![]() |
| ግራኝ መሀመድ አልጋዚ |
Monday, September 14, 2026
የአሕመድ ግራኝ ጦርነትና ተጽዕኖዎቹ
Saturday, September 12, 2026
የዋሺንግተን ዲሲና አካባቢው ሃገረ ስበከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ፋኑኤል አደገኛ የቁልቁለት መንገድ
![]() |
| ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል |
በፍቅር ጠብቆ አደረሰን በማለት የመልካም ምኞታችንን ከዚህ ከዝግጅት ክፍላችን ለማስተላለፍ እንወዳለን።
መጪውም ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የፍሠሀ፣ እንዲሁም የንሥሃ ዘመን እንዲሆንልን ልባዊ ምኞታችንን ለመግለጽ እንወዳለን፤ በዚህ ሣምንት መጀመሪያ አካባቢ የደረሰንን ዜና ይዘን በዚህ በዓዲስ አመት ለመምጣት ያስገደደን ነገሩ ትንሽ አስደንጋጭ እና አሳሳቢም በመሆኑ ይሄንኑ ከወዲሁ ለማስታወስ እንወዳለን።
በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው የዋሺንግተን ዲሲና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ ፋኑኤል ለአንድ አጥቢያ ምሥራቀ ጸሐይ አቡነ ተክለሃማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት አባ ፍቅረ ማርያም አስተራይ ለተባሉ መነኩስ እጅግ አደገኛ የሆነ ፤ እና የምዕመናንና የሰበካ ጉባኤ አባላትን ሃላፊነት እና ቦታ ያላገናዘበ እጅግ በጣም ከፋፋይ እና መሰሪ የሆነ ደበዳቤ በድብቅ ጽፈው ለአስተዳዳሪው በመስጠት፤ አስተዳዳሪውም ባለፍው ሣምንት ውስጥ ለአካባቢው ፖሊስ ጠርተው የማይፈልጓቸውን ሰዎች ከቤተክርስቲያን ቅጽር እንዲባረሩ እና በድጋሚ ወደ ቤተክርስቲያን እንዳይመለሱ በማድረግ እጅግ በጣም ከባድ እና አደገኛ አካሄድ መጀመራቸውን የሰማንው በዚህ ሣምንት መጀመሪያ አካባቢ ነበር፤
Wednesday, September 9, 2026
የቃሊቲ ክፍለ ከተማ አገልጋይ መልአከ ሕይወት ተስፋዬ ጀንበሬ እግድ ተነሳ

![]() ![]() |
| መልአከ ሕይወት ተስፋዬ ጀንበሬ |
የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም
Wednesday, September 2, 2026
ኦቦ በላይ መኮንን ከእሥር መፈታታቸው ተነገረ
![]() |
| ኦቦ በላይ መኮንን (ዋቄ ፈና) |
ኦቦ በላይ ከእሥር መፈታታቸው እየተነገረ ነው፤
የቀሲስ በላይ ቀጣይ ሁኔታ ምን ሊሆን ይችላል?
ቀሲስ በላይ እደምናስታውሰው የኦሮሚያ ቤተክህነት አደራጅ እና ሃላፊ ሆነው ይሰሩ እንደነበር የሚታወስ ነው፤ ይሄንንም ተከትሎ በተለያየ ጊዜ ከሚሰጡ መግለጫዎች ጋር እና አቡነ ሣዊሮስ እና እነ አቡነ ኤዎስጣቲዎስ እነ አቡነ ዜና ማርቆስ በተደጋጋሚ አብረዋቸው ይታዩ እንደነበር ይታወሣል፤ በመሆኑም በቀጣይነት ለቀሲስ በላይ ከእሥር በፊት የነበራቸውን የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊነትን ይሰጧቸው ይሆን?
