Wednesday, September 2, 2026

ኦቦ በላይ መኮንን ከእሥር መፈታታቸው ተነገረ

No photo description available.
ኦቦ በላይ መኮንን (ዋቄ ፈና)

 

 ኦቦ በላይ ከእሥር መፈታታቸው እየተነገረ ነው፤ 

 ከሦስት ዓመታት በፊት በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ከ7 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማዘዋወር ሞክረዋል በሚል የተከሰሱት ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን በአመክሮ ከእሥር መለቀቃቸው ተዘግቧል። ቀሲስ በላይ በመጀመሪያ የ5 ዓመት እሥራት እና የ10 ሺሕ ብር ቅጣት ተወስኖባቸው የነበረ ቢሆንም፣ በይግባኝ ቅጣታቸው ወደ 3 ዓመት ከ7 ወር ዝቅ ብሎ ነበር። የእሥር ጊዜያቸውን ባጠናቀቁበት ማረሚያ ቤት ባሳዩት መልካም ሥነ-ምግባር ምክንያት በአመክሮ ከእሥር እንዲለቀቁ በመወሰኑ የእሥር ጊዜያቸውን አጠናቀው መውጣታቸውን ዘ-ሃበሻ ዘግቧል።

 የቀሲስ በላይ ቀጣይ ሁኔታ ምን ሊሆን ይችላል? 

ቀሲስ በላይ እደምናስታውሰው የኦሮሚያ ቤተክህነት አደራጅ እና ሃላፊ ሆነው ይሰሩ እንደነበር የሚታወስ ነው፤ ይሄንንም ተከትሎ በተለያየ ጊዜ ከሚሰጡ መግለጫዎች ጋር እና አቡነ ሣዊሮስ እና እነ አቡነ ኤዎስጣቲዎስ እነ አቡነ ዜና ማርቆስ በተደጋጋሚ አብረዋቸው ይታዩ እንደነበር ይታወሣል፤ በመሆኑም በቀጣይነት ለቀሲስ በላይ ከእሥር በፊት የነበራቸውን የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊነትን ይሰጧቸው ይሆን?