Friday, June 8, 2012

ስኳር



clik here for pdf 
አንድ መምህር ሁለት ትልልቅ የመስተዋት ገንቦዎች ይዞ ወደ ክፍል መጣ፡፡ ሦስት   ተማሪዎች ደግሞበካርቶን ሌሎች ሦስት ነገሮችን ተሸክመውለታል፡፡ ተማሪዎቹ ከመቀመጫ ተነሥተው ተቀበሉት፡፡
መምህሩ ትልልቁን የመስተዋት ገንቦዎች በተማሪዎቹ ፊት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠው፡፡ ሦስቱንካርቶኖቹን ደግሞ በጎን አደረጋቸው፡፡ መጀመርያ ትልልቅ ድንጋዮች አነሳና በአንደኛው የመስተዋትገንቦ ውስጥ እስካፉ ድረስ ከተታቸው፡፡ ከዚያም ተማሪዎቹን አንድ ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
 «ይህ የመስተዋት ገንቦ ሙሉ ነውን?´
ተማሪዎቹም በአዎንታ ራሳቸውን ነቀነቁ፡፡
ከዚያም ቀጠለና ትንንሽ የከበሩ ድንጋዮችን አንሥቶ ወደ መስተዋቱ ገንቦ ውስጥ ከተታቸው፡፡በድንጋዮችና በድንጋዮቹ መካከል በሚገኙ ባዶ ቦታዎች ወስጥ እየገቡ የከበሩት ድንጋዮች ገንቦውንሞሉት፡፡ መምህሩም ተማሪዎቹን በድጋሚ ጠየቃቸው፡፡
«አሁንስ የመስተዋቱ ገንቦ ሙሉ ነውን?´
ተማሪዎቹም ሙሉ መሆኑን ተናገሩ፡፡
ቀጠለና መምህሩ ከሦስተኛው ካርቶን ስኳር እያፈሰ ወደ መስተዋቱ ገንቦ ውስጥ ከተተ፡፡ በቀሪውባዶ ቦታ ውስጥ እየገባ ስኳሩ ሞላ፡፡ መምህሩም የተለመደ ጥያቄውን ጠየቀ፡፡ «የመስተዋቱ ገንቦሙሉ ነውን?´
ተማሪዎቹም በአዎንታ መለሱ፡፡
እንደገና መምህሩ ሁለተኛውን የመስተዋት ገንቦ አቀረበ፡፡ ከዚያም በተቃራኒው ስኳሩን በመስተዋቱገንቦ ውስጥ ሞላበት፡፡ ተማሪዎቹንም ገንቦው ሙሉ መሆንና አለመሆኑን ጠየቀ፡፡ ተማሪዎቹም ሙሉመሆኑን መሰከሩ፡፡ በመቀጠል ድንጋዮቹን ለማስገባት ሞከረ፡፡ ነገር ግን ስኳሩ ሁሉንም ቦታስለያዘው ማስገባት አልቻለም፡፡ ለከበሩ ድንጋዮች የሚሆን ቦታም አላገኘም፡፡
መምህሩ ከሁለቱ የመስተዋት ገንቦዎች ፎት ቆመና ተማሪዎቹን ሃሳብ ጠየቃቸው፡፡ የመጀመርያውየመስተዋት ገንቦ ሦስቱንም ነገሮች ሲያስገባ ሁለተኛው ገንቦ ለምን አልቻለም? የመጀመርያው ገንቦድንጋዩን ሲያስገባ ሙሉ ነበረ፡፡ የከበሩ ድንጋዮች ሲጨመሩም ሙሉ ነበረ፡፡ ስኳሩም ሲጨመርሙሉ ነበረ፡፡ ሁለተኛው ገንቦ ግን በስኳሩ ብቻ ሞላ፡፡ ለምን?
