Tuesday, June 4, 2013

ቤተ ክርስቲያን በአደጋ ላይ! የቅ/ሲኖዶሱ ስብሰባ ሂደት በፅልመታዊው ጎጠኛና ሙሰኛ ቡድን ተጽዕኖ እንዳይጠለፍ ተሰግቷል


  • የጠ/ቤ/ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅነት ምርጫ ሊቃነ ጳጳሳቱን እርስ በርስ አደፋፍጧል
  • ርእሰ መንበሩ ስብሰባውን በአግባቡ ለመምራትና ለመጠቅለል ተስኗቸዋል ተብሏል
  • በሙሰኝነትና ጎጠኝነት በተዘፈቁበት ተግባራቸው ከሚመጣባቸው ተጠያቂነት ራሳቸውን ለማዳን የተባበሩ ጳጳሳትለተቋማዊ ለውጡ ስጋት ደቅነዋል፤ የፓትርያሪኩን የተቋማዊ ለውጥ ይኹንታዎች ተፈታትነዋል፤ አቡነ ሳዊሮስ፣ አቡነ ማርቆስ፣ አቡነ ፋኑኤል፣ አቡነ ዲዮስቆሮስ፣ አቡነ ቄርሎስ እና አቡነ ሕዝቅኤል ይገኙበታል
  • ምክትል ዋ/ሥራ አስኪያጁን ጨምሮ ልመታዊውን ቡድን በብርቱ የተቋቋሙ የተቋማዊ ለውጡ አውራዎችከሓላፊነታቸው እንዲነሡ መወሰኑ ተሰምቷል፤ራሳቸውን በሙሰኛና ጎጠኛ አሠራር ከመጠየቅ ለማዳን የሚረባረቡ ጳጳሳት ቡድናዊነትና ለዋ/ሥራ አስኪያጅነት ምርጫው የተያዘው መደፋፈጥ በሰፈነበት አጋጣሚ በአጀንዳው ዝርዝር ሳይካተት ም/ዋ/ሥራ አስኪያጁን ከሓላፊነት የማንሣት ውሳኔ የተላለፈበት ኹኔ ተኰንኗል
  • ምክትል ዋ/ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ውብሸት ከሓላፊነት የተነሡበት ምክንያት ‹‹ክህነት የላቸውም››  በሚል ቢኾንም ቄስ አይሏቸው መነኵሴ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ቦታውን ለመረከብ አሰፍስፈዋል፤ የአራት መኖርያ ቤቶችና አንድ የንግድ ቤት ባለቤት መኾናቸው የተረጋገጠው ንቡረ እዱ የፀረ – ሙስናውን እንቅስቃሴ በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ለማክሸፍ ተነሣስተዋል
  • ‹‹የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ስብከተ ወንጌል ነው›› በሚል የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ እንዲፈርስ ተወስኗል፤ የጠ/ቤ/ክህነቱ አስተዳደር መምሪያ ዋና ሓላፊ ታግደዋል፤ ውሳኔው ‹‹በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ ድንጋጌ መሠረት ደረጃውን ጠብቆ ያልተወሰደ፣ በፅልመታዊው ቡድን ጎጠኝነት የተገፋና የፀረ – ሙስና ትግሉን የሚያደናቅፍ የቂም በቀል ርምጃ ነ፤›› በሚል ተተችቷል
  • የፀረ – ሙስና እርምት ርምጃዎችን፣ የአስተዳደራዊ መዋቅር እና ፋይናንስ ሥርዐት ለውጦችን አጥንቶ የሚያቀርብበሁለት ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ የባለሞያዎች ኮሚቴ እንዲቋቋም ተወስኗል፤ ሕጉንና ቃለ ዐዋዲውን የማሻሻል ጅምርሥራዎች የማስፈጸምና የስልታዊ ዕቅዱ ዝግጅት በኮሚቴው ይከናወና
  • የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት በአንድ ረዳት ሊቀ ጳጳስና በአራት ሥራ አስኪያጆች እንዲመራ የቀረበው ሐሳብእያከራከረ ነው
የርክበ ካህናት ቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሁለተኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ከተጀመረ አራተኛ ቀኑን አስቆጥሯል፡፡ ግንቦት ፳ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የመክፈቻ ጸሎት ያካሄደው ምልአተ ጉባኤው 18 ያህል አጀንዳዎችን በማጽደቅ ዛሬን ጨምሮ በሥራ ላይ በቆየባቸው አራት ቀናት 13 ያህል አጀንዳዎችን ተመልክቶ ውሳኔ ማስተላለፉ ተዘግቧል፡፡

ምንጭ: ሐራ ዘተዋህዶ
የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

Friday, May 31, 2013

ጀብራሬው ‹‹ኢህአዴግ›› በአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ላይ


የሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ሲነሳ

(አንድ አድርገን ግንቦት 23 2005 ዓ.ም)፡- ‹‹ ከምሽቱ 1፤30 ላይ አንድ ሞቅ ያለው የተበሳጨ ጀብራሬ አቡነ ጴጥሮስ  ሃውልት ላይ ሽንቱን እየሸና  ‹አንተ ድንጋይ ጓደኞችህ  ተመችቷቸው በማርቼዲስ ሲንሸራሸሩ ይህው አንተ ድንጋይ ሆነህ ቀረህ ድንጋይ አሸናብሃለሁ › ሲል በልጅነት ደም ፍላት  ዘልዬ  ከጀብራሬው ጋር ግብ ግብ ገጠምኩኝ ፡፡ ድንጋይ አይደለም፡  ‹ድንጋይ ነው› በሚል በቡጢም  ተቃመስን ፡፡ ከስብሰባው የተበተኑ ሰራተኞች ገላገሉንና እየተበሳጨሁ ቤቴ ገባሁ፡፡ ሌሊቱን አልተኛሁም፡፡ ጴጥሮስ ሕያው ነህ ለማለት ፤ ጴጥሮስ ድንጋይ አይደለም ለማለት ይመስለኛል ‹ጴጥሮስ ያችን ሰዓት› ስጭር አደርኩ ›› ጸጋዬ ገብረ መድህን

