Friday, October 31, 2025

በአርሲ የእልቂት ድግሱ እንደቀጠለ ነው፤ ለማን አቤት ይባል???

አርሲ በኦርቶክስት ደም ታጥባለች ፤ 

በምሥራቅ  አርሲ  ሽርካ  ወረዳ ሄላ  ዘባባ ቀበሌ  ከሚኖሩ ኦርቶዶክሳዊያን ሦስቱ መገደላቸው እና አራቱ መታገታቸው ተሰማ፡፡

በወረዳው ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ115 በላይ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውና ከ16 በላይ ዐብያተ ክርስቲያናት መዘጋታቸው ታውቋል።

ጥቅምት ፲፱/፳፻፲፰ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ 

ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን በደረሰው መረጃ ጥቅምት  17 ቀን 2018  ዓ.ም ከለሊቱ 4:00 ሰዓት አካባቢ በምሥራቅ አርሲ ሽርካ ወረዳ ሄላ ዘባባ ቀበሌ አርሴማ አጥቢያ የሚኖሩ ምእመናን በታጠቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ሦስቱ መገደላቸው እና አራቱ ደግሞ መታገታቸው ተገልጿል።

ከተገደሉት ምእመናን ውስጥ የአንዱ ሟች አባትና ወንድም መታገታቸው በመረጃው የተገለጸ ሲሆን ታፍነው የተወሰዱት ምእመናን ስለሚገኙበት  ሁኔታ አይታወቅም ተብሏል፡፡

በመረጃው እንደተነገረው የሞቱት ሦስቱ ኦርቶዶክሳውያን በትላንትናው ዕለት ጥቅምት 18  ቀን  2018  ዓ.ም  ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል፡፡

ላለፉት ሁለት ዓመታት ማለትም ከ2016 ዓ.ም መስከረም 02 ጀምሮ  እስከ  2017 ዓ.ም  ድረስ ያለማቋረጥ በወረዳው ከ115 በላይ ምእመናን የተገደሉ  ሲሆን  27  ኦርቶዶክሳዉያን  ደግሞ አሁንም  ድረስ  ታግተው  ያሉበት  እንደማይታወቅ  ነዋሪዎቹ  ለጣቢያችን  ገልጸዋል።

በግድያ  ያላበቃው  መከራና  ስቃይ  በሽርካ  ወረዳ  ብቻ  በዘጠኝ  ቀበሌዎች  በሺዎች የሚቆጠሩ  ኦርቶዶክሳዉያን  መፈናቀላቸውንም በመረጃው ተጠቅሷል፡፡

Thursday, October 30, 2025

አትነሳም ወይ፤ ኦርቶዶክሳዊ አይደልህም ወይ?

የመጣብንን የአላውያን ጦር በመስቀሉ እንሰብራለን፤
"አትነሳም ወይ? " 

አንተ የተዋሕዶ ልጅ ሆይ
ማንቀላፋቱ አይበቃም ሆይ!
መዘናጋቱስ አይበቃም  ወይ
አይገድህም ወይ!
አትነሳም ወይ
እያለቀ ያለው ወገንህ አይደለም ወይ!

ወገን ሲታረድ እንደ በግ ጠቦት
ደሙ ሲፈስ እንደ ውኃ ጅረት
አየነው አየነው እረፉ ባይ ጠፋ
ሞት ታውጆብን ከምድር እንድንጠፋ

       አየገባህም ወይ
        አትነሳም ወይ
       በግፍ የሚገደለው ሕዝብህ አይደለም ወይ

       መንግሥት አለ ብለህ እንዳትጃጃል
አባት አለ ብለህ እንዳትጃጃል
እግዚአብሔርን ይዘህ ተነስ ለ ትግል
ወደ ፊት ሩጥ እንጂ ወደ ኋላ አትበል

           አይበቃም ወይ
            አያሳዝንም ወይ
            አትነሳም ወይ
      በግፍ የሚታረደው
       ሕዝብህ አይደለም ወይ
ወገን በሃይማኖቱ በግፍ ሲገደል
ሬሳው እንኳ  ሳይቀር በእሳት ሲቃጠል
አያሳዝንም ወይ እየሆነ ያለው
ተነሳ ወጣት ሆይ  መፍትሔው 
መነሳት ነው

ሌላው አጀንዳ በራሱ ድምፃችንን የሚያጎላ ሳይሆን ድምፅ የሚቀንስ ነው!