በሕይወታችሁ ውስጥ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ አለ መምህሩ፡፡ የመስተዋት ገንቦ ሕይወታችሁ ናት፡፡ድንጋዩ፣ የከበሩት ድንጋዮችና ስኳሩ ደግሞ በሕይወታችሁ ውስጥ ቅድሚያ የምትሰጧቸው ጉዳዮችናቸው፡፡ ሰው በሕይወቱ ውስጥ የሚያስፈልጉትም ሆኑ የሚፈልጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡የሚያገኙትም ሆኑ የሚያገኛቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ የሚገጥማቸውም ሆኑ የሚያጋጥሙት ብዙአማራጮች አሉ፡፡ ሁሉም ቦታ ይይዛሉ፡፡
አንዳንዶቹ ነገሮች እነርሱ በሕይወታችን ቀድመው ከገቡ ለሌሎቹ የሚሆን ቦታ የማይኖራቸውናቸው፡፡ እነርሱ ብቻ ከሞሉ የሌሎችን ቦታ ይይዛሉ፡፡ ለሌሎች ቦታ እንተው ካልን ደግሞ እነርሱይጎድላሉ፡፡ በሌላም በኩል አንዳንዶች እነርሱ በሕይወታችን ቢሞሉም ለሌሎች ቦታ ያላቸውናቸው፡፡
በመጀመርያው ገንቦ ውስጥ ድንጋዩን ስናስገባው ገንቦው ሙሉ ነበረ፡፡ ነገር ግን ለሌሎች መግቢያየሚሆን ቦታ ነበረው፡፡ ድንጋዩ ምንድን ነው? በሕይወታችን የመጀመርያ ቦታ ልንሰጣቸው የሚገቡነገሮች አሉ፡፡ እምነታችን፤የሕይወት መመርያዎቻችን፤ ማንነታችን፣ ቤተሰባችን፣ ሀገራችን፣ለእውነት የምናደርገው ተጋድሎ እነዚህ መጀመርያ በሕይወት ገንቧችን ውስጥ ከገቡ ሕይወታችንሙሉ ትሆናለች፡፡
ተመልከቱ መጀመርያ ድንጋዩ ከገባ በኋላ ብንተወው እንኳን ገንቦው ግን ሙሉ ነበር የሚሆነው፡፡ ማለት ምን ማለት ነው፡፡ ገንቦው ሙሉም ጎዶሎም ነበር ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ጎዶሎነቱ ሙላቱንአልቀነሰውም፡፡በቃ ገንቦው ሊይዘው የሚችለው የድንጋይ መጠን ያንን ብቻ ነበረ፡፡ ስለዚህ ሙሉነበረ፡፡ ገንቦውን ሙሉ ለማድረግም እርሱ ብቻ በቂ ነበረ፡፡ ነገር ግን ቦታም ነበረው፡፡
ከላይ ያነሣናቸው ነገሮች በሕይወታችን ካሉ ሕይወታችን ሙሉ ትሆናለች፡፡ ነገር ግን ለሌሎችምነገሮች ቦታ ይኖሯታል፡፡ ምናልባት ግን የከበሩ ድንጋዮችና ስኳሩ እንኳን ባይኖር ሙሉ እንደሆነችትቀጥላለች፡፡ ሀብታም አንሆን ይሆናል፤ ታዋቂ አንሆን ይሆናል፤ ሁሉ ነገር የተሳካልን አንሆንይሆናል፤ ከኛ ተርፎ ለሌለ የምንሰጥ አንሆን ይሆናል፤ ለመትረፍረፍና ለመዝናናት የሚበቃ ነገርአይኖረን ይሆናል፡፡ እንዲህም ሆኖ እንኳን ሕይወታችን ግን ሙሉ ትሆናለች፡፡
ሕይወትን የሚሞላት እንደ ድንጋዩ ጠንከርና ከፍ ያሉ ነገሮች ናቸው፡፡ እምነትና የሕይወትመመርያዎች ዋነኛ የሕይወት ሙላቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ካሉ የከበረው ድንጋይና ስኳሩ ባይኖሩእንኳን ሕይወት ግን ሙሉ መሆንዋ አይቀርም፡፡ ሕይወትን በዋናነት የሚሞሏት እምነትና የሕይወትመመርያዎች ወይንም አቋሞች ናቸው፡፡ ችግር ችግር የሚሆነው በራሱ ችግር ስለሆነ አይደለም፡፡ችግር ችግር የሚሆነው በችግር ዓይን ሲያዩት ነው፡፡
