Thursday, May 17, 2012

የቅዱስ ሲኖዶስ ስድስተኛ ቀን ውሎ ሪፖርታዥ


·      ኮሚቴው ፍጹም ውግዘት የሚገባቸውን የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ እንቅስቃሴ አራማጅ ማኅበራትና ግለሰቦች ለይቷል - ማኅበረ ሰላማ፣ ማኅበረ በኵር፣ የምሥራች አገልግሎት፣ አንቀጸ ብርሃን፣ የቅድስት ልደታ ለማርያም መንፈሳዊ ማኅበር፣ የኢትዮጵያ መንፈሳዊ ተሐድሶ ኅብረት፣ አሸናፊ መኰንን፣ አግዛቸው ተፈራ፣ ጽጌ ስጦታው እና ግርማ በቀለ ይገኙባቸዋል።
·         “ሃይማኖቴ እንደ አባቶቼ ነው” ያሉት የአባ ሰረቀ እና “የቅን ልቦና የመንፈሳዊና የፈውስ አገልግሎትን ያቋቋምኹት ልጆቼን የማበላቸው ስለተቸገርኹ ነው” ያሉት የ‹ሊቀ ካህናት› ጌታቸው ዶኒ ጉዳይ ያለውሳኔ ሐሳብ ለምልአተ ጉባኤው ውሳኔ ቀርቧል።
·    አባ ጳውሎስ ከጥንተ አብሶ ጋራ በተያያዘ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕና እንዲመሰክሩ ሊጠየቁ ይችላሉ።

·         ሊቃውንት ጉባኤው ተደጋጋሚ ጥሪ አድርጎለት ያልቀረበው በጋሻው ደሳለኝ ዛሬ ጠዋት የሊቃውንት ጉባኤውን ሰብሳቢ በእጅጋየሁ በየነ አማላጅነት ሲለማመጥ ታይቷል፤ ሊቃውንት ጉባኤው “በአንድ ወቅት በራስ ቅል ኮረብታ ላይ ኢየሱስና ዲያቢሎስ ቁማር ተጫወቱ . . . ዲያቢሎስም በጨበጣ ገባ” የሚለውና ሌሎቹም ጥንቃቄ የጎደላቸው ንግግሮቹ ፍጹም ውግዘት የሚገባቸው እንደኾኑ አመልክቷል።
·         የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን አመራርና መዋቅር ይሻሻላል፤ በጠቅላላ ጉባኤና በቦርድ ይመራል፤ የኮሚሽኑ ሊቀ ጳጳስ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር እንደሚኾኑ ተጠቁሟል።
·         የማኅበራት መመሪያ ረቂቅ ለውይይት ቀርቧል፤ አሁን ባሉበት አኳኋን ከቀጠሉ “ሌላ ሲኖዶስ ይኾናሉ፤ የፖሊቲካ ዓላማ ማስፈጸሚያ ይኾናሉ፤ በቀኝ ዘመምና ግራ ዘመም አቋም ቤተ ክርስቲያኒቷን ይውጣሉ/ይከፍላሉ” የሚል ስጋት የቀረበባቸው ማኅበራት ንብረት በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ተጠቃልሎ እንዲተዳደር ሐሳብ ቀርቧል፤ የመመሪያውን ረቂቅ በጥንቃቄ የተመለከቱት የምልአተ ጉባኤው አባላት ጉዳዩ በይደር እንዲታይ አድርገዋል።
(ደጀ ሰላም፤ ግንቦት 9/2004 ዓ.ም፤ May 17/ 2012)፦ የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በግንቦት 8ቀን 2004 . ስድስተኛ ቀን ውሎው በፕሮቴስታንት ድርጅቶች ከፍተኛ ድጋፍ እየተደረገላቸው የቤተክርስቲያናችንን ትምህርተ ሃይማኖት ለማፋለስ፣ ሥርዐተ እምነቷን ለመለወጥ፣ አገልጋዩንና ምእመኑንለመከፋፈል በቡድንና በድርጅት ኾነው በመንቀሳቀስ ላይ ስለሚገኙት የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ አራማጅማኅበራትና ግለሰቦች የተዘጋጀውን ሪፖርት አዳምጧል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶሱ በአጀንዳ . (13) ላይ ስለ ሃይማኖት ሕጸጽ በተመለከተው ርእሰ ጉዳይ በጥቅምቱ ቅዱስሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ ከሊቃውንት ጉባኤ ጋራ በመኾን የቀረቡ ማስረጃዎችን መርምረው የውሳኔ ሐሳብየሚያቀርቡ ሰባት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በአባልነት የሚገኙበት ኮሚቴ ሠይሞ ነበር፡፡

በወቅቱ የኮሚቴው አባላት እንዲኾኑ ተመርጠው የነበሩት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፡ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕአቡነ ገሪማ፣ ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ፣ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ፣ ብፁዕ አቡነ እንድርያስና ብፁዕ አቡነ ያሬድ ነበሩ፡፡ጥቅምት 20 ቀን 2004 . ከተሠየመው ከእኒህ የኮሚቴው አባላት መካከል ሦስቱ (አቡነ ናትናኤል፣ አቡነቄርሎስ እና አቡነ እንድርያስበተለያየ ምክንያት መቀጠል ስላልቻሉ ቋሚ ሲኖዶሱ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስን፣ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስንና ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስን ተክቷል፡፡

