የምንሰውማ ጉድ ምንድነው?
| አዲስ የተገዛው የ8 ሚሊዮን የቅድስ ተ/ኃይማኖት ቤ/ክ አሜሪካ |
በቀጣይነት ያሉትን እየተከታተልን እንዘግባለን፤ በዚህ አጥቢያ ያሉትንም ምዕመናን መረጃውን ብታደርሱን በሚዲያችን ለማስተናገድ እንደምንችል ከወዲሁ ለማስታወስ እንድወዳለን፤
📝የሚሰማው ምንድን ነው ?
👉በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው በቅርቡ ስምንት ሚሊዮን ዶላር (8Million $) ወጥቶበት የተገዛው የምሥራቀ ጸሐይ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ቨርጅኒያ በመሀከላቸው ምንድን ነው የተፈጠረው ?
👉 የሚሰማው ደስ አይልም ፦ ከእናንተው ይምጣ ብለን እንጂ ፣ በቪዲዮም ሆነ በጽሑህፍ እና በድምፅ የቀረቡትን መረጃዎች አይተናል ፣ ቀደም ሲልም ቤተክርስቲያኑ ሳይገዛ በፊት በአውደ ምሕረቱ ጭምር የነበረውን ምልልሶች አይተናል፣ የአሁንም ለሚዲያችንም ደርሶናል ።
👉ተፈጠረ የተባለውንም ችግር ዋጋ ለከፈለው ለሕዝበ ክርስቲያኑ ( ለምዕመኑ ) ብሎም ለወጣቱ ትውልድ ስብራት እንዳይገጥመው በማሰብ ይህ ፈተና መሆኑንን በማመን በርን ዘግቶ መክሮ ለመፍትሔ አንድ ልብ መሆኑ ግን ሚዛን የደፋ ምርጫ እንደሆነ ለመጦቆም እንወዳለን ።
👉መረጃው እውነት ቢሆንም ከባለጉዳዮቹ ስላልመጣ ዝርዝሩን ለማውጣት አልፈለግንም ፣ በየትኛውም በኩል ላሉ ባለ ድርሻ አካላት እውነት አለን ሕዝብ ማወቅ አለበት ካሉ ግን ሚዲያችን በሩ ክፍት ነው ።
No comments:
Post a Comment