በኢንዱስትሪ አብዮት ዘመን ሁለት ሰዎች ከአንድ የጫማ ፋብሪካ ተልከው ወደ አፍሪካ መጡ፡፡የጫማ ገበያን ጉዳይ ሊያጠኑ፡፡ ሁለቱም ሰዎች የተለያያ ሪፖርት ይዘው ተመለሱ፡፡ የመጀመርያውሰው «እዚያ ለጫማ የሚሆን ገበያ የለም፡፡ ምክንያቱም ሁሉም ሰዎች በባዶ እግራቸው ነውየሚሄዱት´ አለ፡፡ ሁለተኛው ሰውዬ ደግሞ «እዚያ ከፍተኛ የጫማ ገበያ አለ፤ ምክንያቱም አንድምጫማ ያለው ሰው የለምና´ ብሎ ሪፖርት አቀረበ፡፡
አያችሁ ሁለቱም በአንድ እውነታ ላይ ተስማምተዋል፡፡ የሄዱበት ቦታ ጫማ ያደረገ ሰው የለም፡፡በመርሐቸው ግን ተለየይተዋል፡፡ አንዱ እንደ ችግር የቆጠረውን ሌላው እንደ ዕድል ቆጥሮታል፡፡ስለዚህ በሕይወታችሁ ውስጥ አምነትና መርሕ ካለ ሕይወትን ሙሉ ያደርጋታል፡፡
 ማለት ግን ለሌሎች ነገሮች ቦታ አይኖራችሁም ማለት አይደለም፡፡ አሉ ሌሎች ነገሮች፡፡ትምህርት፣ ሥራ፣ ዕድገት፣ ትዳር፣ ልጆች፣ ሌሎችም ነገሮች፡፡ በእምነትና በመርሕ አስቀድሞሕይወቱ የተሞላ ሰው ለእነዚህ ነገሮች በቂ ቦታ አለው፡፡ ሳይጎድ ልበት መሙላት የሚችል ቦታአለው፡፡ የዚያኛውን ቦታ ሳያስለቅቅ ነገር ግን ለእነዚህም ቦታ ይኖረዋል፡፡
አለ ደግሞ ሦስተኛው ነገር፡፡ ስኳሩ፡፡ እንደምታውቁት ዛሬ ዛሬ ብዙ ሰዎች ስኳር እየተው ነው፡፡ካልሆነም ደግሞ እየቀነሱ ነው፡፡ በሕይወታችንም እንደ ስኳር ያሉ ነገሮች አሉ፡፡ ለእነርሱም ቢሆንግን ሕይወታችን ቦታ አላት፡፡ ግን መጀመርያ ድንጋዩና የከበሩት ድንጋዮች ከገቡ ነው፡፡
አስቀድማችሁ ስኳሩን ቦታ ካስያዛችሁት ለሌላ ነገር የሚሆን ቦታ አታገኙም፡፡እንዲህ ያደረጉ ሰዎችአሉ፡፡ መጀመርያ ሕይወታቸውን በትርኪ ምርኪ ነገር የሞሉ፡፡ በመዝናናት፤ በክብርና ዝና፤በቧልትና ቀልድ፤ የሞሉ ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች በኋላ ለሌሎች የሚሆኑ ቦታ አያገኙም፡፡ካልሆነም የግድ የእነዚያን ቦታ ማስለቀቅ ይኖርባቸዋል፡፡ የገባን ማስወጣት ደግሞ ቀላል አይደለም፡፡
አንዳንዶች ከትዳር በፊት የለመዱትን ስኳር በትዳር ወቅት ማስለቀቅ አቅቷቸው መከራ ያያሉ፡፡አንዳንዶች ከሥልጣን በፊት የለመዱትን ስኳር መላቀቅ አቅቷቸው ለመርሕና እምነት ቦታአጥተዋል፡፡ አንዳንዶች ከትምህርት በፊት የለመዱትን ክፉ ስኳር በዕውቀት መተካት አቅቷቸውይሰቃያሉ፡፡
ለመሆኑ በገንዘብ፣ በሥልጣን፣ በቆንጆ ወንዶችና ሴቶች፣ በግብዣና በስጦታ በቀላ የሚደለሉ ሰዎችአላያችሁም? ለምን ይመስላችኋል? እነዚህ ሰዎች ሕይወታቸው በስኳሩ ብቻ የተሞላ ስለሆነ ነው፡፡በሕይወታቸው ውስጥ ምንም ዓይነት ጠንካራ ዐለት የለም፡፡ ምንም ዓይነት የከበረ ድንጋይአልገባም፡፡ እነርሱ በስኳር ብቻ የተሞሉ ናቸው፡፡
