Saturday, February 23, 2013

ሰበር ዜና – የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ያለስምምነት ተቋጨ

  • ‹‹የሚመረጠውን እያወቅን እኛ መናጆ ነን እንዴ!!›› /አራቱ ዕጩ ፓትርያሪኮች/
  • ስብሰባው ያለስምምነት በተቋጨበት ኹኔታ የኮሚቴው ሕዝብ ግንኙነት ቅ/ሲኖዶሱ የዕጩ ፓትርያሪኮቹን ዝርዝር እንዳጸደቀ አድርገው መግለጫ ሰጥተዋል
አርእስተ ጉዳይ፡-
  • አስመራጭ ኮሚቴው ያቀረባቸው አራት ሊቃነ ጳጳሳት ራሳቸውን ከዕጩነት አገለሉ
  • አስመራጭ ኮሚቴው ለምልአተ ጉባኤው በርካታ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ተስኖት ውሏል
  • ኮሚቴው በአምስቱ ዕጩዎች ላይ የተስማማበትን የውሳኔ ቃለ ጉባኤ ማቅረብ አልቻለም
  • አብዛኞቹ ብፁዓን አባቶች በየሀ/ስብከታቸው የደኅንነት ወከባ እንደተፈጸመ ሪፖርት አድርገዋል
  • መንግሥት ጣልቃ ገብቶ ከኾነ እጁን ከቤተ ክርስቲያን ላይ እንዲያነሣ በአጽንዖት ተጠይቋል
  • ብፁዕ አቡነ ማትያስን የተመለከቱ መረጃዎችን ለማድበስበስ ተሞክሯል
  • በኮሚቴው ዋና ጸሐፊ እና በሕዝብ ግንኙነቱ መካከል የከረረ ልዩነት ተፈጥሯል
  • ‹‹የኮሚቴው አካሄድ ሕጉን ሥርዐቱን ካልጠበቀ የማስተካከል የማረም የመጨረሻ ሓላፊነቱ የምርጫው ባለቤት የኾነው ቅ/ሲኖዶሱ ነው፤ አስፈላጊውን ውሳኔ መስጠት ይችላል፤ እኛ ያልነው ይኾናል፤ ሌላ ነገር አንነጋገር›› /የኮሚቴው ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ/
  • ‹‹የሚመረጠውን እያወቅን እኛ መናጆ ነን እንዴ!!›› /አራቱ ዕጩ ፓትርያሪኮች/
  •  ‹‹የሚሾማቸው አካል በቀጥታ በደብዳቤ ይሹማቸው [አቡነ ማትያስን] እንጂ በዚህ ዐይነቱ አካሄድ ላይ ፊርማችንን አስቀምጠን አንመርጥም፡፡›› /ብዙኀኑ የምልአተ ጉባኤው አባላት/
ዜናው በዝርዝር አቀራረብ ይቀጥላል
 http://haratewahido.wordpress.com/

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

No comments:

Post a Comment