Friday, May 15, 2026

አርሲ ሮቤ ገድምሳ የደም ምድር ሆና ቀጥላለች፤ ይህች ምድር ለክርስቲያኖች ሲዖል ከኢአማንያን ደግሞ የደም ምድር ሆና ቀጥላለች

አርሲ የደም ምድር
በምሥራቅ አርሲ ልዩ ስሙ ሮቢ ገድምሳ በምትባል ቦታ የክርስቲያኖች መታረጃ ሆና ቀጥላለች፤ በአካባቢው የሚገኙ የመንግሥት አካላት 
ዜጎችን እያስጨረሱ በሰላም ይኖራሉ፤ ሃገረ ስብከት ጠቅላይ ቤተ ክህነት እንዲሁም አብዛኛው ክርስቲያን ይሄ አይመለከተውም ፤ ደም ይፈሳል እንደ ቀጠለ ነው፤ እስከ መቼ ይሆን ይሄ የክርስቲያኖች እልቂት የሚያበቃው? 
በ26/08/2018 ዓ.ም አርሲ ሮቤ ገደምሳ የሚባል ቦታ አየለ ጣሶ የሚባል ክርስቲያን ከዓመት በፊት ሙሉ ከብቱ (8) የተወሰደበት እና ተሰዶ በኪራይ ቤት የሚኖር ሲሆን ቀን ቀን የሉም በማለት እርሻ ላይ እያለ ቀን በቀን በሮቹን ሲወስዱበት እሱ እየተኮሱበት ሊያመልጥ ችሏል።
በሳምንቱ ዛሬ 06/09/2018ዓ.ም. በተመሳሳይ ቦታ እርሻ ና ከብት ጥበቃ ላይ የነበሩ ስምንት ሰዎችና 22 ከብት ከቀኑ 7:00 እስከ 9:00 ሰዓት ባለው ተወስደዋል። ይሄ ማለት የመንግሥት ሃይል ካለበት ከተማ የ15 ደቂቃ እግር መንገድ ማለት ነው።
የተወሰዱት:
1. ተካልኝ እሼቱ
2. አቢቲ አበራ
3. ሚሊዮን ጂማ
4. ካሲዬ ፈለቅ
5. መብራቱ ታደሰ
6. አዲስ አባይነህ
7. መለሰ ጸጋዬ
8. አስናቀ አባይነህ እና 22 ከብት

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

No comments:

Post a Comment