ያንን ስኳር ደግሞ ማሟሟት ቀላል ነው፡፡ ዐለቱ ግን አይሟሟም፡፡ የለመዱትን ስኳር እያላሱእንደፈለጉ እምነታቸውንም ሆነ አመለካከታቸውን መቀያየር ቀላል ነው፡፡ አያችሁ በዐለት የተሞሉሰዎች ውስጥ የተወሰነ ስኳር መክተት የምትችሉትን ያህል በስኳር የተሞሉ ሰዎች ውስጥ ግንየተወሰነ ዐለት መክተት አትችሉም፡፡
እናም እነዚህ ሰዎች ለሕይወት ርባና ያለው ምንም ዓይነት ፋይዳ የላቸውም፡፡ እነርሱ ገንዘብእስከተከፈላቸው ድረስ ለየትኛውም ቡድን ይጫወታሉ፡፡ ዛሬ ገጥመውት ከእጁ ዋንጫ የነጠቁትንቡድን ነገ ደግሞ አብረውት ሆነው ዋንጫውን ለማንሳት ዝግጁ ናቸው፡፡ ሥልጣንና ክብር እስካገኙድረስ ከመላእክት ወገን ወርደው ከሰይጣን ጋር ለመሰለፍ አይዳግታቸውም፡፡
ለእነዚህ ሰዎች በሕይወታቸው ሜዳ ላይ ምንም ዐይነት መሥመር የላቸውም፡፡ አረንጓዴም፤ ቢጫምሆነ ቀይ መሥመር የላቸውም፡፡ ሁሉንም ይሻገሩታል፡፡ «ከዚህ በመለስ ከመጣማ ሕይወቴ ያልፋልእንጂ፤´ የሚሉት ነገር የለም፡፡ አካባቢያቸውን ለመለወጥ ሳይሆን እንደ እስስት ከአካባቢያቸው ጋርለመለወጥ ዝግጁ ናቸው፡፡ እንደ ስኳር ለመድረቅም፤ ለመሟሟትም ይችላሉና፡፡
ሰው ሲፈጠር ለሁለቱ ነገሮች የተፈጠረ መሆኑን ተፈጥሮው ይነግረናል፡፡ አእምሮ፣ ልቡናና ኅሊናእንዲኖረን የተደረገው ለምን ይመስላችኋል? አእምሮ ለማወቂያ ነው፡፡ ዓለምን የምናውቅበት፡፡በአምስቱ የስሜት ሕዋሳት በኩል በሚገባው ዕውቀት የምንረዳበት፡፡ ኅሊናስ? ኅሊናማ የሕይወትየምትባለው መርከብ ካፒቴኗ ነው፡፡ ሕይወት በዚህ ካፒቴን ካልተመራች በማዕበል መካከልእንደተተወች የነጋዴዎች መርከብ ትሆናለች፡፡ ኅሊና የተቀመጠው ሕይወት በመርሕ እንድትመራነው፡፡ አንድ ሰው እሺም እምቢም የሚላቸው፤ የሚያከብራቸውና የሚሞትላቸው፤የሚታገልላቸውና፤ መሥዋዕትነት የሚከፍልላቸው መርሖች ከሌሉት እርሱ ሰው ሳይሆን ካልዕፍጥረት ነው ማለት ነው፡፡
ልቡናስ ምንድን ነው? ልቡና የእምነት ቦታ ነው፡፡ ምንም እንመን ምን፣ ግን እምነት ያስፈልጋል፡፡የሚያበረታና የሚያጠነክር፤ ኃይልና ብርታት የሚሆን፤ የማይታዩትን ነገሮች ልናይበት የምንችል፤ከሞት ወዲያ ዓላማ እንዲኖረን የሚያደርግ፤ ሞትን ሊያሸንፍ የሚችል እምነት፡፡ እነዚህ ናቸውዐለቶቹ፡፡ እነዚህም ናቸው የከበሩት ድንጋዮቹ፡፡ ከእነዚህ በመለስ ያለው ቢመጣ የማይጨምር፤ቢቀርም የማያጎድል ስኳር ነው፡፡ ችግሩ አስቀድሞ ስኳሩ ከሞላ ለሌሎች ነገሮች ቦታ የለውም፡፡
አሌክሳንድርያ፣ ቨርጆንያ፣ ዩኤስ 
source: www.danielkibret.com የተወሰደ

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

No comments:

Post a Comment