስ እንክርዳድ ሥርዓት ይዘራልና።አብረውም እስከ መከር ይቆያሉ።መከሩ የዚህ ዓለም ማለቅ ሆኖ አጫጆቹም መልእክት ናቸው።ያን ጊዜ ንጉሥ ስንዴውን ከእንክርዳዱ የሚያበጥርበት የማያሳስት ሥልጣን የተባለ ነፋስ አለው።እንክርዳዱን በእሳት አቃጥሎ ስንዴውን በመንግሥተ ሰማያት ጎተራ ይሰበስባል ነበር የተማርነው።ማቴ፲፫፥፴፱-፵፪

የሥጋ ዓይን ሳይኖራቸው በነፍሳቸው  የሚያዩት የኔታ መጋቤ ምሥጢር ተሾመ ደግሞ አሁንም “ስንዴውን እየሸከፈ ነው አሉ”።በ፳፲፫ ዓም መጽሐፈ መነኮሳትን ከእርሳቸው እያሄድኩ ሳለ ወንበር እንዳበቃ አንድ ትልቅ ሰው እንዳረፉ ሰማን።የኔታም ካዘኑ በኋላ “ አይ እግዚአብሔር እኮ እንክርዳዱን ለማቃጠል ስንዴውን አስቀድሞ እየሸከፈ  ነው” አሉ። ምን ማለት ነው የኔታ ስላቸው፦ “ ሰዉ ከፍቷል፤አልመለስ ብሏል፤ ስለዚህ ወዳጆቹን አስቀድሞ ሸካክፎ በመከራ እሳት ሊገርፈን ይመስለኛል አሉ” ያን ጊዜም ጦርነት ውስጥ ነበርን። አሁንም እንደዚያው የመከራው እሳት እየገረፈን አለን።በጊዜው ተጨንቄ አሁንም የሚሆነውን ሁሉ እያየሁ እያሰብኳቸው ሳለ  እንዳረፉ ሰማሁ።