Friday, January 23, 2026

የቀበሮ መነኩሴው አባ ፍቅረ ማርያም አንተነህ አጣናው የዋሺንግተን አቡነ ተክለሃማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ (የብልጽና ክንፍ) በሰሜን አሜሪካ እንደሆኑ ተረጋግጧል፤


በቅድሚያ እንኳን ለጌታችን እና ለመድኅኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ሁላችንንም በሰላም አድረሰን እንዲሁም ቅዱስ 

አባ ፍቅረማርያም አጣናው 


ሚካኤል ቃና ዘገሊላ ሁላችንንም በያለንበት በስላም አድረሰን እንላለን፤ ባለፈው በአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አስተዳደር ላይ ሰፋ ያለ ዳሰሳ አዘጋጅተን እንዳስተላለፍን ይታወሳል፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአቡነ ተክለሃይማኖት አስተዳዳሪ የሆኑት አባ ፍቅረማርያም አጣናው አንተነህ በአቡነ አብረሃም አማካኝነት ከኢትዮጵያ መጥተው አንገታቸውን ደፍተው የተጠጉት እና የሕዝቡን ፍቅር እና አክብሮት ካገኙ እና ሁኔታዎች በሙሉ በእኔ ቁጥጥር ስር ነው ብለው በአመኑበት ሰዓት ይልቁንም አሁን ባለው አዲስ በተገዛው ሕንጻ ላይ የበላይነታቸውን ይዘው ከዚህ በኃላ ከእኔ በስተቀር ማንም ሰው በዚህ አጥቢያ ላይ ሊያዝም ሆነ ሊናዝዝ አይችልም ብለው አምነው ወይንም ተመኝተው ሕዝቡንምም ሆነ ማኅበረ ካሕናቱን እየተጠበጡት የሚጉኙት የቀበሮው መነኩሴ ዛሬ ላይ በርካታ ካህናትን በማገድ፤ እንዲሁም ብዙ መከራ አይተው በገንዘብ፣ በእውቀት እንዲሁም በሙያ ሲያግዙ የነበሩትን ምዕመናን ከዚህ በኃል የዚህ አጥቢያ አባል አይደላችሁም በማለት በማገድ ማሕበረ ምዕመናኑን በተለይ ይቃወኛል ወይም እኔ በምለው መንገድ አይሄድም ብለው ያሰቡትን በሙሉ በማገድ፤ ማኅበረ ምዕመናኑን በማወቅ በተለይ በዚህ አጥቢያ ላይ ከባድ የሆነ ይልቁንም በመላው አሜሪካ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የማናለብኝነት እና የጎጠኝነት ሥራቸውን እይሰሩ እያ እያስፋፉ ይገኛሉ።

Monday, January 5, 2026

ነብዩ ዘካርያስ

ዘካርያስ የሚለው ስም “ዛካር”ማስታወስ፣ መዘከር እና “ያህ” ከእግዚአብሔር መጠሪያ ስሞች አንዱ የሚሉትን የሁለት ቃላቶች ጥምር 
ዘካርያስ 

ሲሆን ትርጓሜውም “እግዚአብሔር አስታወሰ” ወይም “እግዚአብሔር አሰበ ማለት ነው፡፡ 

ምንአልባት ዘካርያስ የባቢሎን የስደት ኑሮ መጨረሻ አካባቢ 539 ዓ. ዓ. ተወልዶ ወላጆቹ በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር እኛን ሕዝቦቹ ከስደትና ከጉስቁልና ኑሮአችን ነፃ ሊያወጣን አሰበን፤ እኛን ሕዝቦቹ አስታወሰን ከሚለው ጋር በተያያዘ መልኩ የተሰየመ ሊሆን እንደሚችል ይታመናል፡፡ 

ዘካርያስ የዒዶ ልጅ መሆኑን ቢገለጽም በሌላ መልኩ ደግሞ የቤሬክያ ልጅ እንደሆነም ተነግሯል። ዘካ 1፡1 ስለዚህ ወላጅ አባቱ ዒዶ ወይም ቤሬክያ መሆኑን በትክክል ባይታወቅም እንደነ ቅዱስ ጀሮም ያሉ ሊቃውንቶች ግን ቤሬክያ የዘካርያስ ወላጅ አባቱ ዒዶ ግን መንፈሳዊ አባቱ ሊሆን እንደሚችል መላ ይመታሉ፡፡