ሃሙስ ሚያዚያ 24 ቀን 2004 ዓ.ም  ጠዋት ሳተና የሆኑ ወጣቶችና ጎልማሶች የአቡነ ጴጥሮስን ሃውልት ልክ እንደ አስቸጋሪ ኮርማ በገመድ ጠልፈው አንዳች የሚያህል ክሬነር አስረው ከነበረበት ለመንቀል ደፋ ቀና ይላሉ፡፡
አላፊ  አግዳሚው ወጪ ወራጁ እንደ ዘበት እያየ ያልፋል፡፡ ከፊሉም ሞባይሉን አውጥቶ ፎቶ ሊያነሳ እና ሊቀርጽ ይሞክራል፡፡ ‹‹የሰውየው›› (ሁነኛ ሰው) ሃውልት (የእኛ የእውነተኝነት) ዋቢ ከውስጥ በአቡጀዲ ተጠቅልሎ ፤ ከውጭ በጣውላ ተጠፍንጎ ፤ በብረት ዘንግ ተደግፎ ሊነቀል ትዕዛዝ ይጠብቃል፡፡
 

ቅ/ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያን ስልታዊ ዕቅድ ላይ ይወያያል


  • ምልአተ ጉባኤው 18 የመነጋገሪያ አጀንዳዎችን ለይቶ ውይይቱን ቀጥሏል
ምልአተ ጉባኤው በዋናነት ከሚነጋገርባቸው ጉዳዮች ውስጥ፡-
  • ቤተ ክርስቲያኒቱ በመሪ ዕቅድ መመራት እንዳለባት የታመነበት በመኾኑ መሪ ዕቅዱ ‹‹ተዘጋጅቶ ሲቀርብ›› ተመርምሮ ውሳኔ ይሰጥበታል፡፡
  • የሕገ ቤተ ክርስቲያን እና ቃለ ዐዋዲ ማሻሻያ ረቂቆች በኮሚቴው ቀርበውና ተደምጠው ተጨማሪ ሐሳብ ይሰጥባቸዋል፤
  • በቤተ ክርስቲያኒቱ የአስተዳደርና ሙስና ችግሮች ላይ ‹‹መጠነ ሰፊ›› ውይይት ተደርጎ ውሳኔ  ይተላለፋ በጠቅላይ ቤተ ክህነት መምሪያዎችና ድርጅቶች፣ በሁሉም አህጉረ ስብከት መዋቅሮች ሙስናን የመከላከያውና መቆጣጠርያው አግባብ ከሚያሰፍነው ጥብቅ ሥርዐት አንጻር አጀንዳው አነጋጋሪና አከራካሪ እንደሚኾን ይገመታል፡
  • የቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የጠ/ቤ/ክህነት ዋና ሥ/አስኪያጅ ምርጫ ይካሄዳል በቂ የሰው ኀይልና በበጀት ተደግፎ በሦስት ዴስኮች እንዲደራጅና የራሱ ወርኃዊ መጽሔት እንዲኖረው የተወሰነለት የውጭ ግንኙነት መምሪያ አዲስ ሓላፊና ሊቀ ጳጳስ ይሾምለታል፤ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የቅድሚያ ግምት የተሰጣቸው ቢኾንም ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፣ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስና ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ይጠበቃሉ፤

Thursday, May 30, 2013

የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ተጀመረ፤ ‹‹ሙስና ቤተ ክህነት››ን ያጠፋሉ የተባሉ የእርምት ርምጃዎች ይፋ ተደረጉ

  • ሙሰኛ እንክርዳድ ሁሉ በፀረ – ሙስና ዐቢይ ኮሚቴ ተለይቶ ሕጋዊ ርምጃ ይወሰድበታል!
  • የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር፣ ሕግና ደንብ በውጤት ተኮር ማሻሻያ ይዘጋጃል
  • ከመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ እስከ አጥቢያ የፋይናንስ ሥርዐቱ በዘመናዊ አሠራር ይደራጃል
  • የቤተ ክርስቲያንን ርእይና ተልእኮ የሚያሳይ የስትራተጂያዊ አመራር ሥርዐት ይነደፋል
  • በሁሉም የለውጥ ርምጃዎች የባለሞያ ምእመናን ተሳትፎ ይረጋገጣል
  • በእግዚአብሔር፣ በታሪክና በትውልድ ፊት ለሚመዘነው የለውጥ ርምጃ በጋራ እንነሣ!
  • ‹‹በዚህ ትልቅ የሓላፊነት ወንበር ላይ ስታስቀምጡኝ÷ የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ፣ የምእመናንን የልብ ትርታ እያዳመጥኹ ለእናንተ ለብፁዓን አባቶች ሳቀርብ ይኹንታውንና እገዛውን እየለገሣችኹኝ የጋራ ሓላፊነታችንን እንድንወጣ መኾን አለበት፡፡››/የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ መክፈቻ ንግግር/
ቢሮክራሲው በእጅጉ በተንዛዛውና ከሚያስፈልገው በላይ የሠራተኛ ቁጥር በተሸከመው÷ ለመንፈሳዊነት፣ ሞያና ልምድ ቦታ በማይሰጠው÷ የሰው ኀይል አመዳደቡም ከመሠረታዊ ተልእኮው ጋራ ባልተቀናጀው፣ ከዚህም የተነሣ ሙስናና ወገንተኝነት በሰፈነበት የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር ላይ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሊወሰድ የሚገባውን የእርምት ርምጃ የሚያመላክቱ ሦስት የይኹንታ ሐሳቦችበዛሬው ዕለት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ ይፋ ተደርገዋል፡፡
Abune Matyas Looking Forward
ወደፊት፤ በእግዚአብሔር፣ በታሪክና በትውልድ ፊት ለሚመዘነው የለውጥ ርምጃ!
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ ዛሬ ጥዋት የተጀመረው የርክበ ካህናት ቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ ትኩረት ሊሰጥባቸው ይገባል ባሏቸው መሠረታዊ የለውጥ ርምጃ ይኹንታቸው እንደገለጹት÷ በቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደር የሚታየው የሥነ ምግባር ብልሹ አሠራር ከቤተ ክርስቲያን ክብርና ቅድስና ጋራ የማይጣጣም ነው፤ በምእመናን ላይ ባሳደረው ከፍተኛ ቅሬታ ምእመናኑ በቤተ ክርስቲያን አመራር ላይ ያላቸውን እምነት እያሳጣ ነው፤ አሳፋሪውና አሳዛኙ ብልሹ አሠራር ሥር ከመስደዱ የተነሣ ሳይታረም ቢቀጥል ቤተ ክርስቲያኒቱን ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሚጥል በግልጽ እየታየ ነው፡፡
ብልሹ አሠራሩን ለማረምና ለማስወገድ፣ አስተዳደሩን በአዲስ መልክ ለማዋቀርና የፋይናንስ አያያዝና አጠቃቀሙን ግልጽ በኾነና ተጠያቂነት ባለው መልኩ ለማደራጀት የሚወሰደው የእርምት ርምጃ÷ የቤተ ክርስቲያንን ስምና ክብር በማስጠበቅ ቤተ ክርስቲያንን የሚታደግ፣ ካህናትና ምእመናን የተባበሩበትና ተሳትፎቸው የተረጋገጠበት፣ አመራሩንም ከታሪክ ፍርድና ወቀሳ የሚያድን ሊኾን ይገባል፡፡
የፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ የመሠረታዊ ለውጥ ርምጃ ይኹንታዎች፡-

