Friday, December 5, 2025

መምህር ዲ/ን ዮሴፍ ዛሬም በግፈኞች እሥር እንዲቀጥል ተደጓል! እግዚኦ ለዳኝነት!!

መምህር ዮሴፍ ዛሬም አልተፈታም፡፡ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ የተቀጠረ የነበረ ቢሆንም አሁንም ፖሊስ ይግባኝ በማለቱና ወንጀል
መምህር ዲ/ን ዮሴፍ

ሊያገኝበት ስላልቻል ለቀጣይ ማክሰኞ ቀጥረውታል፡፡ ለቀጣይም ዮሴፍ ላይ ወንጀል ማግኘት አይችልም፡፡ የማራዘሚያ ዘልዛላ ምክንያት ግን ይፈበርክ ይሆናል፡፡

ዮሴፍ እንዳይፈታ እየታገለ ያለው ታጋይ የሚባለው ቤተ ክርስቲያንን ይታገልና ሥርዓቱን ያገለግል ዘንድ በቤተ ክርስቲያን ስም የሆነ ተቋም ''እመራለሁ'' የሚል ሰው ነው፡፡ 

ምንም እንኳን አሁን እንደተገለጠው ዮሴፍ አንድ ታጋይ የሚባል የቀድሞ ደረሳ እስረኛ ቢሆንም ለዮሴፍ መንገላታት ግን ዋና ተጠያቂው የቤተ ክርስቲያን ጠላት የሆነው ሥርዓቱ ነው፡፡ እንደ ታጋይ ያሉ አረመኔዎች የግል ታሳሪዎቻቸውን ያለ ምንም ወንጀል በመንግሥት ማረሚያ ቤት የሚያጉሩ ከሆነ ተጠያቂው ሥርዓቱ ነው፡፡ 

ይኸ ሥርዓት ገና ከጥንስሱ የቤተ ክርስቲያን ጠላትነቱን ያስመሰከረና ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጥራዝ ነጠቆችን፣ ሆዳሞችንና ከሐዲዎችን በመሰብሰብ በራሷ ልጆች በሚመስል መልኩ በተደጋጋሚ እያቆሰላት ይገኛል፡፡ ሥርዓቱን የሚያገለግሉ፣ ቋንቋዋን የሚናገሩና አልባሳቷን የሚለብሱ ሰዎችን የሚፈልጋቸው ከውስጥ ያለውን መከራ ለማጽናት ነው፡፡ 

Thursday, December 4, 2025

✍️መንግሥት በወንድማችን ዮሴፍ አንጻር ቤተ ክርስትያን ላይ የሚያደርገውን ቀልድ ቀጥሎበታል፡፡

ሁላችንም እንደምናውቀው መምህር ዮሴፍ የታፈነው ዕለተ ቅዳሜ ከሥራ ገበታው ላይ እጅግ አጸያፊ በሆነ መልኩ፣ መታሰሩን እንኳን
ዲ/ን ዮሴፍ ፍሰሐ 

ለቤተሰብ እንዲናገር ሳይፈቅዱለት ነበር፡፡ ከዚያም በወንድሞች የየማጎሪያ ቤት ዳሰሳ ከብዙ ድካም በኋላ በማእከላዊ የቶርቸር ቻምበር ውስጥ ለብቻው ጨላማ ክፍል ውስጥ አስረውት የከረሙ መሆኑ ተደረሰበት፡፡ በጨለማ ቤት ባሰሩባቸው ቀናት ማንም ሳያውቅ ፍርድ ቤትም አቅርበውትም ነበር፡፡ ልብ አድርጉ! ያንን ያደረጉት ጠበቃ እንዲቆምለትም ሳይፈቅዱ፣ ቤተሰብ እንዲጠይቀውም ሳያደርጉ ነበር፡፡ 

ከሳንንት እንግልት በኋላ ቤተሰብ እንዲጠይቀው ፈቀዱ፣ ከዚያም የታሰረበትን ወሕኒ ቤትና የፈርድ ቤት ቀጠሮው ከታወቀ በኋላ ጠበቆች ቆሙለት፡፡ ባለፈው ፍርድ ቤት አቅርበውት ምንም በደል ስላላገኙበት ፖሊስ ተጨማሪ 10 ቀናት ያስፈልገኛል በማለቱ ለታኅሳስ 2 ቀጥረውት ነበር፡፡