ኮሚቴው ከሊቃውንት ጉባኤው የቀረበለትና መርምሮ በትናትናው ዕለት ከቀትር በኋላ በጸሐፊው በኩል ለቅዱስሲኖዶስ በንባብ ያሰማው ሪፖርት ባለ 60 ገጽ ሲኾን በዛሬው ዕለት ምልአተ ጉባኤው በሪፖርቱ ላይ በመወያየትየውሳኔ ሐሳቡን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ሪፖርቱ በፕሮቴስንታንት ድርጅቶች ከፍተኛ ድጋፍ እየተደረገላቸው ኦርቶዶክሳውያን መስለው በሁሉም የቤተክርስቲያን እንቅስቃሴዎች በመሳተፍ እና የአስተዳደር መዋቅሮች ውስጥ በመሰግሰግ ፕሮቴስታንታዊ አጀንዳቸውንለማስፈጸም ከሚንቀሳቀሱት ማኅበራት መካከል በስምንቱ ላይ ያተኮሩ የኅትመት ውጤቶችን፣ የድምፅ እና ምስልማስረጃዎችን መርምሯል፡፡

የፕሮቴስታንት እምነት ተቋማት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋራ ያላቸውን የመሠረተ እምነት/ዶግማልዩነት /ድንበርአጥፍተው ቤተ ክርስቲያናችንን በቁጥጥር ሥር አውለው ባለችበት ፕሮቴስታንታዊማድረግ ወይም ቤተ ክርስቲያናችንን  የጦርነት ቀጣና በማድረግ እንደ ሕንድ ቤተ ክርስቲያን ለሁለት መክፈልዓላማ ያላቸው ማኅበራቱ በአሁኑ ሰዓት በሚያወጧቸው መጻሕፍትና መጽሔቶች እንዲሁም በራሪ ወረቀቶችየቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ በግልጽ ይቃወማሉ፤ አገልጋዩና ምእመኑ በማይመች አካሄድ እንዲጠመድ እናበዘረኝነት እንዲከፋፈል ጭምር ይንቀሳቀሳሉ፡፡ ይህም በማስረጃ ተደግፎ የቀረበ በመኾኑ ፍጹም መወገዝያለባቸው ማኅበራት ተለይተው ቀርበዋል፡፡

ከእኒህም ውስጥ ኮሚቴው ፍጹም ውግዘት እንዲተላለፍባቸው የውሳኔ ሐሳብ ከቀረበባቸውየፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ አራማጅ ማኅበራት መካከል፡-

1.   ማኅበረ ሰላማ - በክልል ትግራይ ፍትሕ ቢሮ ተመዝግቦ ፈቃድ ባወጣበት ስሙ ማኅበረ ሰላማ ምትሕግጋዝማኅበር (Abune Selama Self Help Associationእየተባለ የሚጠራና ዋና /ቤቱ መቐለ የሚገኝ ነው፡፡ባወጣው ፈቃድ መሠረት በልማት ሥራ ላይ መሳተፍ ሲገባው ከሕገ ወጥ ባሕታውያንና ሌሎች የተሐድሶማኅበራት ጋራ በመቀናጀት ‹‹በገዳማት ላይ ጥናት ማድረግ›› በሚል ሰበብ በቅርሶች ላይ ከፍተኛ ዘመቻበማካሄድ ማንነትን ለማጥፋትና በአቋራጭ ለመክበር ይንቀሳቀሳል፤ ዘረኝነትን ያስፋፋል፡፡ የአሲራ መቲራውገዳም አበምኔት ነኝ ባዩ አባ ገብረ መድኅን ገብረ ጊዮርጊስ ከማኅበሩ መሪዎች ጋራ በድብቅ በመገናኘት ዕቅዱንለማስፈጸም ይንቀሳቀሳል፡፡

2.   ማኅበረ በኵር - 1983 . የተመሠረተ ሲኾን መሥራቹ 1953 . ከቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊኮሌጅ የተባረረው መሠረት ስብሐት ለአብ ነው፡፡ ከምሥረታው ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በፕሮቴስታንቶች ድጋፍላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ሌሎች የተሐድሶ ኑፋቄ ማኅበራት ‹‹አርኣያችን ነው›› ይሉታል፡፡ ጮራ› የተሰኘመጽሔት ያሳትማል፡፡ መጽሔቱን በሕገ ወጥ መንገድ ለብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ለሰንበት /ቤቶችና ለከፍተኛትምህርት ተቋማት ግቢ ግባኤያት ይልካሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት  አግዛቸው ተፈራ የተባለው በዋና አዘጋጅነትበሚሠራበት መጽሔት የጸሎት መጻሕፍትን ይቃወማሉ፤ አባቶችን ይዘልፋሉ፤ አዋልድ መጻሕፍትን አይቀበሉም፤‹‹ቅዱሳት ሥዕላት አያስፈልጉም›› ይላሉ፤ ‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ አሁንም አማላጅ ነው›› ሥልጣነ ክህነትንአይቀበሉም፤ የእምነት ልዩነት ድንበርን ያፈርሳሉ፤ ‹‹ቅዱስ ቍርባን መታሰቢያ ነው፤ ውላጤ ኅብስት የለም››ይላሉ፤ ምስጢረ ሜሮንን ይቃወማሉ፤ ‹‹ሥጋ በተዋሕዶ የባሕርይ አምላክ አልኾነም›› ይላሉ፡፡

3.   የምሥራች አገልግሎት - 1990 . የተመሠረተና አሸናፊ ሲሳይ በተባለ ግለሰብ የሚመራ ሲኾን‹‹ቤተ ክርስቲያን የውጊያ ቀጣና ናት›› በማለት ለእንቅስቃሴው የሚረዱ 34,000 ‹‹እርሾዎችን›› በቤተክርስቲያን ውስጥ ለመሰግሰግ ከፍተኛ የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ የሚደረግለት፣ እያንዳንዳቸው 100 - 160አባላት ባሉት ኅቡእ ቡድን (Cell basedየሚንቀሳቀስ አካል ነው፡፡ ‹‹ፕሮቴስታንት እና ኦርቶዶክሳውያንበመሠረተ እምነት አንድ ናቸው›› ከሣቴ ብርሃን ከተባለው ድርጅት ጋራ አንድ ዐይነት ዓላማ ያራምዳል፤የክርስቶስን አምላክነት በአግባቡ አያምንም፤ ምንኵስናን ይቃወማል፤ አዋልድ መጻሕፍትን አይቀበልም፡፡