Friday, May 24, 2013

ኦርቶዶክሳዊ መምህር


ከታምራት ፍሰሐ
"በሃይማኖት ብርኖሩ፥ እራሳችሁን መርምሩ" ፪ኛ ቆሮ. ፲፫ ፥ ፭

ይድረስ ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ አዘጋጅተው በልዩ ልዩ መንገድ ለህዝብ ለሚያደርሱ ኦርቶዶክሳውያን መምህራን

         ብዙወች መምህራን ተብለው ይጠሩ ዘንድ ይሾማሉ፡ አንዳንዶቹ ስለመልካም ግብር አንዳንዶቹም ስለዋዛ ፈዛዛ ብዙወች መምህራን ተብለው እንዲያስተምሩ ወደ ምእመናን ይላካሉ ፡አንዳንዶቹ ከመንፈስ ቅዱስ አንዳንዶቹ ከዲያቢሎስ አንዳንዶቹ መምህራን ከማስተማራቸው አስቀድመው ለራሳቸው ጥበብን ይማሯታል፡ ይተረጉሟታል ይኖሯታል አንዳንዶች ግን ያልገባቸውን ጥበብ ለሌሎች ሊያስረዱ ይደክማሉ፡፡

በምዕራብ አ/አ ሀ/ስብከት ‹ያልጠለቀችው› የሙስናና የጎጠኝነት ጀንበር ‹እየቀላች› ነው


  • በሀ/ስብከቱ የአቡነ ሕዝቅኤል አስተዳደር ሙስናና ጎጠኝነት ባስነሣው ቀውስ ተዘፍቋል
  • የሊቀ ጳጳሱ ዘመዶች ከደብር እልቅና እስከ ዕቅብና በከፍተኛ ደመወዝ ተቀጥረዋል
  • ሊቀ ጳጳሱ ሥራ አስኪያጁን ያገዱበት ርምጃ የሀ/ስብከቱን አድባራት ተቃውሞ ቀስቅሷል
  • ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ በታገዱት ሥ/አስኪያጅ ምትክ ለመመደብ ከሊቀ ጳጳሱ ጋራ እየተሸማገሉ መኾናቸው ተሰምቷል
  • ፓትርያሪኩ እግዱ ተነሥቶ ሥ/አስኪያጁ ወደ ሓላፊነታቸው እንዲመለሱና የእግዱ አግባብነት እንዲጣራ ለጠ/ቤ/ክህነቱ ጽ/ቤት የሰጡት መመሪያ አልተፈጸመም፤ /ሥ/አስኪያጁ እግዱን ለማስፈጸም ዳተኛ ሲኾኑ ሊቀ ጳጳሱ ደግሞ ላልተገባ ርምጃቸው ድጋፍ ለማግኘት የሀ/ስብከቱን አጥቢያ አብ/ክርስቲያን ሓላፊዎች ነገ ስብሰባ ጠርተዋል
  • አቡነ ሕዝቅኤል በዕጩነት በቀረቡበት የስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ ድጋፍ ነፍገውኛል ያሏቸውን እየተበቀሉ ነውን?
metering the sunsetየጥቅምት 2005 ዓ.ም ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በአራት አህጉረ ስብከት እንዲከፈል ሲወስን በሀ/ስብከቱ የተንሰራፋውን የሙስናና የመልካም አስተዳደር ችግር በዘላቂነት እንደሚፈታው በመታመኑ ነበር፡፡ ምልአተ ጉባኤው ስለ ውሳኔው ያወጣው መግለጫ ቃል የሚከተለውን ይላል፡-
በቅ/ሲኖዶስ የተቋቋመው ኮሚቴ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ችግር ለመፍታት አጥንቶ ያቀረበውን ጥናታዊ ጽሑፍ የመረመረው የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በጥናቱ መሠረት የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በአራት አህጉረ ስብከት ቢከፈል ለአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ቅርበት ያለው አገልግሎት መስጠት የሚችል ከመኾኑም በላይ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አካባቢ የሚታየው የአስተዳደር ችግር በዘላቂነት እንደሚፈታው በመታመኑ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በምሥራቅ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን፣ በደቡብ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት እንዲደራጅ ወስኗል፡፡
የምልአተ ጉባኤውን ውሳኔ አስመልክቶ የቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ከብዙኀን መገናኛ ለቀረበላቸው ጥያቄ በወቅቱ በሰጡት ምላሽ÷ ‹‹አቤት ባዩ በዛ፤ ጩኸት በዝቷልና ሁሉም በአካባቢው እንዲስተናገድ በሊቃውንትም በአባቶችም ተጠንቶ ቀጠሮ ተይዞበት የቆየ ነው፤›› ብለው ነበር፡፡

ሰበር ዜና – ጠቅላይ ቤተ ክህነት በአጥማቂ ነኝ ባዩ ግርማ ወንድሙ ላይ የተላለፈውን እግድ አጸና!


