Monday, January 5, 2026

ነብዩ ዘካርያስ

ዘካርያስ የሚለው ስም “ዛካር”ማስታወስ፣ መዘከር እና “ያህ” ከእግዚአብሔር መጠሪያ ስሞች አንዱ የሚሉትን የሁለት ቃላቶች ጥምር 
ዘካርያስ 

ሲሆን ትርጓሜውም “እግዚአብሔር አስታወሰ” ወይም “እግዚአብሔር አሰበ ማለት ነው፡፡ 

ምንአልባት ዘካርያስ የባቢሎን የስደት ኑሮ መጨረሻ አካባቢ 539 ዓ. ዓ. ተወልዶ ወላጆቹ በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር እኛን ሕዝቦቹ ከስደትና ከጉስቁልና ኑሮአችን ነፃ ሊያወጣን አሰበን፤ እኛን ሕዝቦቹ አስታወሰን ከሚለው ጋር በተያያዘ መልኩ የተሰየመ ሊሆን እንደሚችል ይታመናል፡፡ 

ዘካርያስ የዒዶ ልጅ መሆኑን ቢገለጽም በሌላ መልኩ ደግሞ የቤሬክያ ልጅ እንደሆነም ተነግሯል። ዘካ 1፡1 ስለዚህ ወላጅ አባቱ ዒዶ ወይም ቤሬክያ መሆኑን በትክክል ባይታወቅም እንደነ ቅዱስ ጀሮም ያሉ ሊቃውንቶች ግን ቤሬክያ የዘካርያስ ወላጅ አባቱ ዒዶ ግን መንፈሳዊ አባቱ ሊሆን እንደሚችል መላ ይመታሉ፡፡ 

ሌሎች ሊቃውንቶች ደግሞ የመጽሐፉ የመጀመርያው ክፍል ዘካ 1-8 በዒዶ ልጅ ዘካርያስ የተጻፈ ሲሆን ሁለተኛው ክፍል ዘካ8-14 ደግሞ በቤሬክያ ልጅ ዘካርያስ የተጻፈ ነው፤ በኋላ ግን መጽሐፉ ወደ አንድ ጥንቅር ወይም በአንድ መልክ በተዋቀረ ጊዜ ዒዶና ቤሬክያ እንደ አባት በአንድነት ተጠቅሰዋል በማለት መላ ምታቸውን ያቀርባሉ፡፡ 

ነቢዩ ዘካርያስ የኖረውና የነቢይነት ተግባሩን የተወጣው ነቢዩ ሐጌ በኖረበትና የነቢይነት ተግባሩን ባከናወነበት ተመሳሳይ ወቅት ነው፡፡ 

ዘካርያስ ለነቢይነት አገልግሎት እንዴት እንደተጠራ፣ የቤተሰባዊ ኑሮው ምን እንደሚመስል፣ የት እንደኖረና የነቢይነት አገልግሎቱ የት እንደተወጣ ምንም የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ 

ነገር ግን በመጽሐፉ ስለ ኢየሩሳሌምና ቤተ መቅደስዋ እንዲሁም በውስጥዋም ስለሚኖሩ እቃዎች፣ ስለ ሕገ እግዚአብሔር፣ ስለ ይሁዳ ሕዝቦች፣ በቤተ መቅደስ ስለሚያገለግሉት ሊቀ ካህናቶችና የአገልግሎት ልብሶቻቸው ብዙ ትኩረት ሰጥቶ ስለሚናገር የነቢይነት ተግባሩን የተወጣው በኢየሩሳሌም አካባቢ እንደሆነና እሱም ከወገነ ክህነት በኩል ሊሆን እንደሚችል ይታመናል፡፡ 

በእርግጥ ዘካርያስ ኢየሩሳሌምንና አካባቢዋ በደንብ እንደሚያውቀው ከመጽሐፉ በግልጽ መረዳት ይቻላል፡፡ እንደ መጽሐፈ ነህምያ አገላለጽ ደግሞ ዘካርያስ ከይሁዳ ዘርና ከሌዋውያን ወገን እንደነበረ እንረዳለን። ነህ 11


ዘካርያስ እስራኤል ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ በኋላ ከነቢዩ ሐጌ ጋር የነበረ ነቢይ ነው ዕዝ .5፣1-5።  የዘካርያስ መጽሐፍ ተመዝግበውበታል ወይም አርዕስት አሥር ራዕያት የነቢያት መጽሐፍ ተመሳሳይነት ቢኖረውም የዘካርያስ መጽሐፍ በሚስበራዊ ርቀቱ ከሕዝቅኤልና ዳንኤል መጽሐፍ እንዲሁም የሐዲስ ኪዳን የትንቢት መጽሐፍ ከሆነው ከራዕየ ዮሐንስ ይጎራበታል።

ዘካርያስ ያያቸው አስደናቂ ራዕያት የሚከተሉት ናቸው:-

1. መጋላና ሐመር አንበላይ ፈረሶች ም 1፣ 8-17 እነዚህም የኢየሩሳሌምን ምሕረታዊ ተስፋ ሰላምና ፀጥታ ጥጋብና ደስታን ያመለክታሉ።

2. አራት ቀንዶች ም.1፥18-21 እነዚም በቀንድ የተመሰሉ ኢየሩሳሌምን የደመሰሱ ንብረቷን የወረሱ ኅብረተሰቧን ያፈለሱ ኃያላን የአሕዛብ ነገዞታት እንደነበሩ መልአክ ተርጉሞለታል፡፡

3. አራት ጠራቢዎች ም2፣ 1 እነዚህም መላእክት ናቸው በቀንድ የተመሰሉ ኢየሩኄምን ያጠፋ የአሕዛብን ነገሥታት ያጠፋ አራቱ ሊቃነ መላıክት መሆናቸው ተተርጉሟል::

4. የመለኪያ ገመድ የያዘ ሰው ይህ በሰው የተመሰለው መላዕ ነው ይኸውም የኢየሩሳሌምን ልማት የእግዚአብሔርን ረድኤት ያመለክታል። ምዕ..2፣1-5

5. የኢያሱ ወይም የዮሴዕ በሰይጣን መከሰስ። እንደዚሁም ሰይጣኑን በሚያደርገው ተንኮል በመልአከ ምህረት መወቀስ። ምዕ.3፣1-10

6. ባለሰባት መቅረዝ የወርቅ ማብሪያ ከሁለት የወይራ ዛፎች ጋር ሰባቱ መቅረዞች በዘሩባቤል የተሰራውን የቤተመቅደስ ፍጹም ክብር ሲያጠይቅ። ም.4፥1-14

 ሐጌ 2 ፣1-10 በሁለት የወይራ ዛፎች የተመሰሉት ንጉሡ ዘሩባቤልና ሊቀ ካህናቱ የሴዕ ናቸው ሐጌ 6፥1-10

2. በራሪ የመጽሐፍ ጥቅል ርዝመቱ ሃያ ክንድ ወርዱም አስር ክንድ ምዕ5፣1-5 የዚህንም የመጽሐፍ ትርጓሜ መልአኩ እንደነገረው በሌቦችና በሀሰተኞች ላይ እግዚአብሔር መርገም አዘል ከባድ መዓት እንደሚያመጣባቸው በከፋ መቅሰፍት እንደቀጣቸው እንደ እርዝማኔው የመከራቸውን ብዛት ያስቃያቸውን ጽንአት ይገልጻል።

ንዋይ ካሳሁን



የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

No comments:

Post a Comment