4.   አንቀጸ ብርሃን - ከሰበታ መካነ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት /ቤትተለይቶ የወጣው አሸናፊ መኰንን የሚያሳትማቸውን የኑፋቄ መጻሕፍት ያስተዋውቃል፡፡ በሌላ ስያሜው ራሱን‹‹ማኅበረ መንፈስ ቅዱስ›› እያለ ይጠራል፡፡ ‹‹የኢ////ያን እምነትና ሥርዐት የጠበቀ መንፈሳዊ ጽሑፍ››በሚል በኅቡእ በሚያሰራጫቸው ጽሑፎቹ ምሥጢረ ሥላሴን አፋልሶ ያስተምራል፤ ምስጢረ ሥጋዌን በማፋለስቅብዐትን ይሰብካል፤ በካህን ፊት የሚደረግ ኑዛዜን ይቃወማል፡፡

5.   የቅድስት ልደታ ለማርያም መንፈሳዊ ማኅበር - በኑፋቄያቸው ከማኅደረ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ተክለ ሳዊሮስ ሰንበት /ቤት የተሰናበቱ ተወግዞ የተባረረው የሃይማኖተ አበው ማኅበር ሰለባዎች ነው፡፡አቶ መስፍን በተባለ ግለሰብ ይመራል፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ወደ ፕሮቴስታንትነት መቀየራቸውን ሳያውቁትሃይማኖታቸውን የሚያስክዱ የርቀት ትምህርቶችን ይሰጣል፤ ኅትመቶችን ያሰራጫል፤ ቤተ ክርስቲያንን በግልጽይዘልፋል፤ የሥጋ ወደሙን አማናዊነት አያምንም፡፡

6.   የእውነት ቃል አገልግሎት - ድርጅቱ ይህን ስያሜ ከመያዙ በፊት በመጀመሪያ BGNLJ (Brothers Gathered Unto Lord Jesus) በኋላም (Bible Truth Ministry) እየተባለ ይጠራ ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ የድርጅቱመሪ በቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርትና ማኅበረሰብ ብርታት የተባረረው ግርማ በቀለ ነው፡፡ሌላው ተጠቃሽ ግለሰብ ሥዩም ያሚ የሚባለው ነው፡፡ ድርጅቱ ከእንግሊዝኛ በሚተረጉማቸው መጻሕፍት የቤተክርስቲያንን መጻሕፍት ክፉኛ ያብጠለጥላል፤ በየክልሉ በከፈታቸው ቅርንጫፍ ማከፋፈያዎች ጽሑፎችን በነጻበማደል፣ ሥልጠናዎችን በመስጠት፣ ታሪክን በማዛባትና በአዋልድ መጻሕፍት ላይ የማይገባ ትችት በመሰንዘርአገልጋዮችን ያደናግራል፡፡

የድርጅቱ ዓላማ የቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ መቀየር እንደ ኾነ ከኅትመቶቹ መረዳት ይቻላል፡፡ ለዚህምከፕሮቴስንታን ኮሌጅ የተመረቁ መናፍቃንን ቀጥሮ በደብረ ዘይት፣ ጅማ፣ በደሌ፣ ጎባ፣ ወናጎ፣ ባሕር ዳር፣ ሐዋሳ፣. . .ወዘተ በከፈታቸው ቅርንጫፎች የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶን ሥራ እንዲያቀላጥፉ ያደርጋል - በራሪ ጽሑፍማሰራጨት፣ የርቀት ትምህርት መስጠት፣ ወደ ገዳማት እና አድባራት ተመሳስሎ በመግባት፣ በከፍተኛ ትምህርትተቋማት ግቢ ጉባኤያት ተመሳስሎ በመስረግ በጎችን ለመንጠቅ እየተሯሯጠ ይገኛል፡፡

ድርጅቱ የሚያስፋፋቸው ኑፋቄዎች ‹‹ክርስቶስ ወደ ምድር መጥቶ ለአንድ ሺሕ ዓመት ይነግሣል›› ይላል፤‹‹ወልድም መንፈስ ቅዱስም አማላጆች ናቸው›› ይላል፤ አጽዋማትን ይቃወማሉ፤ ሥልጣነ ክህነትን አይቀበሉም፤የቅዱሳንን አማላጅነት አይቀበሉም፡፡

‹‹የኢትዮጵያ መንፈሳዊ ተሐድሶ ኅብረት›› በሚል ስያሜ የሚጠራውና ነሐሴ 10 ቀን 1996 . በፍትሕሚኒስቴር ተመዝግቦ በአዲስ አበባ ገርጂ /ቤት ከፍቶ ኑፋቄ የሚያስፋፋ፤ በደሴ፣ ከላላ፣ ጎንደር፣ ጎጃም እና ደብረብርሃን ቅርንጫፍ /ቤቶች ከፍቶ በሚንቀሳቀሰው ማኅበር ላይ (የቦርድ ሰብሳቢው / ሙሉጌታ ደምሴይባላልየቀረቡት ማስረጃዎች ተጠናክረው ምርመራው እንዲቀጥል ኮሚቴው ሐሳብ አቅርቧል፡፡

በተለይም የዚህ ማኅበር አባል እንደ ኾነ የሚታወቀውና ‹‹በውኑ በማርያም ማመን ይገባሃልን?›› በሚል ርእስየኑፋቄ መጽሐፍ የጻፈው ‹መጋቤ ጥበብ› ሰሎሞን ጥበቡ ፍጹም ውግዘት ከሚገባቸው ግለሰቦች መካከል እንደኾነየኮሚቴው ሪፖርት ያስረዳል፡፡