  • ውሳኔው የአጥማቂ ነኝ ባዩን ሥርዐተ አልበኝነት ሲቃወሙና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ለማስከበር ሲጋደሉ ለቆዩት የደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ሰንበት ት/ቤት አባላትና ምእመናን ታላቅ ድል ነው፡፡
  • ሰንበት ት/ቤቱ እና ምእመናኑ የውሳኔውን አፈጻጸም በቀጣይነትና በጋራ ሊከታተሉ ይገባል
  • ሕገ ወጥ ሰባክያንና አጥማቂ ነን ባዮች ችግር የሚፈጥሩባቸው ሌሎች አጥቢያዎችስ ከዚህ ምን ይማራሉ?BeteKihnet banned Girma

Tuesday, May 14, 2013

ስመ ‹‹መቲራ››ው ሲመተር! ቀንደኛው ፅልመታዊና ሙሰኛ ‹‹አባ›› ገ/መድኅን ገ/ጊዮርጊስ ወደ መንበረ ፓትርያሪኩ እንዳይገቡ ታገዱ!


  • ጀብደኛው ሙሰኛ ‹‹አባ›› ገብረ መድኅን በመንበረ ፓትርያሪኩ አሠራር ጣልቃ በመግባት፣ ከሥ ሓላፊዎችና ከጥበቃ አባላት ጋራ ሁከት በመፍጠር አቤቱታ ቀርቦባቸዋል
  • Abba Gebre Medhin banned
  • ከምስጉን አቋማቸው በመንሸራተት ከሙሰኞች ጋራ መተቃቀፍ የጀመሩት አቡ ሕዝቅኤል በሙሰኛው ‹‹መነኩሴ›› ላይ የተላለፈውን እግድ በጣልቃ ገብነት መቃወማቸው አስገራሚ ኾኗል

Thursday, May 2, 2013

ስለ ሃይማኖት ተቋማት ምዝገባ አንዳንድ ነጥቦች


*ቀለመ ወርቅ ሚደቅሳ
ምንጭ፡- ዕንቁ መጽሔት፣ ቅጽ 6 ቁጥር 90፣ ሚያዝያ 2005 ዓ.ም
መንደርደሪያ
የሃይማኖት እና የእምነት ነጻነት መብት መሠረታዊ የሰብአዊ መብት አካል ነው፡፡ የሃይማኖት ነጻነት መብት የምንለው አንድ ሰው ፈጣሪ መኖሩን በመሰለው መልክ በመበየን ብቻውን ወይም ከሌሎች ጋር የሚኖረውን የማምለክ መብት የሚገልጽ ነው፡፡ የእምነት ነጻነት ደግሞ ፈጣሪ የለም ብሎ ከማመን ጀምሮ አንድ ሰው የእምነት ጉዳይን በሚመለከት ያለውን ነጻነት የሚመለከት ነው፡፡
በቅርብ ዓመታት ውስጥ በተደረገ የሕዝብ ቆጠራ ከአጠቃላዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ 97% የሚኾነው ‹‹ሃይማኖተኛ›› መኾኑን ከብሔራዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ የተገኘ መረጃ ይገልጻል፡፡ ከዚህ ነጥብ በመነሣት በኢትዮጵያ ውስጥ የሃይማኖት ጉዳይ ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው ማኅበራዊ ጉዳይ መኾኑን መደምደም ይቻላል፡፡ በተጨማሪም የእምነት ነጻነት ጉዳይ ያለው ሽፋን አነስተኛ መኾኑን ማየት ይቻላል፡፡ በመኾኑም የዚህ ጽሑፍ ትኩረት የሃይማኖት ጉዳይ ላይ ይኾናል፡፡
የሃይማኖት ነጻነት መብት በግል የሚያምኑበትን ሃይማኖት መምረጥን ወይም መያዝን፣ ሃይማኖትን ለብቻ ወይም ከሌሎች ጋር በመኾን ማምለክን፣ መተግበርን፣ ማስተማርን ወይም መግለጽን ያጠቃልላል፡፡ በእነዚህ ዝርዝር መብቶች በጋራ ተጠቃሚ ለመኾን አንድ ቡድን የሃይማኖት ተቋሙ የሕግ ዕውቅና እንዲያገኝለት ያስፈልገዋል፡፡ ይህ ጽሑፍ ከሃይማኖት ተቋማት ምዝገባ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማንሣት ይሞክራል፡፡
የሃይማኖት ነጻነት መብት የሕግ ማዕቀፍ  

የሕማማት ዋዜማው ሕማም! የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ህልውና እና የክህነታዊ ሥልጣን ማእከላዊነት በምዝገባና ፈቃድ ዕድሳት በሚሸረሽር እና በሚያፋልስ የመመሪያ ረቂቅ ላይ እየተመከረ ነው

Sebeka Gubae General Structure
  • ቤተ ክርስቲያን ፍትሐ ብሔር ሕጉ ያገኘችውን ሕጋዊነት የሚከልስ፣ ታሪካዊ ክብሯን የሚያንኳስስ፣ ማኅበራዊ እሴቷን የሚቀንስና አሐቲነቷን የሚያፈርስ በምትኩ የመንግሥትን የቁጥጥር አቅም የሚያፈረጥምና የሚያነግሥ ነው፡፡
  • የሃይማኖትና መንግሥት ግንኙነትን ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ የሚጥስ መመሪያ ነው
  • የሃይማኖት ተቋማትን ልዩ መንፈሳዊና ድርጅታዊ ጠባይ ያገናዘበ መመሪያ አይደለም
  • መመሪያው ለአድልዎና ብልሹ አሠራር የመጋለጥ ዕድሉ የሰፋ ነው
  • መመሪያው የአሐቲ ቤተ ክርስቲያንን መርሕ በመጣስ የፕሮቴስታንቲዝምን ራስ በቀል ዘይቤ የሚያስፋፋ ነው፡፡
  • ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱን ያሳዘነውና የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትን ጨምሮ የሕግ ምሁራንን ያነጋገረው የመመሪያው ረቂቅ ከቅዱስ ሲኖዶሱ ዐበይት አጀንዳዎች አንዱ እንደሚኾን ተጠቁሟል
የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ‹‹የሃይማኖት ተቋማትን ለመመዝገብ›› በሚል በቅርቡ ለውይይት የዘረጋው የመመሪያ ረቂቅ፣ በአገራችን ታላቅ ፋይዳ ያላቸውን የሃይማኖት ተቋማት ልዩ መንፈሳዊ ጠባይ እና ድርጅታዊ አሠራር ያላገናዘበ በተለይም ጥንታዊትና ብሔራዊት የኾነችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ሰውነት የሚከልስና ማእከላዊ አሠራሯን የሚያፈርስ እንደኾነ እየተገለጸ ነው፡፡
የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በዐዋጅ ቁጥር 691/2003 አንቀጽ 14/1/ሸ የተሰጠውን ሥልጣንና ተግባር ለመወጣት በሚል መዘጋጀቱ የተገለጸው የመመሪያው ረቂቅ፣ አስፈላጊ የኾነባቸው አራት ነጥቦች በመግቢያው ላይ ተመልክተዋል፡፡ ከእኒህም ዋነኛው ‹‹ለሃይማኖት ወይም እምነት ተቋማት በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጠው÷ የሃይማኖት ነጻነት፣ እኩልነትና የመደራጀት መብት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ለማስቻልና ነጻነታቸው እንደተጠበቀ ኾኖ አሠራራቸው ከሕገ መንግሥቱና ከሌሎች የአገሪቱ ሕጎች ጋራ በተጣጣመ ኹኔታ እንዲቀጥል ለማድረግ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ነው፤›› በሚል ሰፍሯል፡፡

