![]() |
| ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል |
በፍቅር ጠብቆ አደረሰን በማለት የመልካም ምኞታችንን ከዚህ ከዝግጅት ክፍላችን ለማስተላለፍ እንወዳለን።
መጪውም ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የፍሠሀ፣ እንዲሁም የንሥሃ ዘመን እንዲሆንልን ልባዊ ምኞታችንን ለመግለጽ እንወዳለን፤ በዚህ ሣምንት መጀመሪያ አካባቢ የደረሰንን ዜና ይዘን በዚህ በዓዲስ አመት ለመምጣት ያስገደደን ነገሩ ትንሽ አስደንጋጭ እና አሳሳቢም በመሆኑ ይሄንኑ ከወዲሁ ለማስታወስ እንወዳለን።
በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው የዋሺንግተን ዲሲና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ ፋኑኤል ለአንድ አጥቢያ ምሥራቀ ጸሐይ አቡነ ተክለሃማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት አባ ፍቅረ ማርያም አስተራይ ለተባሉ መነኩስ እጅግ አደገኛ የሆነ ፤ እና የምዕመናንና የሰበካ ጉባኤ አባላትን ሃላፊነት እና ቦታ ያላገናዘበ እጅግ በጣም ከፋፋይ እና መሰሪ የሆነ ደበዳቤ በድብቅ ጽፈው ለአስተዳዳሪው በመስጠት፤ አስተዳዳሪውም ባለፍው ሣምንት ውስጥ ለአካባቢው ፖሊስ ጠርተው የማይፈልጓቸውን ሰዎች ከቤተክርስቲያን ቅጽር እንዲባረሩ እና በድጋሚ ወደ ቤተክርስቲያን እንዳይመለሱ በማድረግ እጅግ በጣም ከባድ እና አደገኛ አካሄድ መጀመራቸውን የሰማንው በዚህ ሣምንት መጀመሪያ አካባቢ ነበር፤