 የታሰረው በፌስቡክ በለጠፈው ሆኖ ሳለ ሌላ በደል ፍለጋ ትርጉም የማይሰጥ ስለሆነ ቀጠሮው ማጠር አለበት የሚል ይግባኝ ጠበቆቹ ስላስገቡ ትናንት ከቀኑ ሰምንት ሰዓት ላይ በድጋሜ ፍርድ ቤት ቀርቦ ነበር፡፡ አሳፋሪው የፖሊስ መከራከሪያ 'ላይክና ሼር ያደረጉ አባላቱን እያፈላለኩ ነውና ከወጣ ተፈለጊዎቹን ይሰውርብኝል' የሚል በዐለም ላይ ተሰምቶ የማይታወቅን ደደብ ካልሆንክ ብቻ ልትናገረው የማትችለውን መከራከሪያ ቢያቀርብም ፍርዱ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ 8፡30 ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር፡፡ 

ወልዲያ ከተማ ውስጥ የሚገኙ በርካታ የዓብነት ተማሪዎች ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ታፍሰው መወሰዳቸው ታወቀ

DEC 01, 2025
የጠለፋ ወንጀል በኢትዮጵያ ተባብሷል
(መሠረት ሚድያ)- በቅርብ ወራት በበርካታ ከተሞች ውስጥ ወጣቶች ከየመንገዱ እና ከስራ ቦታ እየታፈሱ ለስልጠና ወደ ካምፖች እየገቡ 
እንደሆነ በተደጋጋሚ ያወጣናቸው መረጃዎች ጠቁመዋል። 
አሁን ከወደ ወልዲያ የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው በርካታ የዓብነት ተማሪዎች ባሳለፍነው ሳምንት ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ታፍሰው ተወስደዋል። 
ስልካቸውን ከተቀሙ በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት በሚሊሻዎች የተወሰዱት የዓብነት (የቤተክርስቲያን) ተማሪዎቹ በወልዲያ ከተማ የሚገኘው የቲንፋዝ ደብረ በረከት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርሰቲያን እና የሌሎች ቤተክርስቲያኖች ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል። 

"ዓራት ዓይናው ታላቁ አባት መላከ ገነት አምደብርሃን የኔታ ይባቤ በላይ ትላንት ምሽት ለዛሬ ሌሊት አጥቢያ አርፈዋል " - ቤተክርስቲያኗ

➡️ " የስኳር ህመም በፊትም አለባቸው፤ ግን አሞኝም ብለው ከጉባዔ አልወረዱም፤ ከተኙ በኋላ ነው ገደማያውያኑ 'ምን ነው'? 
መልአከ ገነት አምደብርሃን የኔታ ይባቤ በላይ

ሲሏቸው ማውራት አልቻሉም' ነው ያሉን" - የሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት

በሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት፣ "ክብረ ደናግል ናዳ ቅድስት ማርያም ገዳም" አበምኔት፣ የአራቱ ጉባዔያት መምህር መላከ ገነት አምደብርሃን የኔታ ይባቤ በላይ ማረፋቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ረፋድ ገልጻለች።

የቤተክርስቲያኗ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ መላከሰላም ሰለሞን ቶልቻ በሰጡን ቃል፣ " ዓራት ዓይናው ታላቁ አባት መላከ ገነት አምደብርሃን የኔታ ይባቤ በላይ ትላንት ምሽት ለዛሬ ሌሊት አጥቢያ አርፈዋል " ብለዋል።

በምዕራብ ሐረርጌ የታፈነው ጩኸት እና በአርሲ የቀጠለው ዘር ፍጅት!

ምዕራብ ሐረርጌ ዞን፣ ጭሮ ወረዳ፣ ላሎ ጉዶ ቀበሌ፣  ኢፈ ባስ (ifabaas) በምትባል የገጠር መንደር ውስጥ በኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም 
እናት ፓርቲ

ከምሽቱ 3:00 እልፌ ተስፋ ወሌ የሚባሉ እናት በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል። በዚኹ ቀበሌና በአጎራባች ቀበሌዎች ያብዶ ሸንበቆ፣ ረብሱ፣ ሼክ አደም፣ ሉጎ በርካታ ሃይማኖትና ማንነትን ማዕከል ያደረጉ ጭፍጨፋዎች የሚካሄዱባቸው ናቸው። ብንናገርም ሰሚ የለም። ሕዝቡና ሚዲያውም እኛን ረስቶናል ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች በምሬትና በፍርኃት ተውጠው። 

በወረዳው በቅርቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት የኾኑ ተፈሪ መንገሻ ከነ ባለቤቱ ቀለሟ በለጠ ጋር፣ ባለው መንገሻ፣ አሳምነው አባይነህ የተባሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በአሰቃቂ ኹኔታ በስለትና በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል። ግድያውን የሚፈጽመው በአካባቢው ሰዎች አጠራር ኦነግ ሸኔ(ራሱን ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል) ነው። 