Wednesday, April 24, 2013

በአዲስ አበባ 3 ዓመት አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው የቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ቦታ የኢንደስትሪ ዞን ነው በማለት ፈረሰ

ቅዱስ ሩፋኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 15 2005 ዓ.ም)፡- በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 የሚገኝው የቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን በኢንደስትሪ ዞን ላይ የተሰራ ነው በሚል የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ለቅዱስ ሲኖዶስ በጻፈው ደብዳቤ 24 ሰዓት ሳይሞላው ማፍረሱን የደብሩ ኃላፊዎች አስወቁ፡፡

ሚያዚያ 9 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ አንድ ሰዓት ሲሆን የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ ኤልሳቤት መንግስቱ የደብሩን ኃላፊዎች በጽ/ቤታቸው እንዲገኙ የስልክ ጥሪ በማድረግ ቤተክርስቲያን እዲያፈርሱ የነገሯቸው መሆኑን ያስረዱት የደብሩ ኃላፊዎች ቤተ ክርስቲያን የማፍረስ ስልጣን  የእነሱ አለመሆኑን በመግለጻቸው በማግስቱ ጠዋት 3 ሰዓት ወረዳው ለሲኖዶስ የላከው ደብዳቤ ይዘው ከወረዳው ተወካይ ጋር በሲኖዶስ ተገናኝተው እየተወያዩ ሳለ የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ በሶስት መኪና ፖሊስ በመታገዝ በሕገ ወጥ መንገድ እንዲፈርስ ማድረጋቸው የደብሩ ኃላፊዎች  አስታወቁ፡፡

ስለ ዴር ሡልጣን ገዳም የኢትዮጵያው ቅ/ሲኖዶስ ከግብጽ ቅ/ሲኖዶስ ጋራ ይወያያል


    His Holiness on Interview
  • ፓትርያሪኩ የቅድስት ሀገር የታሪክና ቅድስና ይዞታችንን ለማስከበር ሕዝባዊ ዲፕሎማሲው ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል
  • ፓትርያሪኩ የ፳፻፭ ዓ.ም በዓለ ትንሣኤ የኢየሩሳሌም ተሳላሚ ምእመናንን አሰናብተዋል፤ እጅጋየሁ በየነ ሕገ ወጥ ጥቅም የምትሰበስብበት ‹አስጎብኚና የጉዞ ወኪል› በስንብት መርሐ ግብሩ አልተካተተም
  • ‹‹የዴር ሡልጣን ችግር ከመካከለኛው ምሥራቅ ጠቅላላ ገጽታዎች ተለይቶ መታየት የለበትም፡፡›› /በግብጽ መንግሥታዊ ሥልጣን የያዘው የእስላም ወንድማማቾች አቋም/
  • ‹‹ጉዳዩ ብሔራዊ ስለኾነ ከዐረብ ወንድሞቻችንና ከእስላሞች ጋራ ካልኾነ በቀር ወደ ኢየሩሳሌም አንገባም፡፡ ይህን በተመለከተ ሁላችንም በአንድነት ቆመናል፡፡›› /ፖፕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ዴር ሡልጣንን በተመለከተ በእስራኤል ላይ የቱሪዝም ጫና ለመፍጠር የሞከሩበት ጋዜጣዊ መግለጫ/
  • ‹‹ኢትዮጵያውያን ምእመናን በታሪክ ይዞታችንና በወገኖቻችን መካከል በብዛት መገኘት ለቅድስና ይዞታችንና ለወገኖቻችን ክብር በቀላሉ የማይገመት ዋስትና ያለው ነው፡፡ ጉዟችን ከሁሉም አቅጣጫ ድጋፍ እያገኘ በበለጠ ከቀጠለ በታሪክ ይዞታችን ላይ ያለው ችግር መፍትሔ አግኝቶ የመንፈስ ዕረፍትና ርካታ እንደሚገኝ ተስፋ አለን፡፡›› /በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ ለተሳላሚዎች ከተናገሩት/

Friday, April 19, 2013

ከሸፈ እንዴ?! ‹‹ዜና ቤተ ክርስቲያን›› ጋዜጣ በመጽሔት ቅጽ መታተም ጀመረ!