Saturday, July 11, 2026
ሥር እየሰደደ የሄደው የምሥራቅ ጎጃም “ቅብዓት” የክህደት አምልኮ ወደ ሰሜን አሜሪካ እየተዛመተ እንደሆነ ተነግሯል፤
![]() |
| የምሥራቅ ጎጃም ተሿሚው |
እንቅስቃሴዎች በቅርበት ለተከታተለው፤ <<እንቁላል በቆይታ በእግሯ ትሄዳለች>> የሚለው አካሄድ በትክክል የሚያጠናክር አካሄድ እየሄዱ እንዳለ በደንብ መረዳት ይቻላል። በተለይ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ “ጳጳሳትን ሾመናል” ብለው ወደ ፊት ከመጡ በኃላ በበቤተክርስቲያን በኩል ምንም አይነት ምላሽ አልተሰጠም፣ ምንም አይነት እርምጃም አልተወሰደም፤ ይሄ ደግሞ የሚነግረን አንድ ጠንከር ያለ አካሄድ እንዳለ በትክክል የሚያስረዱ ሁኔታዎች እንዳሉ መረዳት የሚያዳግት አይመስለንም፤ በተለይ በኦሮሚያ ቤተክህነት፣ በአቡነ ሰላማ ቤተክህነት ምረታ ማግስት የተከሰቱ በርካታ ደም አፋሳሽ እውነታዎች ለምን በምሥራቅ ጎጃም እንደዚህ አይነት እርምጃም ሆነ አካሄድ መሄድ ተሳናቸው የሚለው ትልቁ እና ዋነኛው ጥያቄ እንደሆነ ብዙዎች የሚረዱት ይመስለናል።
“ቅብዓት” የሚለው እምነት ምን አይነት መሰረት አለው? የሚለውን በጥቂቱ ብንመለክት ምናልባት አካሄዳቸው እና መጥነው የሚረግጡት ብዙ ማሳያዎችን ብንመለከት ትንሽ ነገሮችን ሊያጠራልን ይችላል ብለን ስላሰብን ጥቂት የእምነቱን መሰረት የሆኑትን ነገሮች እናንሳ፤ በቅብዓት እምነት “ወልድን በሰውነቱ ከተዋሕዶ በኃላ ፍጡር አንለውም” ይሉናል፤ በሌላ በኩል “ፍጡር ሥጋን አልተዋኃደም” ይላሉ እስቲ እነዚህን እንተንትናቸው፤ ወልድን በሰውነቱ ከተዋሕዶ በኃላ ፍጡር አንለውም - በቅድስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ወልድ የምንነው የእግዚአብሔር አብ ድኅረ ዓለም ያለ እናት፤ በኃላም ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት የተወለደው እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በተለይ ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን፤ ነከፍሷ ነፍስን ነስቶ ፍፁም ሰው ፤ ፍፁም አምላክ ሆኖ መወለዱን የቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ይነግረናል፤ ነገር ግን እንደ “ቅብዓት” እምነት ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው እግዚአብሔር ወልድ ፍፁም ሰው የሚለውን አይቀበሉም ፤ የእመቤታችንን ንጽሕይተ ንፁሃን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከሰዎች ተለይታ እግዚአብሔር አብ ያዘጋጃት ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች መባልን አይቀብሉም፤ ለዚህም ይመስላል በታሕሣስ 28 የጌታ መወለድ የሚበሰርበት እለት ታዓምረ ማርያምን በፍፁም አያነቡም፤ ስለማይቀበሉት ማለት ነው።
Wednesday, June 3, 2026
| ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ |
ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
Friday, May 15, 2026
አርሲ ሮቤ ገድምሳ የደም ምድር ሆና ቀጥላለች፤ ይህች ምድር ለክርስቲያኖች ሲዖል ከኢአማንያን ደግሞ የደም ምድር ሆና ቀጥላለች
| አርሲ የደም ምድር |
ዜጎችን እያስጨረሱ በሰላም ይኖራሉ፤ ሃገረ ስብከት ጠቅላይ ቤተ ክህነት እንዲሁም አብዛኛው ክርስቲያን ይሄ አይመለከተውም ፤ ደም ይፈሳል እንደ ቀጠለ ነው፤ እስከ መቼ ይሆን ይሄ የክርስቲያኖች እልቂት የሚያበቃው?
