ዘካርያስ የሚለው ስም “ዛካር”ማስታወስ፣ መዘከር እና “ያህ” ከእግዚአብሔር መጠሪያ ስሞች አንዱ የሚሉትን የሁለት ቃላቶች ጥምር
ሲሆን ትርጓሜውም “እግዚአብሔር አስታወሰ” ወይም “እግዚአብሔር አሰበ ማለት ነው፡፡
| ዘካርያስ |
ሲሆን ትርጓሜውም “እግዚአብሔር አስታወሰ” ወይም “እግዚአብሔር አሰበ ማለት ነው፡፡
ምንአልባት ዘካርያስ የባቢሎን የስደት ኑሮ መጨረሻ አካባቢ 539 ዓ. ዓ. ተወልዶ ወላጆቹ በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር እኛን ሕዝቦቹ ከስደትና ከጉስቁልና ኑሮአችን ነፃ ሊያወጣን አሰበን፤ እኛን ሕዝቦቹ አስታወሰን ከሚለው ጋር በተያያዘ መልኩ የተሰየመ ሊሆን እንደሚችል ይታመናል፡፡
ዘካርያስ የዒዶ ልጅ መሆኑን ቢገለጽም በሌላ መልኩ ደግሞ የቤሬክያ ልጅ እንደሆነም ተነግሯል። ዘካ 1፡1 ስለዚህ ወላጅ አባቱ ዒዶ ወይም ቤሬክያ መሆኑን በትክክል ባይታወቅም እንደነ ቅዱስ ጀሮም ያሉ ሊቃውንቶች ግን ቤሬክያ የዘካርያስ ወላጅ አባቱ ዒዶ ግን መንፈሳዊ አባቱ ሊሆን እንደሚችል መላ ይመታሉ፡፡