His Holiness Abune Matyas Zena BeteK Magazine Cover
  • መጽሔቱ የቤተ ክርስቲያንን የሕዝብ ግንኙነት ሥራ የሚያጠናክር ነው፡፡
  • በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች በየሩብ ዓመቱ በላቀ የኅትመት ጥራት ይዘጋጃል፡፡
  • አዘጋጂው በአዲስ መልክ የተዋቀረው የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው፡፡
  • የዝግጅቱ ውጥን ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በ፳፻፭ ዓ.ም የበጀት ዓመት ለማካሄድ ካቀደው ተቋማዊ የአደረጃጀት ለውጥና የወቅታዊ እንቅስቃሴዎችን መረጃ በተሻለ አሠራር ከመቀመር አኳያ በመምሪያው የሕዝብ ግንኙነት ቁልፍ ተግባራት ውስጥ ቀደም ብሎ ዓላማና ግብ ተወስኖለት የተካተተ እንጂ ከፓትርያሪኩ ‹‹የዜና መዋዕል ዝግጅት›› ጋራ ፈጽሞ የተያያዘ አይደለም፡፡
  • መጽሔቱ ቤተ ክርስቲያናችን በኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መስኮች የምታከናውናቸው ተግባራትና ውጤቶቻቸው በአገር ውስጥና በውጭ ባለድርሻ አካላት እንዲታወቁ እንዲሁም ‹‹ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት ስትራቴጂ›› ላይ አተኩሮ ይዘጋጃል፡፡
  • በመጽሔቱ ዝግጅት ሂደት የሚገኘው ልምድ ወደፊት ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ መጽሐፍ እንዲኖራት በመምሪያው ለታሰበው ዕቅድ ግብዓት እንደሚኾን ተመልክቷል፡፡
  • ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ የመጽሔቱ ኅትመት ወቅቱን ጠብቆ እንዲቀጥል መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ እናስ፣ የከሸፈው÷  የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አራማጁ ብሎግ ወይስ የመጽሔቱ አዘጋጆች ዕቅድ?!

Thursday, April 18, 2013

ሰበር ዜና – ‹‹ለፓትርያሪኩ መመሪያ ለመስጠት ተዘጋጅተዋል›› የተባሉት ኣባይ ፀሃየ ከደጅ ተመለሱ


  • በሦስት ቡድኖ የተደራጀው የጨለማው ቡድን ‹‹የኣባይ ፀሃዬን አመራር›› ያቀናጃል
  • መመሪያው÷ የልዩ ጽ/ቤት፣ ፕሮቶኮል፣ ጥበቃ ሓላፊዎችን ምደባ ይመለከታል ተብሏል
  • ‹‹ኣባይ ፀሃዬ ከስኳር ኮርፖሬሽን በተጨማሪ ጠቅላይ ቤተ ክህነትን በበላይነት እንዲመሩ ከመንግሥት ትእዛዝ ተላልፏል፡፡ የትግራይ ተወላጆች የግቢውን አመራር ሙሉ በሙሉ እንረከበዋለን፡፡ ከዚህ በኋላ ቤተ ክርስቲያን በትግራዎት እንጂ በአማራ አትመራም፡፡ ለሚኒስትሮች የሚፈለገውን ጥቅም እያቀረብን እናስፈጽመዋለን፡፡››
/ኣባይ ፀሃዬ ለፓትርያሪኩ የሚሰጡትን ‹‹አመራር›› ከእነ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ጋራ ያስተባብራሉ የተባሉት በምሥራቅ ትግራይ የደብረ ኣላማ አሲራ መቲራ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም አበምኔት አባ ገብረ መድኅን ኀይለ ጊዮርጊስ ዛሬ ጠዋት የተናገሩት/
  • ፓትርያሪኩ ‹‹አባ›› ነኝ ባዩን ከግቢው እንዲያርቁላቸው መመሪያ ሰጥተዋል፤ ተፈጻሚነት ይኖረው ይኾን?
  • መንግሥት፣ የቤተ ክርስቲያን አመራርና ምእመኑ ጉዳዩን ከምር አጢነው አቋም እንዲወስዱ ተጠይቋል፡፡
abai-tsehaye-tigraionline
አቶ ኣባይ ፀሃዬ
ከአምስተኛው ፓትርያሪክ ኅልፈተ ሕይወት በኋላ፣ የመንበረ ፓትርያሪኩን ላዕላይ መዋቅሮች በመቆጣጠርና ለተቋማዊ ለውጥ የታቀዱትን ተግባራት በማምከን÷ 1)ቡድናዊና ግለሰባዊ ጥቅሙን አስጠብቆ ለመቆየት፣ 2)ኦርቶዶክሳዊ ማንነትን በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ደብዛውን ለማጥፋት በልዩ ኹኔታ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የጨለማው ቡድን÷ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን በጎጠኝነት፣ በፖሊቲካዊ ታማኝነትና በጥቅም ስቦ እና አቅርቦ ማሰለፍ መጀመሩ ተዘገበ፡፡

በረኀብ የተዳከሙት ደቀ መዛሙርት ልመና በፖሊስ ታገደ፤ ፖሊስ ደቀ መዛሙርቱን ለመርዳት ከሚሞክሩ ምእመናን ጋራ ተወዛግቧል


  • ሓላፊዎቹ ከመምህራን የቀረቡላቸውን ሦስት ማግባቢያዎች በሙሉ ውድቅ አድርገዋል
  • ደቀ መዛሙርቱ በኮሌጁ አስተዳደር ላይ ክሥ መመሥረታቸው ተጠቁሟል
  • በአዲስ አበባ ዘመድ/መጠጊያ የሌላቸው ደቀ መዛሙርት በእጅጉ ተቸግረዋል
  • ፓትርያሪኩ ‹‹ጣልቃ አልገባም›› ማለታቸው የመምህራኑን ጥረት ጎድቷል
  • ‹‹ሃይማኖት የሌለው መምህር አያስተምረንም ባልን በረኀብ እየተቀጣን ነው›› /በደቀ መዛሙርቱ ከተለጠፉት ጥቅሶች አንዱ/
ሚያዝያ 7 ቀን 2005 ዓ.ም፤ ንጋት ላይ ነው፡፡ በአራት ኪሎ ወ.ወ.ክ.ማ በኩል ወደ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴCollege bld 01 ካቴድራል በሚያስገባው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሦስተኛ በር በርካታ ምእመናን ተሰባስበዋል፡፡ ዕለቱ የቅድስት ሥላሴ ወርኀዊ በዓል መታሰቢያ እንደመኾኑ የምእመናኑ ቁጥር ከፍተኛ ነበር፡፡ በኮሌጁ ቅጽር ውስጥ ቆመው ጥቁር ቀሚሳቸውን እንደለበሱ መሥመር ይዘውና ፊታቸውን በካቴድራሉ መውጫና መግቢያ ላይ አድርገው በዝምታ የቆሙትን ደቀ መዛሙርት ይመለከታሉ፡፡ የብዙዎቹ ደቀ መዛሙርት ገጽታ ድካምና ጉስቁልና ይነበብበታል፡፡ ከፊት ለፊታቸው ነጭ ጨርቅ ተዘርግቷል፡፡

