Thursday, February 12, 2026

በደብረ ወገግ አባ ሣሙኤል አሰቦት ገዳም መናኙ አባት ተገለው ተገኙ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በገጠር በከተማ የሚገኙ ካህናት መናኞች፣ ሞት ዛሬም ቀጥሏል። በተለይ ባለፈው 
በኢሃዴግ ዘምን ብዙ ፈተናዎች እና ብዙ ቤተክርስቲያንን የመግፋት እና ምዕመናንን የምግደል የማሳደድ ታሪክ እንደ ብልጽግና ዘመን ሆኖም ተሰምቶም አይታወቅም፤ በተለይ ባላፉት 7 ዓመታት የተገደሉት እና በግፍ ሕይወታቸውን የተነጠቁ ክርስቲያኖች፣ የተቃጠሉ አብያተ ክርስቲያናት፣ እንዲሁም ሕይወታቸውን የሰዉት ካህናት በኢትዮጵያ ላለፉት 3 ወይም 4 የአገዛዝ ዘመናት ማለትም ፤ በአፄ ኃይለሥላሴ፣ በመንግሥቱ ሃይለማርያም፣ በመለሰ ዜናዊ እና ኃይለማርያም በድምሩ የተገደሉ፣ የተሰዉ፣ የተቃጠሉት ቤተክርስቲያናት በድምሩ የሦስቱም ዘመናት ፤ ዛሬ በአብይ አሕመድ ጊዜ የሞቱት፣ የተቃጠሉት ቤተክርስቲያናት አንድ የተሰዉ ካህናት ቁጥር ሁለት እጥፍ በአሁኑ ማለትም ባለፉት 7 ዓመታት የሆነው በእጅጉ ብዙ ቁጥር ነው እጅግ ዘግናኝም ነው፤ 


የገዳማውያን ሞት የመንግሥት አልባነት ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ ምልክት ነው! (በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰተ መግለጫ) የእናት ፓርቲ መግለጫ

ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ከሺዎች በላይ ከሚቆጠሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ አንደኛው እና 

ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አለኝታ በመሆነ እንደ አማኛም ወይንም እንደ ትክክለኛ ሕዝባዊ የፖለቲካ አደረጃጀት መንግሥት እያደረገ ያለውን እኩይ ተግባር በማውገዝ ይልቁንም በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደርሱትን ብዙ መጠነ ሰፊ አደጋዎች እንግልቶች አንድ አንድን ሃይማኖት ለማጥፋት፣ ለማሳነስ ወይንም character assassination እየተከታተለ ለአባላቱ ይልቁንም ለመላው ኢትዮጵያውያን በመግለጫ ከሚያሳውቁ እና ሕሊና ያላቸው የፖለቲካ መሪዎች ያሉበት ፓርቲ ነው ቢባል ስህተት ሊሆን አይችልም፤ ምክንያቱም በአንድ ሃገር ላይ አንድ ሕዝባዊ ፓርቲ ማለት፤ ለተነሳበት የፖለቲካ ሥልጣን መያዝ ብቻ ሳይሆን በማሕበረሰቡ ውስጥ ያሉትን ችግሮች፣ የመንግሥትን አግባብ ያልሆኑ አካሄዶች፣ የፓርቲዎችን በሌላው ያላቸውን ጣልቃ ገብነት፣ እንዲሁም የሰውን ማሕበራዊ ኑሮ፣ የምጣኔ ሃብት፣ እና አንዱ ከሌላው ጋር ያለውን መስተጋብር ትክክለኛውን እንዲይዝ ማሳወቅ የሚመለክታቸውን የመንግሥት አካላት ማሳሰብ፣ ብሎም ለዚህ  
የገዳማውያን ሞት የመንግሥት አልባነት ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ ምልክት ነው! 
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰተ መግለጫ)

Tuesday, February 10, 2026

A Cry for Justice: The Ongoing Massacre of Orthodox Christians in Oromia

The bloodshed in Eastern Arsi, Oromia, Ethiopia has not stopped it grows worse each day. After the horrific 
slaughter of 25 Orthodox Christians in October 2025, the killing continues unchecked, uninvestigated, and largely ignored. The most vulnerable children, women, and the elderly are paying the highest price for a crime they did not commit: their faith and identity.

Little Tamrat, just four years old, was shot three times. Doctors now face the unbearable decision to amputate his leg to save his life. Sentayehu, only eight, lies motionless in a hospital bed after surviving both gunfire and a brutal machete blow to the head. These are not statistics. These are children whose lives have been shattered before they had a chance to begin.

Wednesday, February 4, 2026

የሰማዕታቱን ደም አንረሳውም

እነርሱም ማስጠንቀቂያውን ተቀብለው ንሰሐ ገቡ “የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፥ ከታላቁም ጀምሮ እስከ
ደመ ሰማዕታት ይጣራል 

ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ። ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፤ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጐናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፥ በአመድም ላይ ተቀመጠ። አዋጅም አስነገረ፥ በነነዌም ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፥ እንዲህም አለ፦ ሰዎችና እንስሶች ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ፤ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ” አለ።  ዮናስ ወደ ቤተ መንግሥቱ እንኳ መሒዱን አናነብም ነገር ግን ንጉሡ ሳይቀር ለስብከቱ ጆሮ ሰጠ። 