ይኽን መረጃ እያጣራን ባለንበት አፍታ በአርሲ ዞን በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፣ በቀቅሳ ቀበሌ በአጨዳ ላይ የነበሩ ከ19 በላይ ገበሬዎች ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ታፍነው መወሰዳቸውን ከቦታው ለማረጋገጥ ችለናል። በዚኹ አካባቢ በቅርቡ ወንድማማቾችን ጨምሮ ሦስት ንጹሓን እንደተገደሉ ይታወሳል። 

Wednesday, December 3, 2025

ይድረስ ለኦርቶዶክሳውያን ሚዲያዎች



ይኽ ሰው አብደላ አማን(አብደላ ማይክሮ) ይባላል።በምሥራቅ አርሲ ዞን የ ሽርካ ወረዳ የምክር ቤት አባል ነው።የሽርካ  የኦርቶዶክሳውያን

ላይ በሚፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀል ከወረዳው አስተዳዳሪ እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉ ካድሬዎች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጃቸው እንዳለበት የታወቀ ነው አቶ አብደላ ግን ትልቅ ሚና ያለው ሰው ነው፦

፩  አራጁን ቡድን(የኦሮሞ ኢስላማዊ መንግሥት ታጣቂዎችን) የሚያንቀሳቅሰው እርሱ ነው

፪  መቀመጫውን ባሌ በረሃ ካደረገው አል ሸባብ  Al shabab ቡድን  ጋር በቀጥታ ግኑኝነት አለው

Tuesday, December 2, 2025

“ ስንዴውን እየሸከፈ ነው”

      “ስንዴውን እየሸከፈ ነው”

ጌታ ራሱን ከመሰለበት ምሳሌዎች ንጹሕ ዘር በሚዘራ ገበሬ ነው።እርሻውም ይህ ዓለም፣ ዘሩንም ወንጌል ነው።እንክርዳድም ክፉት
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ 

ዘሪውም ዲያብሎስ ነው።እንክርዳዱም የሚዘራው  ሰዎቹ ሲተኙ ነው። ሰዎቹ ያላቸው ታላላቁ የእግዚአብሔር ሰዎች ናቸው። ማንቀላፋታቸው ዕረፍታቸው ሲሆን ሰዎቹ ሲተኙ እንክርዳድ መዘራቱ ታላላቆቹ ሲያርፉ በዲያብሎስና ግብር አበሮቹ አዲስ እንክርዳድ ሥርዓት ይዘራልና።አብረውም እስከ መከር ይቆያሉ።መከሩ የዚህ ዓለም ማለቅ ሆኖ አጫጆቹም መልእክት ናቸው።ያን ጊዜ ንጉሥ ስንዴውን ከእንክርዳዱ የሚያበጥርበት የማያሳስት ሥልጣን የተባለ ነፋስ አለው።እንክርዳዱን በእሳት አቃጥሎ ስንዴውን በመንግሥተ ሰማያት ጎተራ ይሰበስባል ነበር የተማርነው።ማቴ፲፫፥፴፱-፵፪

የሥጋ ዓይን ሳይኖራቸው በነፍሳቸው  የሚያዩት የኔታ መጋቤ ምሥጢር ተሾመ ደግሞ አሁንም “ስንዴውን እየሸከፈ ነው አሉ”።በ፳፲፫ ዓም መጽሐፈ መነኮሳትን ከእርሳቸው እያሄድኩ ሳለ ወንበር እንዳበቃ አንድ ትልቅ ሰው እንዳረፉ ሰማን።የኔታም ካዘኑ በኋላ “ አይ እግዚአብሔር እኮ እንክርዳዱን ለማቃጠል ስንዴውን አስቀድሞ እየሸከፈ  ነው” አሉ። ምን ማለት ነው የኔታ ስላቸው፦ “ ሰዉ ከፍቷል፤አልመለስ ብሏል፤ ስለዚህ ወዳጆቹን አስቀድሞ ሸካክፎ በመከራ እሳት ሊገርፈን ይመስለኛል አሉ” ያን ጊዜም ጦርነት ውስጥ ነበርን። አሁንም እንደዚያው የመከራው እሳት እየገረፈን አለን።በጊዜው ተጨንቄ አሁንም የሚሆነውን ሁሉ እያየሁ እያሰብኳቸው ሳለ  እንዳረፉ ሰማሁ።