በሪፖርቱ መሠረት በግለሰብ ደረጃ ከተዘረዘሩት መካከል፡-
1.   ጽጌ ስጦታው - ቅዱስ ሲኖዶስ በነገረ ሃይማኖትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ስሕተት መፈጸሙን አጣርቶ ጥያቄናመልስ ሲያካሂድበት ‹‹ተሳስቻለኹ፤ ልመለስ›› በማለቱ ቅዱስ ሲኖዶስ በቀን 29/11/2003 . በቁጥር4560/136/90 በጻፈው ደብዳቤ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም የሐዲሳት መምህር አባ ገብረ ኢየሱስ ዘንድ ልኮትከጓደኛው ጋራ በፈጸመው ተመሳሳይ ጥፋት ከገዳሙ የተባረረ ነው፡፡

ግለሰቡ ከቀድሞው በባሰ እኵይ ተግባር ተጠምዶ ይገኛል፤ የራሱን ድርጅትና ሓላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርአቋቁሞ ንግዱን በሃይማኖት ስም እያጧጧፈ ‹‹ይቅርታ አድርጉልኝ›› ያላቸውን የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትእያንቋቋሸና እየዘለፈ ይገኛል፡፡ ከብዙ ኑፋቄው መካከል ‹‹ይነጋል›› በተሰኘው መጽሐፉ ‹‹እመቤታችን ጥንተአብሶ አለባት፤ ተኣምረ ማርያምን የጻፉት ፀረ - ወንጌሎች ናቸው፤ በኢየሱስ ክርስቶስ ያመነ ሁሉ ካህን ነው፤ አቡነተክለ ሃይማኖት እግራቸው የተቆረጠው በጦርነት ነው፤ በቅዱሳን ስም መዘከር አግባብ አይደለም፤…›› እያለይወሸክታል፡፡

በሌሎችም ጽሑፎቹ የመነኰሳትን ክብር አቃሏል፤ ‹‹ደርግ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ቴዎፍሎስንበመግደሉ ሲኖዶሱ ተስማምቶበታል›› በማለት ምእመኑ በሲኖዶስ ላይ ያለው እምነት ለመሸርሸር ሞክሯል፡፡‹‹ለታቦት፣ ለመስቀል እና ለሥዕል መስገድ፤ የጾም መብዛት፣ በሕግ በኾነ ጋብቻ በተወሰኑ ቀናት ከሩካቤ ሥጋመከልከል በሕዝቡ ላይ የተጫነ የአማራ ቀንበር ነው፤›› ይላል፡፡

2.   አሸናፊ መኰንን - አንቀጸ ብርሃን በሚል ስያሜ በሚያሳትመው መጽሔት ለአብነት ያህል ‹‹በእኛ ቤተክርስቲያን አምላክነቱን አጉልቶ የሰውነቱን ቅርበት መዘንጋት፣ በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት የሥጋውንቅርበት አግንኖ የመለኮቱን ክብር መርሳት የተለመደ ነው፡፡ መጽሐፉ ግን ያቻችለዋል፤›› የሚሉና የመሰሉበርካታ ክሕደቶችን ጽፏል፡፡
በመመሪያ ሓላፊ ደረጃ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና መዝገብ ቤት ሓላፊ ከኾነችውና ሙሉ ወንጌል› ቤተ እምነትከምታዘወትረው / ዐጸደ ግርማይ ጋራ ጥብቅ ግንኙነት እንዳለው ይነገራል፡፡ በወ/ እጅጋየሁ በየነ አማካይነትበፓትርያሪኩ ልዩ /ቤት መሽጎ በበዓለ ሢመት፣ በዐበይት በዓላት፣ በደቀ መዛሙርት ምረቃ መርሐ ግብሮች ላይበፓትርያሪኩ ስም የሚተላለፉ መልእክቶችን እስከ መጻፍ መድረሱ ይነገርለታል፡፡

3.   ደረጀ ገዙ - በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተለያየ ደረጃ ኑፋቄውን ሲያራምድ ከቆየ በኋላ ሲነቃበት ወደ አዲስአበባ ተዛውሮ በከሣቴ ብርሃን የተሐድሶ ድርጅት ውስጥ በዋና /ቤት ተቀጥሮ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡ በባሕርዳር ከተማ በድብቅ ለካህናትና ዲያቆናት እንዲሁም ደባትራንና መዘምራን በተከራየው ቤትና ‹‹በሰሜን ምዕራብአብያተ ክርስቲያናት ኅብረት /ቤት›› ሥልጠና ሰጥቷል፤ ከኑፋቄዎቹ መካከል ‹‹ጽዮን የሚለው ስምከእመቤታችን ጋራ ዝምድና የለውም፤ የተራራ ስም ነው፤ ለቅዱሳን ይኹን ለመላእክት ስግደት አይገባም፤ለቤተ ክርስቲያን ስግደት ይገባል ማለት ክርስቲያን ለኾነው ሁሉ ይሰገድለት ማለት ነው፤ እንደ ኦሪታውያኖችየዕጣን ጭስ እንድንወዝውዝ አልታዘዝንም፤›› በሚል ግልጽ ድፍረት በዐውደ ምሕረት በድፍረት ተናግሯል፤በመጽሐፍ ጽፏል፡፡ በውስጥ አጋፋሪዎቹ እየተረዳ እርሱም ባለቤቱም መናፍቅ መኾናቸው እየታወቀ 27/09/98. በብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ‹‹ሥርዐተ ተክሊል›› ፈጽሟል፡፡

