Wednesday, August 19, 2015

ልብ ያለው ልብ ይበል


ሰሞኑን በአንድ የፌስ ቡክ ግድግዳ ላይ ተለጥፎ ያየነው ነገር ዓይናችንን ስቦት ትንሽ ነበብ ስናደርገው እንዲህ ይላልኢየሱስ ሳያቆስል የማረካቸውይላል ዝርዝሩን ለመመልከት ጓጓን እና ወደ ውስጥ ገባ ብለን ማንበብ ቀጠልን እንዲህ ይላል
የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብርቅዬ ልጆች የወንጌል ዘማቾች ሰባኪያን ባንድ ዝርዝር ዘማርያን በሌላ ዝርዝር ተዘርዝረው ተመለከትን እንደእውነቱ ከሆነ ሰውየው ጥሩ መረጃዎችን ለኦርቶዶክሳውያኑ የሰጠን ይመስለናል ምክንያቱም ሰውየው ሲዘረዝር ዋናዋናዎቹን ብቻ ነበር የምናውቃቸውብርቅዬዎቹንማለታችን እንደሆነ እንዲሰመርልን እንፈልጋለን ነገር ግን አብዛኛው ኦርቶዶክሳዊ ጋሻ ጃግሬዎቹን ወይንም ተከታዮቹን እንደ ግንባረ ቀደሞቹ ለመሆን የሚጣጣሩን እታች ያሉትን እስከ ዛሬ አናውቃቸውም ነበር ነገር ግን ሰፋ የለ መረጃ ስለሰጠን ቃለ ሕይወትን ያሰማልን እያልን እነዚህን ዝርዝሮች ጎላ አድርገን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ምዕመናን ለማሳወቅ ወደድን በዚህም ይህንን ትንሽ ክታብ ጨምረን ለማቅረብ ተዘጋጀን እነሆ ጋበዝናችሁ ዝርዝሩን ይመልከቱን