የሚያሳዝነኝ ዛሬ መሞታችን ብቻ ሳይሆን ሞታችን እንዳይቀጥል አንድ አይነት ድምፅ ማውጣት አለመቻላችን ነው ሌሎች እንኳን ሲሞቱ ይቅርና ሲታመሙ እንኳን የሚያወጡት ድምፅ አንድ አይነት ነው እኛ በሞታችን ሳይቀር ዥንጉርጉር ነን ድምፃችንን አንድ አድርገን መኖር ይፈቀድልን ለምን እንገደላለን ከሚል ጩኸት ይልቅ ሞታችንን እንከፋፈልበታለን እነ እገሌ አብረውን አልቅሰዋል እነ እገሌ በደንብ አልጮሁም የእነ እገሌ አለመጮህ ወዘተ እያልን ድምፅ መቀነሳችን ልዩነት መፍጠራችን ወደ ፊት እንኳን ለገዳዮቻችን አንድ ሆነን እንደማንቆም እየነገርናቸው ነው😭😭 ኦርቶዶክስ ናቸው ተብለን እየተገደልን ሞታችን ውስጥ ብዙ ነገር መሥራታችን ሞታችንን በልዩ ልዩ ምንዛሬ ማየታችን እጅግ ያሳዝናል መግደል ባይደክማችሁ እንኳን መሞት ደክሞናል ይበቃል እንበል የተከፋፈለ ሐሳብና የግል አመለካከት ከመሰንዘር ወጥተን ሞታችንን እናስቁም ገዳዮቻችንን እናውግዝ ዝምተኞችን እንቀስቅስ ተናጋሪዎች ንግግራቸው ትክክለኛ ሐሳብ ላይ ያነጣጠረ እንዲሆን እንምከር ሞታችንን ለልዩ ልዩ ፍጆታ የሚጎትቱትን በወንድምና እህት በልጅ በእናትና አባት ሞት ገብያ አትክፈቱ እንበል ያ ካልሆነ በስተቀር ለጊዜው ተነቃቅፈን ተወጋግዘንና ተነቋቁረን ተመልሰን ደግሞ ዝም እንላለን ሞቱም መቀጠሉ አይቀርምና አንድ ሆነን እንቁም ሞታችን ውስጥ በመከራችን የምድጃ እሳት ላይ የግል ነገራችንን ለማብሰል የግል ድስት አንጣድ!😭

በምሥራቅ አርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በሚፈጸመው መንግሥት መር ኢስላማዊ ጅሃድ

ብፁዕ አቡነ ያሬድ የምሥራቅ አርሲ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ

በምሥራቅ አርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ  በሚፈጸመው  መንግሥት መር ኢስላማዊ ጅሃድ የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ክፍል ሠራተኞች እልቂቱ ወደ ተፈጸመበት ወረዳ ደውለው ከአንድ ኦርቶዶክሳዊ መረጃ ይቀበላሉ።መረጃ ሰጪው ኦርቶዶክሳውያን ያሉበት አሳሳቢ መሆኑንና የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አባ ያሬድም ለ ጉዳዩ ትኩረት አለመስጠታቸውን ይናገራሉ።ማኅበሩም ድምፁን በሚዲያው ያወጠዋል።ይኽን የሰሙት አቡን ያሬድ ቪድዮው ከሚዲያው  እንዲወርድ በማስፈራሪያ ጭምር አዘዙ። በ ሞቱ ኦርቶዶክሳውያን ሥርዐተ ቀብር ላይ የሚገኙ የሀገረ ሰብከቱ ሠራተኞች ላይም ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደርግም ቀጭን ትእዛዝ ወጥቷል።ይኽ ብቻ አይደለም ከዚህን በፊት "በሀገረ ስብከትዎ ስለሚሞቱት ኦርቶዶክሳውያን ለምን ዝምታን መረጡ "ሲባሉ "ኦርቶዶክሳውያን መሞታቸውን እርግጠኛ አይደለሁም" እስከ ማለት የደፈሩ ሰው ናቸው።እንግዲህ ቤተ ክርስቲያን በእንደነዚህ ዓይነት ሰዎች እጅ ላይ ነው የወደቀችው።#EOTC  የገዳያችንን የብልጽግና ገጽታ የሚገነባ ስለ ኮሪደር ልማት ካልሆነ በቀር ሙሉ በሙሉ ስለ ኦርቶዶክሳውያን እልቂት አይዘግብም።ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የአዳነች አቤቤ የቅርብ ሰው የሆኑት አባ ሄኖክsilent mood ላይ ቢያስገቡትም አልፎ አልፎም ቢሆን መከራችንን ይዘግባል።#Mktv  ገዳዮቻችንን  በስም እንዳይጠሩአቸው  "ያልታወቁ ኀይሎች" እያሉ እንዲዘግቡ  የሚያደርጉት የ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ  እሾኾች ናቸው።

Tuesday, October 28, 2025

ሁለተኛው አሳዛኝ የእልቂት ዜና





በአርሲ ሀገረ ስብከት በኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ። 

ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ] 

በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን መገዳላቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያሳያል። 

በደረሰን መረጃ መሠረት በቀበሌው የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን ከለሊቱ 6:00 ሰዓት አካባቢ በዕለተ ረቡዕ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ለ14 አጥቢያ  ከተኙበት ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሲሆን ስድስቱ ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፈት ቀድመው ታፍነው ተወስደው ነበር ተብሏል። 

የተገደሉት ምእመናን የዕድሜ ክልላቸው ከ2 ዓመት ጀምሮ እስከ 76 ዓመት አዛውንት እንደሚገኙበት መረጃው ይገልጻል። 

በተጨማሪም ሁለት ሰዎች በጥቃቱ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ለተሻለ ሕክምና ወደ አቦምሳ  ከተማ  ሪፈር  መሄዳቸውን በመረጃው ተያይዞ ተነግሯል፡፡ 

ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በቀበሌው ውስጥ የሚኖሩ 8 ኦርቶዶክሳውያን ሌሊት ላይ ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን በደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል።  

የተነሳው አወዛጋቢው ነገር ምንድነው? መፍትሔውስ ምን ሊሆን ይችላል ከኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ

የምንሰውማ ጉድ ምንድነው? 

