Thursday, July 31, 2014

የብፁዕ አቡነ ዳንኤል የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ ተቃውሞ በብፁዕ አቡነ ዘካርያስ ላይ



የሚከተለውን አስተያየየት መሐሪ Mulugeta Maranatha ከተባሉ ግለሰብ ፌስ ቡክ(facebook) ገጽ ያገኘነው ነው።
+++
ሰሞኑን እንዲያውም በቅርቡ የቅድስት አገር ኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል በደብረ ሰላም መድኃኒዓለም ቤ/ክ
ውስጥ ከሚገኙ ከተወሰኑ ምእመናን ጋር እና ከተወገዙት ካሕናት መካከል ከመሪጌታ ቀሲስ ጌታሁን ጋር በአደረጉት የስልክ ንግግር ላይ
የተናገሯቸው ብዙ ስህተቶች እርሳቸውንም ሆነ የቆሙለትን "ሥርዓተ ቤተክርስቲያን" ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው። ሲጀመር ከእነዚህ ሰዎች
ጋር ከመነጋገራቸው በፊት በመዓረግም ሆነ በሥልጣን ከሚቀርቧቸው አባት ከብፁዕ አቡነ ዘካርያስ ጋር መጀመሪያ ቢነጋገሩ መልካም ነበር ያንን ግን የአደረጉ አይመስልም።

+ ሌላው ከስልክ ንግግራቸው እንደተረዳነው የብፁዕ አቡነ ዘካርያስን ርምጃ በተመለከተ ወደፊት ርሳቸው ከብፁዕነታቸው ጋር ተነጋግረው ሊፈቱት እንደሚችሉ
መናገራቸው መልካም ቢሆንም ርምጃው ግን ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን አንፃር ትክክል እንዳይደለ መናገራቸው በዛ በኩል "ስለ እኔ ጠይቃችው" ብሎ ለሌላ
ሰው ሹክ ያሉትን መሪጌታ ጌታሁንን እና ጥቂት ግለሰቦችን ብቻ ለማስደሰት እንደሆነ የሚያስረዳ ነው።

+ ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ሀገረ ስብከታቸው ሌላ ቦታ፤ እረኝነታቸው ለሌላ ሥፍራ ሆኖ ሳለ ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ በሀገረ ስብከታቸው ውስጥ በአሉት አብያተ
ክርስቲያናት የሚወስዱትን ርምጃ መከላከልም ሆነ ትክክል እንዳልሆነ መናገራቸው ተገቢ አልነበርም።

+ በመጨረሻም ብፁዕ አባታችን ጥቂት ሰዎችን ለማስደሰት ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን መሻርና መጣስ የሚያስከትለው ችግርና መዘዝ ብዙ እንደሆነ እያወቁ፤
ስለ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን መከበር ግድ ከሌላቸው ሰዎች ጋር የሚነጋገሯቸውን ንግግሮች መጀመሪያ በሚገባ ቢያጤኗቸውና ከሚመለከታቸው አባቶች ጋር መክረውና ተመካክረው ቢያወሯቸው መልካም ነው ብዬ አስባለሁ።

+ ለመሪጌታ ቀ/ ጌታሁን፦ ውግዘቱ የመጣቦ ከብፁዕ አቡነ ዘካርያስ ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ነበር። መፍትሔ ማግኘትም የሚችሉት ከርሳቸው ዘንድ ሆኖ ሳለ
በሌላ አቅጣጫ ሌላ ሰውን ሄዶ ፍረድልኝ ማለት እርሶን ሚዛን ላይ የሚጥል በእውነትም ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የወሰዱት ርምጃ ትናንትናም ሆነ ዛሬ አማናዊ የነበረና፤
ሆኖ የሚቀጥል መሆኑን አስረግጦ ያለፈ ትዝብት ላይ የጣሎት አጋጣሚ ነበር የስልኩ ውስጥ ንግግሮት።

ነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን። አሁንም ሆነ ወደፊት የጥቂት ፓለቲከኞች ፈቃድ ሳይሆን፤ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ለማስከበር የሚደርስብንን
ፈተና ለመቀበል ዝግጁዎች ነን።





የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

No comments:

Post a Comment