4.   በዛ ስፍርህ - ከቤተ ክርስቲያናችን ኮሌጅ ተመርቆ በባሕር ዳር ከሣቴ ብርሃን  የኑፋቄ ተልእኮውን ሲወጣከቆየ በኋላ አሁን ወደ ሱዳን መሻገሩ ይነገርለታል፡፡ ደቀ መዝሙር በዛ በሚል ስም ‹‹መቅደስ የገቡ መናፍቃን››በሚል ርእስ ከደረጀ ገዙ ጋራ በጻፈው የክሕደት መጽሐፍ ከላይ የተገለጹትን ኑፋቄዎች ከመናገሩም በላይ‹‹የጥንታዊቷ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮን መሠረት አድርጎ የተዘጋጀ›› በማለት የቤተክርስቲያንን መብት በመጋፋቱ በሕግም ሊጠየቅ ይገባዋል፡፡

5.   ግርማ በቀለ - ከጽጌ ስጦታው ጋራ የቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ ለመለወጥ ሲሯሯጥ ተደርሶበት የተባረረነው፡፡ ከኑፋቄው መካከል ‹‹ቤተ ክርስቲያን ማለት ክርስቲያኖች ተሰብስበው አምልኮ የሚፈጽሙበት ቦታአይደለም፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማይ በእውነተኛዪቱ መቅደስ አገልጋይ ነው፤ አሁንም ይማልዳል፤ እንደሊቀ ካህንነቱ ከዚያ ኾኖ ቤተ ክርስቲያንን ያስተዳድራል፤ ኢየሱስ ሊቀ ካህን ከኾነ እኛ ሁላችን ካህናት ነን፤ እንደወረቀት ይቆጠር የነበረው ሰሌዳ ታቦት ተብሎ አሁን ወደሚገኝበት ደረጃ ተሸጋግሯል፤. . .›› የሚሉትይገኙበታል፡፡

6.   አግዛቸው ተፈራ - በአሰላ ከተማ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ሰንበት /ቤት የነበረ፣ በነፋቄ መርዝከተነደፈ በኋላ በሰንበት /ቤቱ ትጋትና በሰበካ ጉባኤው ጥብቅ ክትትል ተጋልጦ አልመለስ በማለቱ የታገደ ነው፡፡የክሕደት ትምህርቱን ‹‹የተቀበረ መክሊት›› ‹‹የለውጥ ያለህ›› ‹‹ጥላና አካል››. . .በተባሉ መጻሕፍቱያሰራጫል፡፡ ከጥር 2002 . ጀምሮ የመናፍቃኑ ማኅበረ በኵር መጽሔት የኾነው ጮራ መጽሔት ዋና አዘጋጅበመኾን ተቀጥሮ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡

ከኑፋቄው ጥቂቶቹ ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጉባኤ ኒቂያና ቁስጥንጥንያ ከረቀቀውየእምነቷ መሠረት ከኾነው ጸሎተ ሃይማኖት ውጭ ሌሎች ኢመጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮዎች ስላሏትየአስተምህሮ ለውጥ ያስፈልጋታል፤ ክርስቶስ ለተሰቀለበት መስቀል ያልተገባ ክብር ሰጥታለች፤ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብአምልኮተ ዕፀ መስቀልን በቤተ ክርስቲያን እንዳስፋፉ የእርሳቸውን ሥራ ዕውቅና ለመስጠት 2000 . ቤተክርስቲያኗ አዲስ መጽሐፍ ቅዱስ እንዳዘጋጀች ሲተች ይታያል፤ በዓለም ላይ በሐዲስ ኪዳን ዘመን ይልቁንም በቤተክርስቲያን ውስጥ ታቦት እንደሌለ ይታወቃል፤ ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን ብቻ እንጂ ኦሪትንና ወንጌልን በአንድላይ እንድታስኬድ የታዘዘችበት ኹኔታ ፈጽሞ የለም፤. . .›› የሚሉት ይገኙበታል፡፡

7.   መጋቤ ጥበብ› ሰሎሞን ጥበቡ - ‹‹በውኑ በማርያም ማመን ይገባሃልን?›› በሚል የኑፋቄ መጽሐፍየጻፈ ሲኾን ‹‹የኢትዮጵያ መንፈሳዊ ተሐድሶ ኅብረት›› አባል ነው፡፡ በማኅበሩ ላይ የሚደረገው ተጨማሪክትትል እንደተጠበቀ ኾኖ ይህ ግለሰብ ግን ራሱን ችሎ ፍጹም ውግዘት እንዲተላለፍበት ኮሚቴው የውሳኔ ሐሳብአቅርቧል፡፡
በቅዱስ ሲኖዶስ /ቤት በኩል ለሊቃውንት ጉባኤው በቀረበው የሰነድ ማስረጃ .(8) ላይ የተመለከተውበጋሻው ደሳለኝ በሪፖርቱ እንደተመለከተው ሊቃውንት ጉባኤው ለጥያቄና መልስ ተደጋጋሚ ጥሪ በቃልናበጽሑፍ ቢያደርግለትም ጥሪውን አክብሮ ባለመቅረብ አጉራ ዘለልነቱን በድጋሚ አረጋግጧል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ለሠየመው አካል ጥሪ ጆሮ ዳባ ልበስ ያለው በጋሻው ግን በሃይማኖቱ ሕጸጽ ዙሪያ የቀረበውሪፖርት በትናንትናው ዕለት አጀንዳ ኾኖ እንደሚታይ ከውስጥ ተባባሪዎቹ ባገኘው መረጃ ይመስላል ገና በጠዋቱወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ቅጽር ከተፍ ብሏል፡፡ በጋሻው በቅጽሩ በራፍ ላይ ደርሶ የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢከኾኑት መጋቤ ምስጢር ዓምደ ብርሃን ቆሞ እንደተነጋገረ በአቅራቢያው የተከታተሉ ቀናዒ ኦርቶዶክሳውያንለደጀ ሰላም ተናግረዋል፡፡ የበጋሻው ንግግር የልምምጥ ቃና ያለው ‹‹በእንተ እጅጋየሁ›› ዐይነት ተማጥኖ ነበር፡-
በጋሻው ጠየቀ - ‹‹/ እጅጋየሁ ልከውኝ ነው፤ አልነገርዎትም?››
መጋቤ ምስጢር ዓምደ ብርሃን - ‹‹ከሌላ ነገር ጋራ አታገናኘው፤ ንጹሕ ሥራ ነው እየሠራን ያለነው››