አዲስ የተገዛው የ8 ሚሊዮን የቅድስ ተ/ኃይማኖት ቤ/ክ አሜሪካ
በቨርጂኒያ ቅዱስ ተክለኃይማኖት ቤተክርስቲያን አጥቢያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከበድ ያለ ጭቅጭቅ እና ንትርክ የሚመስል ነገር ተነስቷል ፤ ከብዙ የብሎጎች እና የቴሌግራም ግሩፖች እንደተረዳነው፤ ይሄ ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረት ከአሥራ ሁለት ወይም ሦስት አመት በላይ በአገልግሎት እንደቆየ ይነገራል ፤ ነገር ግን ቦታው ከተገዛ ቅርብ ጊዜ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ ጣልቃ ገብነት በተለይ ከባሕርዳር ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ አብርሃም በቀጥታ ጣልቃ በመግባት በቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ እና በቤተክርስቲያኑ ምዕመናን ጋር የተነሳውን አለመግባባት ለማስማማት ሳይሆን ያልተፈጠረውን ታሪኩን በማጣመም ሌላ እንደሆነ አድርገው በማቅረብ በምዕመናኑ እና በቤተክስቲያኑ ምዕመናን መካከል ከፍተኛ አምባጓሮ አይነት መነሳቱን እና ፖሊስ ተጠርቶ እንደነበር የታሰሩ ምዕመናን እንዳሉ ግን የድረሰን መረጃ ባይኖርም፤ ፖሊሶች ግን በቦታው ላይ መጥተው ወደ ቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ገብተው እንደነበር መረጃዎች ደርሰውናል፤ በኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ ለመረዳት እንደቻልነው፤ የሚከተለውን መረጃ ለዚህ ሚዲያ ቤተሰቦች ለማድረስ ፤ ነው፤ 
በቀጣይነት ያሉትን እየተከታተልን እንዘግባለን፤ በዚህ አጥቢያ ያሉትንም ምዕመናን መረጃውን ብታደርሱን በሚዲያችን ለማስተናገድ እንደምንችል ከወዲሁ ለማስታወስ እንድወዳለን፤ 

📝የሚሰማው ምንድን ነው ? 

👉በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው  በቅርቡ ስምንት ሚሊዮን ዶላር (8Million $) ወጥቶበት  የተገዛው የምሥራቀ ጸሐይ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን  ቨርጅኒያ በመሀከላቸው ምንድን ነው የተፈጠረው ?

"ደብር ወገዳም"

ደብር ወገዳም 

 መልካም ቃላት የሚበዙት ክፉት ሲበዛ ነው። ሰው መልካም ሥራ ሲርቀው ክፋቱን ሊደብቅ ሲል መልካም ስም ማዕረግ ይደረድራል። መልካም ቃላት ጋጋታ ይጠቀማል። የዘንድሮን የመንፈስ እርቃንነት መቋቋም ያልቻለ ስው ግማሹ በስም ግማሹ ባሸበረቀ ካባና ቀሚስ እንደ ሞዴል በሚቀያየር አልባሳት ያጌጣል። 

ቀደም ባለው ጊዜ የቆየው ባሕል ሊቃውንት ብቻ የሚጠሩበት ሥም አለ። እንደየ ትምህርታቸው እንደ ደብሩ ትልቅነት የአለቃ ስም ይሰጣል። ዛሬ ግን ስም ያልወሰደ የለም። የማይንቆለጳጰስ የለም። 
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕርዳር እና የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስበከት ሊቀ ጳጳስ

ሰላም በሌለበት ደብር የመልአከ ሰላም አበዛዙ፣ የተማረው የተመገበው ሳይኖር የመጋቤ ሐዶስና ብሉይ አበዛዙ ግርም ይላል። 

መልአከ ከዋክብት፣ መልአከ ጨረቃ፣ መምህረ መምህራን፣ ርዕሰ ርዑሳን፣ ርዕሰ ባሕታውያን፣ ቆሞስ ሞቆሳት …..ሊቀ ሐዋርያት፣ መጋቤ ሰማእታት… ምኑ ቅጡ። አምፓል ለቀጠለ ኹሉ መልአከ ብርሃን። 

አቡነ አብርሃም ደግሞ ሰሞኑን አንዲት ስም አስተዋውቀዋል። ደብር ወገዳም የምትል። የዶላር ስም ናት መሰለኝ። መቼስ ለብር ቤተ ክርስቲያን እንዲኽ ያለ ስም አይወጣም።