Sunday, April 14, 2013

የቅ/ሥላሴ መን/ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት ቀሚሳቸውን አንጥፈው ሲለምኑ ዋሉ

His Grace Abune Timothy
ብፁዕ አቡነ ጢሞቲዎስ
የኮሌጁ የበላይ ሃላፊ ሊቀ ጳጳስ

  • የኮሌጁ ካፊቴሪያ ለደቀ መዛሙርቱ ምግብ እንዳያዘጋጅ በሊቀ ጳጳሱ ታዝዟል
  • ሊቀ ጳጳሱ ሁሉም መምህራን በመደበኛው የቀን መርሐ ግብር እንዳያስተምሩ ከልክለዋል
  • ሊቀ ጳጳሱ በቅ/ሲኖዶስ ውሳኔ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ሥራውን እንዳይጀምር አድርገዋል
  • በሊቀ ጳጳሱ ዙሪያ የተሰለፈው የቤተ ክህነቱ የጨለማ ቡድን ፓትርያሪኩንም እያሳሳተ ነው
  • ደቀ መዛሙርቱን ለማስወጣት የተጠራው የፖሊስ ኀይል ርምጃ ለመውሰድ ፈቃደኛ አልኾነም
  • በኮሌጁ የሚዘዋወሩ ስመ ደኅንነቶች ደቀ መዛሙርቱን፣ መምህራኑንና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን እያስፈራሩ ነው
ይህ ፻ውን የሐራ ዘተዋሕዶ ዘገባ ለንባብ ያበቃንበት ጦማር ነው፡፡ ከጦማሮቹ የሚበዙት የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ተቋማዊ መገለጫ ለመኾን ስለ ደረሰው ጥቅመኝነትን የመከባከብ፣ ሙስናንና የአሠራር ብልሹነትን የማንገሥ፣ ከሙሰኞችና ጥቅመኞች ጋራ የመደራደር አስተሳሰብና ተግባር የሚመለከቱ ናቸው፡፡ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር እና የደቀ መዛሙርቱ ውዝግብ አያያዝና እየተወሳሰበ የመጣበት ኹኔታ ከዚህ የተለየ መነሻ የለውም፡፡
የኮሌጁ መምህራን እንደሚናገሩት፣ የትምህርት አስተዳደሩ እንዲሻሻልና የደቀ መዛሙርቱ አካዳሚያዊ መብቶች እንዲከበሩ የቀረቡ ጥያቄዎችን ሓላፊነት በተሞላበት መንገድ ደቀ መዛሙርቱን ከመምህራኑ ጋራ በግልጽ በማወያየት ምላሽ መስጠት ይቻላል፡፡ ይህም ካልኾነ የመማር ማስተማሩን ጤናማነት/ሰላማዊነት ለመጠበቅ ተቃውሞ የቀረበባቸውና ከደቀ መዛሙርቱ ጋራ መስማማት ያልቻሉ መምህራን ከሓላፊነታቸው ገለል እንዲሉ ማድረግ ነው፡፡
ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ
(የኮሌጁ የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ)
እየኾነ ያለው ግን ላለፉት 14 ዓመታት በኮሌጁ የበላይ ሓላፊነት ከቆዩ ሊቀ ጳጳስ የሚጠበቅ አይደለም፡፡ ደቀ መዛሙርቱ በቅ/ሲኖዶስ የተቋቋመው ኮሚቴ የማጣራት ሥራውን ጨርሶ ጥያቄያቸው ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ የተቃውሟቸው ሁለቱ ሓላፊዎችና መምህራን ወደ ክፍል ገብተው እንዳያስተምሩ በመከላከላቸው እልክ የተጋቡት ሊቀ ጳጳሱ ‹‹ያቋረጣችኹትን ትምህርት በአግባቡ አልጀመራችኹም›› በሚል የቀኑ መደበኛ መርሐ ግብር ከመጋቢት 30 ቀን ጀምሮ የተዘጋ መኾኑን የኮሌጁን ክብ ማኅተም ይዞ መጋቢት 30 ቀን 2005 ዓ.ም ጠዋት በወጣ ማስታወቂያ አሳስበዋል፤ በቁጥር 181 ያህል የሚኾኑት የቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርትም ንብረት አስረክበው በአስቸኳይ ከኮሌጁ እንዲወጡ አዝዘዋል፡፡

የኮሌጁ የቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርት ኮሌጁን እንዲለቁ ታዘዙ


  • መንሥኤው ‹‹ትምህርት በአግባቡ አልጀመራችኹም›› የሚል ነው
  • ‹‹ማስታወቂያው ለብቀላና እስር ሰበብ መፈለጊያ ነው›› /ደቀ መዛሙርቱ/
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር የቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርት ከዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ የኮሌጁን ንብረት እያስረከቡ ኮሌጁን እንዲለቁ አሳሰበ፡፡ ኮሌጁ ማሳሰቢያውን በዛሬው ዕለት በቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርቱ ላይ ያወጣው ‹‹ያቋረጣችኹትን ትምህርት አግባብነት ባለው መንገድ አልጀመራችኹም›› በሚል ነው፡፡
Holy Trinity College Academic Programs
የኮሌጁ የትምህርት መርሐ ግብር