ከቀትር በኋላ በቀረበው የኮሚቴው ሪፖርት ግን በጋሻው የተላከበት የወ/ እጅጋየሁ ሞገስና በመጋቤ ምስጢርዓምደ ብርሃን ምላሽ ውስጥ ግልጽ ኾኖ የወጣው የትእዛዝ መልእክት አልነበረም የተሰማው፡፡ የቤተ ክርስቲያንልጅነት ጠባይ የሌለው በጋሻው በተለያዩ ጊዜያት እጅግ ጥንቃቄ በጎደለውና ድፍረት በተሞላበት ኹኔታ ቀኖናቤተ ክርስቲያንን በመጣስ ያስተምር ስለነበር ብዙ ሕዝብ አሳስቷል፡፡ አባቶችን ከመዝለፍ ጀምሮ የቤተክርስቲያንን ክብር በማዋረዱ ቀርቦ ሊጠየቅ ይገባው ነበር፡፡

በተለይም ‹‹ሳንጠነቀቅ መንፈስ እንዳቀበለን/እንዳዘዘን እናስተምራለን›› በሚለው የዘወትር መርሑ ‹‹በአንድወቅት በራስ ቅል ኮረብታ ላይ ክርስቶስና ዲያቢሎስ ቁማር ተጫወቱ፤ የቁማሩ አሸናፊ በሰው ልጆች ልብ ላይዙፋኑን ዘርግቶ ለዘላለም ይነግሣል፤ ይህ ሲኾን ተስማምተው ጫዋታውን ለመጀመር ያላቸውን ሲያስይዙዲያብሎስ ብልጣብልጥ ቢጤ ነበርና በጨበጣ ገባ(የሚያስይዘው ሳይኖረው) ክርስቶስ ግን የዋህ ነበርናየሚያስይዘው ቢያጣ ቅድስት ነፍሱን በአደባባይ አስያዘ፡፡ በመጨረሻ ግን በነፍሱ የተወራረደው ጌታ ጨዋታውንበርግጥ አሸነፈ፤›› እያለ ለተናገረው መልስ እንዲሰጥ ይፈለግ ነበር፡፡ የስብሰባው ምንጮች እንዳሉት ኤሽታኦል/2001 .በተሰኘው መጽሐፉ ገጽ 30 ላይ የሰፈረው ይኸው ቃሉ የሚያስጠይቀው እንደኾነና ተጠርቶአለመቅረቡ ጭምር ከግምት ተወስዶ ውሳኔው በምልአተ ጉባኤው ደረጃ እንዲተላለፍ ሐሳብ ቀርቧል፡፡

በተመሳሳይ ኹኔታ 131 የአዲስ አበባ ሰንበት /ቤቶች አንድነት በአባ ሰረቀ እና ጌታቸው ዶኒ ላይ ባቀረቧቸውማስረጃዎች የግለሰቦቹ የሃይማኖት ሕጸጽ መመርመሩን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

አባ ሰረቀ በሰሜን አሜሪካ ሳሉ ‹‹እመቤታችን ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ከኃልዮ፣ ከነቢብ ከገቢርየለያት፣ የጠበቃት ስትኾን የአዳም በመኾኗ /እንደመኾኗከትውልድ ወደ ትውልድ ይተላለፍ ከነበረው የውርስኃጢአት ግን የተለየች እንዳልነበረች፤ ከዚህ የውርስ ኃጢአትም መንፈስ ቅዱስ አንጽቶና ቀድሶ የእግዚአብሔርቃልን/ወልድንለመቀበል ዝግጁ አደረጋት›› ከሚሉ ወገኖች ጋራ በመተባበር ‹‹እመቤታችን ጥንተ አብሶ አለባት››እንደሚሉ ነበር የሰነድ ማስረጃ የቀረበባቸው፡፡

በመስከረም ወር 1997 . በዋሽንግተን ዲሲ የደብረ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በተነሣው የነገረሃይማኖት ውዝግብ የአጥቢያው ካህን ቀሲስ አስተርኣየ ጽጌ ‹‹እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንበአዳማዊ ዘር በኩል ከሚተላለፈው የውርስ ኀጢአት መንፈስ ቅዱስ አንጽቷታል›› ሲሉ የያዙትንና የቤተክርስቲያን ያልኾነውን እምነት በመቃወም ብፁዕ አቡነ ማቲያስ ይህ መናፍቅነት መኾኑን ገልጸው ምላሽ ሰጥተዋል- ‹‹እመቤታችን ከአዳም የውርስ ኀጢአት የነጻችው ከመወለዷ በፊት ነው፤ ቤተ ክርስቲያናችንየምታምነውና የምታስተምረው፡አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደች እመቤታችን ድንግልማርያም ከአዳም ዘር የተላለፈ ኃጢአት (ጥንተ አብሶያላገኛት፣ መርገመ ሥጋ፣ መርገመ ነፍስየሌለባት፣ ገና ከመወለዷ አስቀድሞ በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር የነበረች፣ በሰው ልማድና ጠባይከሚደርሰው ሥጋዊ ሐሣብና ፈቃድ ሁሉ የተጠበቀች፣ ከተለዩ የተለየች ንጽሕት ቅድስተ ቅዱሳንናት፡፡››

ከጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በኋላ ራሳቸው አባ ሰረቀ ይህንኑ ጉዳይ በታኅሣሥ ወር 2004 . ‹‹እውነትናንጋት›› በሚል ርእስ ባሳተሙት መጽሐፍ መሰል ጥራዝ በቀሲስ አስተርኣየ ጽጌ እና በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቲያስ መካከል የተደረገውን ምልልስ ባስረዱበትክፍል ነገሩን በንጽጽር በማቅረብ ራሳቸውን ከተጠያቂነት ነጻ ለማድረግ ሞክረዋል፡፡

ይህ ልዩነት ወደ ሊቃውንት ጉባኤና ቅዱስ ሲኖዶስ ተልኮ ውሳኔ እንዲያገኝ በሰሜን አሜሪካ ከነበረው ማኅበረካህናት ጋራ በመኾን ኅዳር 16 ቀን 1997 . በጻፉት ደብዳቤ መላካቸውን ለሊቃውንት ጉባኤ ማስረዳታቸውየተነገረው አባ ሰረቀ÷ ‹‹በአባቶቼ ሃይማኖት ነው የማምነው፤ ርእሰ መንበር የኾኑት አባት [አባ ጳውሎስ]እንዲህ ብለው ጽፈዋል፤ እናንተ የምትሉት የእኔም እምነት ነው፤ በተላከው ደብዳቤ ይኹን በመጽሐፌየገለጽሁት ያሉትን ሐሳቦች ነው፤ አስታርቃችኹ ንገሩኝ›› በማለት መግለጻቸው ተመልክቷል፡፡
ትላንት በተሰማው የኮሚቴው ሪፖርትም አባ ሰረቀ የእነ ቀሲስ አስተርኣየን አቋም በመቃወም እመቤታችን ንጽሐጠባይዕ ያላደፈባት መኾኗን እንደሚያምኑ በመመስከራቸው ‹‹ምልአተ ጉባኤው ውሳኔ ይስጥበት›› ማለቱተዘግቧል፡፡ ምልአተ ጉባኤው በጉዳዩ ላይ የሚያሳልፈው ውሳኔ የሚጠበቅ ኾኖ÷ አባ ሰረቀ የሰበሰቧቸውንማስረጃዎች በመጽሐፍ መልክ ከማሳተምና በይፋ አስመርቀው የውይይት ርእሰ ጉዳይ ከማድረግ ይልቅየተጠረጠሩበትን የሃይማኖት ሕጸጽ ለሚመረምረው ኮሚቴ ማቅረብን ለምን አልመረጡምየሚለው ምላሽየሚሻ ጥያቄ ነው፡፡

ሊቀ ካህናት› ጌታቸው ዶኒ ከሦስት የእምነት ተቋማት ጋራ የተጻጻፏቸውንና ለአንዳንዶቹም አባል መኾናቸውንየገለጹባቸው ስማቸውንና ሙሉ ፊርማቸውን የያዙ ደብዳቤዎች የእርሳቸው አለመኾናቸውን በመካድ በፊርማናአሻራ ምርመራ እንዲረጋገጥላቸው ለሊቃውንት ጉባኤው ጥያቄ አቅርበዋል - ‹‹አሻራዬ በአባ ዲና ይታይ››ብለዋል ጌታቸው ዶኒ፡፡
ለአዲስ አበባ ከተማ ባለአደራ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ /ቤት በቁጥር /////8/2000 በቀን14/01/2000 . ‹‹የቅን ልቡና የመንፈሳዊና የፈውስ አገልግሎት የእምነት ተቋም›› ተመዝግበውየተቋሙ መሥራች እና ዋና ሥራ አስኪያጅ በመኾን በአቃቂ ቃሊቲ / ቀበሌ 02/04 በተከራዩት ግቢለኦርቶዶክሳዊ እምነትና ሥርዐት ተቃራኒ የኾነ ነገር ለማራማዳቸው ሲጠየቁም አስገራሚ ምላሽ ሰጥተዋል -‹‹ልጆቼን የማበላው ተቸግሬ ነው፡፡››
‹‹ከጊዜ በኋላ ለቅዱስ ፓትርያሪኩ የይቅርታ ደብዳቤ ጽፌ ሥራ ሰጥተውኛል›› ያሉት ‹ሊቀ ካህናት› ጌታቸውእርሳቸው የጻፉትን የይቅርታ መጠየቂያ ደብዳቤና በምላሹ ፓትርያሪኩ የጻፉላቸውን ደብዳቤዎች በማስረጃነትማቅረባቸው ተገልጧል፡፡

ኮሚቴው በአዲስ አበባ ሰንበት /ቤቶች በኩል 67 ግለሰቦች ከእኒህም ውስጥ በሕይወት ያሉና የሌሉ፣ በአገርውስጥና በውጭ የሚገኙ የሃይማኖት ሕጸጽ እንዳለባቸው የሚጠረጠሩ ግለሰቦች ሥራዎች ማስረጃዎች መቅረቡንበሪፖርቱ ገልጧል፡፡ ሪፖርቱ አያይዞም የአንዳንዶቹ ስም ዝርዝር ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት /ቤት ተልኮበአድራሻ ተፈልገው እንዲጠሩ ተደጋጋሚ ጥያቄ የቀረበ ቢኾንም ሀገረ ስብከቱ አግኝቶ ሊያቀርባቸው እንዳልቻለአስታውቋል፡፡ በመኾኑም ወደፊት ማስረጃው እየተጠናከረ ምርምራውን ለማጠናቀቅ ጥረት እንደሚደረግ ሪፖርቱአመልክቷል፡፡