በሳምንቱ ዛሬ 06/09/2018ዓ.ም. በተመሳሳይ ቦታ እርሻ ና ከብት ጥበቃ ላይ የነበሩ ስምንት ሰዎችና 22 ከብት ከቀኑ 7:00 እስከ 9:00 ሰዓት ባለው ተወስደዋል። ይሄ ማለት የመንግሥት ሃይል ካለበት ከተማ የ15 ደቂቃ እግር መንገድ ማለት ነው።
የተወሰዱት:
1. ተካልኝ እሼቱ
2. አቢቲ አበራ
3. ሚሊዮን ጂማ
4. ካሲዬ ፈለቅ
5. መብራቱ ታደሰ
6. አዲስ አባይነህ
7. መለሰ ጸጋዬ
8. አስናቀ አባይነህ እና 22 ከብት
ሐሰተኛ አጥማቂው በካሊፎርኒያ ግዛት እግድ ወጣበት
![]() |
| ሐሰተኛው አጥማቂ "አባ ዮሐንስ" |
አባል የሆኑት ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሊዎስ እገዳ ደረሰበት፤ ከዚህ በፊት በቴክሳስ ግዛት በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ አውጥቶ ገዝቶ የራሱን ገዳም ለማቋቋም በሚያደርገው ጥረት፤ በምዕመናን እና በአካባቢው ካህንት ከባድ ተቃውሞ ገጥሞት እንደነበረ ይታወሳል፤ የአካባቢው ሃገረ ስብከት ሠራተኞች ማለትም ሊቀ ጳጳሱን እና ዋና ሥራ አስኪያጁ ብቻ ፈቃዱን ሲሰጡ ፤ ሌሎቹ የሃገረ ስብከቱ ሰራተኞች እና ከ11 በላይ የሚሆኑ የዳላስ አካባቢ አጥቢያዎች ከፍተኛ ተቃውሞ በማቅረባቸው ምክንያት ሳይወድ በግዱ አካባቢው ለቆ ፤ "ጅብ በማያውቅበት ሃገር ሄዶ ፤ ቁርበት አንጥፉልኝ አለ" እንደሚባለው በካሊፎርኒያ ግዛት በመሄድ ከዚህ በፊት በጥንቆላ እና በአጥማቂ ስም ከኢትዮጵያ ምዕመናን የዘረፈውን ገንዘብ በካሽ ይዞ አሜሪካን በመሄድ በተለያዩ ስቴቶች እየሄደ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮችን እያወጣ ቦታ መግዛቱን ተያይዞታል።
![]() |
| ሙሉውን ደብዳቤ ከታች ማስፈንጠሪያውን ይጠቀሙ |
Monday, March 9, 2026
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ በመምህር ዘለዓለም ወንድሙ ሕልፈተ ሕይወት የሐዘን መልዕክት አስተላለፉ።
Monday, March 2, 2026
ምንኵስና ታሟልና መድኃኒት እንፈልግለት!!