ጾማቸው ሁሉንም ያስተባበረ ነበር። ልጅ፣ አዋቂ፣ ንጉሥ፣ አማካሪዎቹ፣ ሴት፣ ወንዱ፣ እንስሳውን ሁሉ አንድ ሆነ። ራስንም ሀገርንም ማዳን የሚቻለው እንዲኽ በትብብር ሲሆን ነው። “ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ፥ ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩኹ፤ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ” ለንሰሐ ትክክለኛ አብነት ሆኑ። መቶ ሃያ ሺህ ሕዝብ አንድ ላይ መጮሕ ያስገርማል። የሚሰሩትን ክፋት በአንድ ቀን አቆሙ። ያቆሙት ከክፋት ብቻ ሳይሆን ከምቾታቸውም ጭምር ነበር። ከአልጋ ወረዱ፣ መሬት አነጠፉ፣ ንጉሡ ዙፋኑን ለቀቀ፣ መሬት ወረደ። ስውነታቸውን አልታጠቡም ፤ የሚለሰልስ ልብስ አወለቁ የሚወጋጋ የሚቆረቁር ማቅ ለበሱ የሚቀቡትን ሽቱና ቅባት አቁመው አመድ ነሰነሱ አመድ ሰውነት ያቃጥላል ቆዳ ያደርቃል ይሰነጥቃል።

Friday, January 23, 2026

የቀበሮ መነኩሴው አባ ፍቅረ ማርያም አንተነህ አጣናው የዋሺንግተን አቡነ ተክለሃማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ (የብልጽና ክንፍ) በሰሜን አሜሪካ እንደሆኑ ተረጋግጧል፤


በቅድሚያ እንኳን ለጌታችን እና ለመድኅኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ሁላችንንም በሰላም አድረሰን እንዲሁም ቅዱስ 

አባ ፍቅረማርያም አጣናው 


ሚካኤል ቃና ዘገሊላ ሁላችንንም በያለንበት በስላም አድረሰን እንላለን፤ ባለፈው በአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳደር ላይ ሰፋ ያለ ዳሰሳ አዘጋጅተን እንዳስተላለፍን ይታወሳል፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአቡነ ተክለሃይማኖት አስተዳዳሪ የሆኑት አባ ፍቅረማርያም አጣናው አንተነህ በአቡነ አብረሃም አማካኝነት ከኢትዮጵያ መጥተው አንገታቸውን ደፍተው የተጠጉት እና የሕዝቡን ፍቅር እና አክብሮት ካገኙ እና ሁኔታዎች በሙሉ በእኔ ቁጥጥር ስር ነው ብለው በአመኑበት ሰዓት ይልቁንም አሁን ባለው አዲስ በተገዛው ሕንጻ ላይ የበላይነታቸውን ይዘው ከዚህ በኃላ ከእኔ በስተቀር ማንም ሰው በዚህ አጥቢያ ላይ ሊያዝም ሆነ ሊናዝዝ አይችልም ብለው አምነው ወይንም ተመኝተው ሕዝቡንምም ሆነ ማኅበረ ካሕናቱን እየተጠበጡት የሚጉኙት የቀበሮው መነኩሴ ዛሬ ላይ በርካታ ካህናትን በማገድ፤ እንዲሁም ብዙ መከራ አይተው በገንዘብ፣ በእውቀት እንዲሁም በሙያ ሲያግዙ የነበሩትን ምዕመናን ከዚህ በኃል የዚህ አጥቢያ አባል አይደላችሁም በማለት በማገድ ማሕበረ ምዕመናኑን በተለይ ይቃወኛል ወይም እኔ በምለው መንገድ አይሄድም ብለው ያሰቡትን በሙሉ በማገድ፤ ማኅበረ ምዕመናኑን በማወቅ በተለይ በዚህ አጥቢያ ላይ ከባድ የሆነ ይልቁንም በመላው አሜሪካ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የማናለብኝነት እና የጎጠኝነት ሥራቸውን እይሰሩ እያ እያስፋፉ ይገኛሉ።

Monday, January 5, 2026

ነብዩ ዘካርያስ

ዘካርያስ የሚለው ስም “ዛካር”ማስታወስ፣ መዘከር እና “ያህ” ከእግዚአብሔር መጠሪያ ስሞች አንዱ የሚሉትን የሁለት ቃላቶች ጥምር 
ዘካርያስ 

ሲሆን ትርጓሜውም “እግዚአብሔር አስታወሰ” ወይም “እግዚአብሔር አሰበ ማለት ነው፡፡ 

ምንአልባት ዘካርያስ የባቢሎን የስደት ኑሮ መጨረሻ አካባቢ 539 ዓ. ዓ. ተወልዶ ወላጆቹ በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር እኛን ሕዝቦቹ ከስደትና ከጉስቁልና ኑሮአችን ነፃ ሊያወጣን አሰበን፤ እኛን ሕዝቦቹ አስታወሰን ከሚለው ጋር በተያያዘ መልኩ የተሰየመ ሊሆን እንደሚችል ይታመናል፡፡ 

ዘካርያስ የዒዶ ልጅ መሆኑን ቢገለጽም በሌላ መልኩ ደግሞ የቤሬክያ ልጅ እንደሆነም ተነግሯል። ዘካ 1፡1 ስለዚህ ወላጅ አባቱ ዒዶ ወይም ቤሬክያ መሆኑን በትክክል ባይታወቅም እንደነ ቅዱስ ጀሮም ያሉ ሊቃውንቶች ግን ቤሬክያ የዘካርያስ ወላጅ አባቱ ዒዶ ግን መንፈሳዊ አባቱ ሊሆን እንደሚችል መላ ይመታሉ፡፡