Wednesday, April 10, 2013

መታሰር ያልሰለቸው ቀበሮ መነኩሴ




(አንድ አድርገን ሚያዚያ 1 2005 ዓ.ም)፡- በደብረ ብርሐን ከተማ አባ በረከት የሚባል ሰው በገዳማት እና በአድባራት ላይ ብዙ ጉዳት እንዳደረሰ ገልጸን ከወራት በፊት መጻፈችን ይታወሳል፡፡ አባ በረከት መጀመሪያ ጎንደር ይኖር የነበረ ከዚያም ደንጨት ዮሐንስ ገዳም ሲያገለግል የነበረ ሰው ሲሆን ከመንዝ አካባቢ እንደመጣ የጀርባ ታሪኩ ይናገራል ፡፡ የካቲት 2004 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሐን ከተማ በደብረ ማዕዶት ቅድስት አርሴማ ገዳም በመግባት ሲያገለግል እንደነበር መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡ በዚህ ገዳም የሚመጡ በርካታ እህቶችን በማታለል ዝሙት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ ስለተደረሰበት ይህን ድርጊቱን እንዲያቆም ከወንድሞች ምክር ተሰጥቶትም ነበር፡፡  በቤተመቅደስ ውስጥ ድፍረትና ክህደት የተሞላበት የአማኙን እምነት የሚቀንስና ለትልቅ ድፍረት የሚያደፋፍር እንቅስቃሴዎች ሲያደርግ እንደነበር በጊዜው በቦታው የነበሩ የአይን እማኞች  ገልጸዋል ፤ ገዳም ሲገባ አብራው የመጣች ወለተ መስቀል የምትባል  መነኩሴ የነበረች ሲሆን ፤ በገዳሙ በነበረው ቆይታ ለገዳማውያን አገልጋይ ካህናት ‹‹ከአንድ እናት ማህጸን የወጣን እህቴ ነች›› እያለ ሲያወራ እና ሲያስወራም ነበር ፡፡(ሴትየዋ በአሁኑ ሰዓት ከአባ በረከት የልጅ እናት ሆናለች)፡፡ ይህ ሰው አውደ ምህረት አግኝቶ የለሰለሰ የኦርቶዶክስ የሚመስል ውስጡ እሾህ የሆነ ትምህርት ባያስተምርም እንኳን ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፤ ስለ ቅዱሳን መላእክት ፤ ስለ ጻድቃን ሰማዕታት ያማልዳሉ? አያማልዱም? የሚል አርእስት በማንሳት በርካታ እህቶች ፤ ወንድሞችና የአብት ተማሪዎች ላይ ውስጥ ውስጡን ምንፍቅና ሲዘራ እንደነበር ከእሱ ጋር ከተወያዩ ጥቂት ምዕመና አማካኝነት ለማወቅ ተችሏል ፡፡

Friday, April 5, 2013

የነገረ መለኰት ምሩቃን ማኅበር አባላት የተሐድሶ ኑፋቄን እንዲዋጉ ፓትርያሪኩ አሳሰቡ


  • ማኅበሩ በሦስት አህጉረ ስብከት ቅርንጫፍ ቢሮዎችን ከፍቷል
  • የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ሥራ አስፈጻሚን በዳግም ምርጫ አጠናክሯል
  • መናፍቁ አሰግድ ሣህሉን ለማስመረጥ የተደረገው ሙከራ ተቀባይነት አላገኘም
  • ሁለት የፀረ – ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ሰባክያንና ዘማርያን ጥምረት አባላት በሥራ አስፈጻሚነት ተካተዋል
  • ማኅበሩ ሕጋዊ ዕውቅናና ተቀባይነት ካላቸው የቤተ ክርስቲያናችን አካላት ጋራ ሁሉ ተባብሮ ለመሥራት ያለውን ዝግጁነት ዳግም አረጋግጧል
Theology Association Logoበቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እና በቅዱስ ፍሬምናጦስ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ምሩቃንን በአባልነት በመያዝ የተመሠረተ ነው፤ ዋና ዓላማው÷ የወንጌል ትምህርት ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች ሐዋርያዊ አገልግሎት መስጠት፣ የቤተ ክርስቲያናችን ዶግማ፣ ሥርዐት፣ ትውፊት እና ንዋያተ ቅድሳት በአግባቡ እንዲጠበቁ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ ነው – የነገረ መለኰት ምሩቃን ማኅበር፡፡
ማኅበሩ ዓላማውን የሚተገብርባቸውየስብከተ ወንጌል፣ የትምህርት፣ የኅትመትና ሥርጭት፣ የሕግ፣ የልማት፣ የመረጃና መዛግብት፣ የሒሳብና ንብረት አስተዳደር እንዲሁም የቁጥጥር ክፍሎችን አዋቅሯል፤ እኒህን ተግባራት የሚያስፈጽሙ 12 የሥራ አስፈጻሚና አፈጻጸሙን በበላይነት የሚመሩ 12 የሥራ አመራር አባላት እንዳሉትም ማኅበሩ ያሰራጫቸው መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

Tuesday, April 2, 2013

የኮሌጁ አስተዳደር የቀን መደበኛ መርሐ ግብር ላልተወሰነ ጊዜ መዘጋቱን አስታወቀ


  • ማስታወቂያው የተለጠፈው በመርሐ ግብሩ አስተባባሪ ዘላለም ረድኤት ነው
  • ደቀ መዛሙርቱ በተቃውሟቸው ለመቀጠል በመስማማት ትምህርት ጀምረዋል
  • ‹‹ሲያስወጡን እንተናነቃለን፤ ኮሌጁን ቅ/ሲኖዶስ እንጂ ዘላለም አይዘጋውም›› /ደቀ መዛሙርቱ
  • የኮሌጁ የበላይ ሓላፊ ‹‹[ለደቀ መዛሙርቱ] እንኳን ምሳ ራት አልሰጥም›› እያሉ ነው
ሙስናንና የአሠራር ብልሹነትን በመቃወም ከሁለት ሳምንት በላይ በተቃውሞ የሰነበቱት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የቀን መደበኛ መርሐ ግብር ደቀ መዛሙርት በትላንትናው ዕለት ረፋድና ከሰዓት በኋላ በክፍል በመገኘት ትምህርት ጀምረዋል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ትምህርት በማቋረጥና በካፊቴሪያው ከመመገብ በመከልከል በኮሌጁ እየከፋ የመጣው ሙስናና የአሠራር ብልሹነት እንዲስተካከል፣ ለዚህም ተጠያቂ ናቸው ያሏቸው ሁለት ሓላፊዎች ከቦታቸው እንዲነሡ ያቀረቡትን ጥያቄ እየተማሩም ለመቀጠል በመወሰን ነው ትምህርታቸውን ለመጀመር የተስማሙት፡፡