Friday, May 15, 2026

አርሲ ሮቤ ገድምሳ የደም ምድር ሆና ቀጥላለች፤ ይህች ምድር ለክርስቲያኖች ሲዖል ከኢአማንያን ደግሞ የደም ምድር ሆና ቀጥላለች

አርሲ የደም ምድር
በምሥራቅ አርሲ ልዩ ስሙ ሮቢ ገድምሳ በምትባል ቦታ የክርስቲያኖች መታረጃ ሆና ቀጥላለች፤ በአካባቢው የሚገኙ የመንግሥት አካላት 
ዜጎችን እያስጨረሱ በሰላም ይኖራሉ፤ ሃገረ ስብከት ጠቅላይ ቤተ ክህነት እንዲሁም አብዛኛው ክርስቲያን ይሄ አይመለከተውም ፤ ደም ይፈሳል እንደ ቀጠለ ነው፤ እስከ መቼ ይሆን ይሄ የክርስቲያኖች እልቂት የሚያበቃው? 
በ26/08/2018 ዓ.ም አርሲ ሮቤ ገደምሳ የሚባል ቦታ አየለ ጣሶ የሚባል ክርስቲያን ከዓመት በፊት ሙሉ ከብቱ (8) የተወሰደበት እና ተሰዶ በኪራይ ቤት የሚኖር ሲሆን ቀን ቀን የሉም በማለት እርሻ ላይ እያለ ቀን በቀን በሮቹን ሲወስዱበት እሱ እየተኮሱበት ሊያመልጥ ችሏል።
በሳምንቱ ዛሬ 06/09/2018ዓ.ም. በተመሳሳይ ቦታ እርሻ ና ከብት ጥበቃ ላይ የነበሩ ስምንት ሰዎችና 22 ከብት ከቀኑ 7:00 እስከ 9:00 ሰዓት ባለው ተወስደዋል። ይሄ ማለት የመንግሥት ሃይል ካለበት ከተማ የ15 ደቂቃ እግር መንገድ ማለት ነው።
የተወሰዱት:
1. ተካልኝ እሼቱ
2. አቢቲ አበራ
3. ሚሊዮን ጂማ
4. ካሲዬ ፈለቅ
5. መብራቱ ታደሰ
6. አዲስ አባይነህ
7. መለሰ ጸጋዬ
8. አስናቀ አባይነህ እና 22 ከብት

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

ሐሰተኛ አጥማቂው በካሊፎርኒያ ግዛት እግድ ወጣበት

ሐሰተኛ አጥማቂው እራሱን "አባ ዮሐንስ" በማለት የሚጠራው አሳሳቹ አጭበርባሪው ራስታው በካሊፎርኒያ ግዛት በሚገኙ የቅዱስ ሲኖዶስ
ሐሰተኛው አጥማቂ "አባ ዮሐንስ"

አባል የሆኑት ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሊዎስ እገዳ ደረሰበት፤ ከዚህ በፊት በቴክሳስ ግዛት በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ አውጥቶ ገዝቶ የራሱን ገዳም ለማቋቋም በሚያደርገው ጥረት፤ በምዕመናን እና በአካባቢው ካህንት ከባድ ተቃውሞ ገጥሞት እንደነበረ ይታወሳል፤ የአካባቢው ሃገረ ስብከት ሠራተኞች ማለትም ሊቀ ጳጳሱን እና ዋና ሥራ አስኪያጁ ብቻ ፈቃዱን ሲሰጡ ፤ ሌሎቹ የሃገረ ስብከቱ ሰራተኞች እና ከ11 በላይ የሚሆኑ የዳላስ አካባቢ አጥቢያዎች ከፍተኛ ተቃውሞ በማቅረባቸው ምክንያት ሳይወድ በግዱ አካባቢው ለቆ ፤ "ጅብ በማያውቅበት ሃገር ሄዶ ፤ ቁርበት አንጥፉልኝ አለ" እንደሚባለው በካሊፎርኒያ ግዛት በመሄድ ከዚህ በፊት በጥንቆላ እና በአጥማቂ ስም ከኢትዮጵያ ምዕመናን የዘረፈውን ገንዘብ በካሽ ይዞ አሜሪካን በመሄድ በተለያዩ ስቴቶች እየሄደ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮችን እያወጣ ቦታ መግዛቱን ተያይዞታል።
ሙሉውን ደብዳቤ ከታች ማስፈንጠሪያውን ይጠቀሙ