| በምንኩስና ቆብ ተደብቀው የሚደፍሩ እና ሆድ አደር የሆኑ |
ቆይቷል ብዙዎቹ ማስተካከል ያልቻሉና ለማስተካከልም ትንሽ ድካም ያልደከሙ ሰዎች ብዙዎች ናቸው።
Thursday, February 12, 2026
በደብረ ወገግ አባ ሣሙኤል አሰቦት ገዳም መናኙ አባት ተገለው ተገኙ
በኢሃዴግ ዘምን ብዙ ፈተናዎች እና ብዙ ቤተክርስቲያንን የመግፋት እና ምዕመናንን የምግደል የማሳደድ ታሪክ እንደ ብልጽግና ዘመን ሆኖም ተሰምቶም አይታወቅም፤ በተለይ ባላፉት 7 ዓመታት የተገደሉት እና በግፍ ሕይወታቸውን የተነጠቁ ክርስቲያኖች፣ የተቃጠሉ አብያተ ክርስቲያናት፣ እንዲሁም ሕይወታቸውን የሰዉት ካህናት በኢትዮጵያ ላለፉት 3 ወይም 4 የአገዛዝ ዘመናት ማለትም ፤ በአፄ ኃይለሥላሴ፣ በመንግሥቱ ሃይለማርያም፣ በመለሰ ዜናዊ እና ኃይለማርያም በድምሩ የተገደሉ፣ የተሰዉ፣ የተቃጠሉት ቤተክርስቲያናት በድምሩ የሦስቱም ዘመናት ፤ ዛሬ በአብይ አሕመድ ጊዜ የሞቱት፣ የተቃጠሉት ቤተክርስቲያናት አንድ የተሰዉ ካህናት ቁጥር ሁለት እጥፍ በአሁኑ ማለትም ባለፉት 7 ዓመታት የሆነው በእጅጉ ብዙ ቁጥር ነው እጅግ ዘግናኝም ነው፤
የገዳማውያን ሞት የመንግሥት አልባነት ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ ምልክት ነው! (በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰተ መግለጫ) የእናት ፓርቲ መግለጫ
ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አለኝታ በመሆነ እንደ አማኛም ወይንም እንደ ትክክለኛ ሕዝባዊ የፖለቲካ አደረጃጀት መንግሥት እያደረገ ያለውን እኩይ ተግባር በማውገዝ ይልቁንም በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደርሱትን ብዙ መጠነ ሰፊ አደጋዎች እንግልቶች አንድ አንድን ሃይማኖት ለማጥፋት፣ ለማሳነስ ወይንም character assassination እየተከታተለ ለአባላቱ ይልቁንም ለመላው ኢትዮጵያውያን በመግለጫ ከሚያሳውቁ እና ሕሊና ያላቸው የፖለቲካ መሪዎች ያሉበት ፓርቲ ነው ቢባል ስህተት ሊሆን አይችልም፤ ምክንያቱም በአንድ ሃገር ላይ አንድ ሕዝባዊ ፓርቲ ማለት፤ ለተነሳበት የፖለቲካ ሥልጣን መያዝ ብቻ ሳይሆን በማሕበረሰቡ ውስጥ ያሉትን ችግሮች፣ የመንግሥትን አግባብ ያልሆኑ አካሄዶች፣ የፓርቲዎችን በሌላው ያላቸውን ጣልቃ ገብነት፣ እንዲሁም የሰውን ማሕበራዊ ኑሮ፣ የምጣኔ ሃብት፣ እና አንዱ ከሌላው ጋር ያለውን መስተጋብር ትክክለኛውን እንዲይዝ ማሳወቅ የሚመለክታቸውን የመንግሥት አካላት ማሳሰብ፣ ብሎም ለዚህ
Tuesday, February 10, 2026
A Cry for Justice: The Ongoing Massacre of Orthodox Christians in Oromia
slaughter of 25 Orthodox Christians in October 2025, the killing continues unchecked, uninvestigated, and largely ignored. The most vulnerable children, women, and the elderly are paying the highest price for a crime they did not commit: their faith and identity.
Little Tamrat, just four years old, was shot three times. Doctors now face the unbearable decision to amputate his leg to save his life. Sentayehu, only eight, lies motionless in a hospital bed after surviving both gunfire and a brutal machete blow to the head. These are not statistics. These are children whose lives have been shattered before they had a chance to begin.