ምልአተ ጉባኤው ከቀትር በፊት በነበረው የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን አዲስ አመራርና አወቃቀርማሻሻያ ላይ ተነጋግሯል፡፡ የአመራርና አወቃቀር ለውጡ ኮሚሽኑ በዐዋጅ ቁጥር 621/2001 እና ደንብ ቁጥር168/2001 በሚደነግገው መሠረት በዳግም ምዝገባ በሰርቲፊኬት ቁጥር 1560 ‹‹ኢትዮጵያ ነዋሪዎች በጎአድራጎት ድርጅት›› ኾኖ መመዝገቡን ተከትሎ ከሃይማኖት አገልግሎት ጋራ ሳይቀላቀል ራሱን የቻለ የልማትድርጅት ኾኖ ለመሥራት የሚያስችለው ነው፡፡

በዐዋጁ ላይ የማኅበራትና በጎ አድራጎት ኤጀንሲ ዳይሬክተር ጄነራል በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ ተገኝተውማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ኮሚሽኑ በዐዋጁና ደንቡ መሠረት እንደ ልማትና በጎ አድራጎት ተቋም ጠቅላላ ጉባኤናቦርድ ያዋቅራል፤ የጠቅላላ ጉባኤው አባላት ብዛት 20 ሲኾን የቦርዱ አባላት ደግሞ ዘጠኝ ናቸው፡፡ ከኻያውየጠቅላላ ጉባኤ አባላት ዐሥሩ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መካከል ሲኾን የተቀሩት ዐሥሩ ደግሞ ከምእመናንየሚመረጡ ባለሞያዎች ይኾናሉ፡፡

ለማኅበራትና በጎ አድራጎት ኤጀንሲ ማናቸውንም የሥራ እንቅስቃሴና የኦዲት ሪፖርቶች፣ የንብረት ይዞታ፣የዓመት ዕቅድና ሌሎችም ተዛማጅ ሰነዶች እያቀረበ ያስገመግማል፡፡ ጠቅላላ ጉባኤውና ቦርዱ ለኮሚሽኑአመራር በመስጠትና ቁጥጥር በማድረግ ሙሉ ሥልጣን የሚኖራቸው በመኾኑ እንደ ችግርየሚጠቀሰውን የፓትርያሪኩን ጣልቃ ገብነት ለመከላከል እንደሚያስችል ተነግሯል፡፡

ኮሚሽኑ 90 በመቶና ከዚያም በላይ ገቢውን ከውጭ የሚያገኝ ሲኾን በአዲሱ አሠራር መሠረት 70 ከመቶወጪውን ለፕሮጀክት/ዓላማ ማስፈጸሚያብቻ፣ 30 ከመቶ ገቢውን ደግሞ ለአስተዳደር ወጪ ማድረግይጠበቅበታል፡፡ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ተጠሪ የኾነው ጠቕላላ ጉባኤው ከተሰበሰበ በኋላ የቦርዱ አባላቱንየሚመርጥ ሲኾን ‹‹የኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ›› የሚለው መዋቅር ቀርቶ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር እንደሚኾኑ ተጠቁሟል፤የሊቀ ጳጳሱ ምክትል በበጎ አድራጎት ድርጅት ባሕርይን በመገንዘብና በልማት አመራር ብቁ ልምድ ያካበተ ባለሞያእንደሚኾን ተመልክቷል - ‹‹ስንት ምሁራን ያሏት ቤተ ክርስቲያን እንዴት የጡረታ መውጫ ትኾናለች?››ብለዋል እርጅና የተጫጫናቸውን የወቅቱን ኮሚሽነር ድክመት የተቹት ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ፡፡

የአሁኑ ምልአተ ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ የጠቅላላ ጉባኤው አባላት የሚኾኑ 10 ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን የመረጠሲኾን እነርሱም፤ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል፣ ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፣ ብፁዕአቡነ አብርሃም፣ ብፁዕ አቡነ ዳንኤል፣ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ እና አሁን የኮሚሽኑ ሊቀ ጳጳስኾነው የሚመሩት ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ናቸው፡፡

ፓትርያሪክ አባ ጳውሎስ በየጊዜው ከለጋሾች የሚሰጠውን የኮሚሽኑን የፕሮጀክት በጀት በየምክንያቱ በመጠየቅማባከናቸውን በመከላከላቸው የኮሚሽኑ ሊቀ ጳጳስ ፊርማ ተሰርዞ የኮሚሽኑ የቁጠባና ተንቀሳቃሽ ሒሳብበኮሚሽነሩና በፋይናንስ መምሪያ ሓላፊው ጣምራ እንዲንቀሳቀስ ለአምስት ባንኮች የተለያዩ ቅርንጫፎችያስተላለፏቸው ትእዛዞችም በዚህ የአመራርና አወቃቀር ለውጥ መሠረት ተቀባይነት እንደማይኖረው ተገልጧል፡፡

በሌላ በኩል ምልአተ ጉባኤው በቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ዙሪያ በመወያየት እስከ አሁንየቤተ ክርስቲያን ይዞታ ኾነው ሳለ ያልተመለሱትን 283 ቤቶች በማስመለስ ረገድ አስተዳደሩ የሚያደርገውንጥረት በአግባቡ አጠናክሮ እንዲቀጥል መመሪያ ሰጥቷል፡፡ እስከ አሁን ድርጅቱ 16 ሕንፃዎችን፣ 271 ቤቶችንና10 መጋዘኖችን ያስተዳድራል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎቻችንን ይከታተሉ፡፡

ቸር ወሬ ያሰማን፤
አሜን፡፡

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

1 comment:

  1. gebe kalefe wesha chohe newe!!!!dero menefeqewe kebetekirstiyan yewetu lòaye meweyayete asefelagi ayemeselegne

    asefelagiwe negere betekihenete tesegesegewe yaluten menafeqane masewegede laye newe!!!



    egiziabehere betekirstiyanene yetebeqelen

    ReplyDelete