Wednesday, February 4, 2026
የሰማዕታቱን ደም አንረሳውም
| ደመ ሰማዕታት ይጣራል |
ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ። ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፤ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጐናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፥ በአመድም ላይ ተቀመጠ። አዋጅም አስነገረ፥ በነነዌም ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፥ እንዲህም አለ፦ ሰዎችና እንስሶች ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ፤ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ” አለ። ዮናስ ወደ ቤተ መንግሥቱ እንኳ መሒዱን አናነብም ነገር ግን ንጉሡ ሳይቀር ለስብከቱ ጆሮ ሰጠ።
Friday, January 23, 2026
የቀበሮ መነኩሴው አባ ፍቅረ ማርያም አንተነህ አጣናው የዋሺንግተን አቡነ ተክለሃማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ (የብልጽና ክንፍ) በሰሜን አሜሪካ እንደሆኑ ተረጋግጧል፤
በቅድሚያ እንኳን ለጌታችን እና ለመድኅኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ሁላችንንም በሰላም አድረሰን እንዲሁም ቅዱስ
| አባ ፍቅረማርያም አጣናው |
ሚካኤል ቃና ዘገሊላ ሁላችንንም በያለንበት በስላም አድረሰን እንላለን፤ ባለፈው በአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳደር ላይ ሰፋ ያለ ዳሰሳ አዘጋጅተን እንዳስተላለፍን ይታወሳል፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአቡነ ተክለሃይማኖት አስተዳዳሪ የሆኑት አባ ፍቅረማርያም አጣናው አንተነህ በአቡነ አብረሃም አማካኝነት ከኢትዮጵያ መጥተው አንገታቸውን ደፍተው የተጠጉ እና የሕዝቡን ፍቅር እና አክብሮት ካገኙ በኃላ ሁኔታዎች በሙሉ በእኔ ቁጥጥር ሥር ነው ብለው በአመኑበት ሰዓት ይልቁንም አሁን ባለው አዲስ በተገዛው ሕንጻ ላይ የበላይነታቸውን ይዘው ከዚህ በኃላ ከእኔ በስተቀር ማንም ሰው በዚህ አጥቢያ ላይ ሊያዝም ሆነ ሊናዝዝ አይችልም ብለው አምነው ወይንም ተመኝተው ሕዝቡንምም ሆነ ማኅበረ ካሕናቱን እየበጠበጡት የሚጉኙት የቀበሮው መነኩሴ ዛሬ ላይ በርካታ ካህናትን በማገድ፤ እንዲሁም ብዙ መከራ አይተው በገንዘብ፣ በእውቀት እንዲሁም በሙያ ሲያግዙ የነበሩትን ምዕመናን ከዚህ በኃላ የዚህ አጥቢያ አባል አይደላችሁም በማለት በማገድ ማሕበረ ምዕመናኑን በተለይ ይቃወኛል ወይም እኔ በምለው መንገድ አይሄድም ብለው ያሰቡትን በሙሉ በማገድ፤ ማኅበረ ምዕመናኑን በማወክ ላይ እንደሚገኙ ለመረደት ችለናል፤ በተለይ በዚህ አጥቢያ ላይ ከባድ የሆነ ይልቁንም በመላው አሜሪካ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የማናለብኝነት እና የጎጠኝነት ሥራቸውን እይሰሩ እያ እያስፋፉ እንደሚገኙ መረጃ ያደረሱን ይሄንን ገልጸውልናል።
Monday, January 5, 2026
ነብዩ ዘካርያስ
| ዘካርያስ |
ሲሆን ትርጓሜውም “እግዚአብሔር አስታወሰ” ወይም “እግዚአብሔር አሰበ ማለት ነው፡፡
Sunday, December 28, 2025
የሠለስቱ ደቂቅ የነገረ መለኮት ትርጓሜ
| ሊቀ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል |
Thursday, December 18, 2025
ጾመ ነቢያት: አስተምህሮ፣ ስብከት፣ ብርሃንና ኖላዊ
የነቢያት ጾም
| ልደተ ክርስቶስ |
ነው፡፡ “ነቢያት የጾሙት ስለምንድን ነው?” ቢሉ ለአዳም የተሰጠውን “አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚለውን የተስፋ ቃል በማሰብ ከሰማየ ሰማያት ይወርዳል፣ ከድንግል ማርያም ይወለዳል፣ በሞቱም ሞት የተፈረደበትን የሰው ልጅ ነፃ ያወጣዋል ብለው ነው፡፡ “ይህንን ጾም የትኞቹ ነቢያት ናቸው የጾሙት?” ቢሉ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ፵ ቀን ጾሟል (ዘጸዓት ፴፬ ፥ ፳፯)፤ ነቢዩ ኤልያስም ፵ ቀን ጾሟል (፩ኛ ነገሥት ፲፱ ፥ ፩)፡፡ በተጨማሪም በተለያየ ዘመን የነበሩት ነቢዩ ዕዝራ፣ ነቢዩ ነህምያ፣ ነቢዩ ዳንኤል እንዲሁም ክቡር ዳዊት ጾመዋል፡፡
Monday, December 15, 2025
በሰሜን አሜሪካ የሚገኙ አባቶች እና ወንድሞች በአሜሪካን ምክር ቤት ፊት ቀርበው የአርሲ ክርስቲያኖችን ጭፍጭፋ መረጃዎችን አጋርተዋል
ዲያቆን ፋሲካው ካሳውን ያካተተ አንድ ጠንካራ አይሰበሬ ባለማዕተብ ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች ልዑክ ባለፈው ሣምንት በሀገረ አሜሪካ በዋሽንግተን ከተማ በአሜሪካ የሚኖሩ፣ እዚያው ተወልደው ባደጉ፣ ዜግነትም ባላቸው ኢትዮጵያውያን የተዋሕዶ ልጆች ያላሰለሰ ተጋድሎና ጥረት በኋላ ከአሜሪካ መንግሥት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የመንግሥቱ ባለሥልጣናት ጋር ታሪካዊ የሆነ የመጀመሪያ ደረጃ ፍሬያማና ውጤታማ ውይይት መደረጉን የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል።
Sunday, December 14, 2025
የሆሮ ጉዱሮ ወለጋ ሃገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ በታጣቂዎች ተገደሉ!!
ሀገረ ስበከት ሥር በምተገኘው በሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ሻንቡ ከተማ መዳረሻ ሲደርሱ መልአከ ኤዶም ቀዲስ ዱጉማ እና በርካታ የህገረ ስብከቱ ሠራተኞችና ወጣት የማሕበራት አገልጋዮች በሕገ ወጥ ታጣቂዎቹ ተወስደው የቆዩ ሲሆን ሌሎቹ ተፈትተው ቆይተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የተመለሱ ሲሆን በትናንትናው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ አፋ እና ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል፤
ዛሬም ኦሮዶክሳውያኑ ተደራጅተን እራሳችንን መከላከል ካልቻልን፤ አንድ በአንድ ተለቅመን እንደምናልቅ ጥርጥር የለውም! " Oromoon Oromoo hin Ajjeesu ማለትም ኦሮሞ ኦሮሞን አይገድልም "የሚለው የኦነግ/ብልጽግና ፍልስፍና ለኦሮሞ ኦርቶዶክስ ሲሆን አይሠራም።ለምን? "ኦርቶዶክስ የአማራ ሃይማኖት ስለሆነ ?"የኦሮሞ ብሔርተኝነትን መስፈርት አያሟላም።እውነታው ይኽ ነው።ዛሬ በወለጋ የተገደሉት ሁለቱም ካህናት ኦሮሞ ናቸው ነገር ግን ግን ከሞት አላመለጡም።ይኽን በመጻፌ ፖለቲካ ውስጥ ገባህ እባል ይሆን?











