Tuesday, February 3, 2015

በዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም የተቀሰቀሰው እሳት በቁጥጥር ሥር ዋለ

  • ቃጠሎው ለአትክልት ልማት ከተደረገ ምንጣሮ ጋራ የተያያዘ መኾኑ ተጠቁሟል
daga-estifanos-church00በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት በዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ደን ውስጥ ዛሬ፣ ጥር ፮ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ከረፋዱ 4፡30 ላይ የተቀሰቀሰው እሳት በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገለጸ፡፡
ቃጠሎው በቁጥጥር ሥር የዋለው ከቀኑ በ9፡00 ገደማ ሲኾን ይኸውም ከቤተ ክርስቲያኑ በግምት ከመቶ ሜትር ባነሰ ርቀት ላይ በደረሰበት ኹኔታ ነው ብለዋል – እሳቱን በማጥፋት የተራዱ የዐይን እማኞች፡፡
የዳጋ እስጢፋኖስን ጨምሮ ከሌሎች የደሴቱ ገዳማት የመጡ መነኰሳት፣ የአቅራቢያው ነዋሪዎች፣ ከባሕር ዳር ከተማ በጀልባ ተጓጉዘው የደረሱ አገልጋዮችና ምእመናን፣ የክልሉ መስተዳድር ተወካዮችና የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሓላፊዎች፣ የባሕር ዳር ዙሪያ ፖሊስና የምዕራብ እዝ ኃይሎች በጋራ ቃጠሎውን በማጥፋት ከፍተኛ የጋራ ርብርብ ማድረጋቸው ተገልጧል፡፡

የቤተ ክርስቲያኒቱ የገቢ ማስገኛ ተቋማት ኪራይ የግለሰቦች መጠቀሚያ መኾናቸው ተጠቆመ

  • ሬት በካሬ በሺሕዎች ዋጋ እያወጣ የቤተ ክርስቲያን በ1.50/2.00 ሒሳብ ተከራይቷል
  • ሀብቷን እና ጥቅሟን የሚያስጠብቅ የኪራይ ተመን ፖሊሲ ጥናት ተጀምሯል
  • የጥቂት አድባራት ሓላፊዎች እንቅስቃሴ ጥናቱን እንዳያኮላሸው ተሰግቷል
  • የአለቆች የመኪና ሽልማት የአማሳኞች ከለላና ለብልሹነት በር የሚከፍት ነው
*       *       *
  • የኪራይ ውሎችንና ሌሎች ሰነዶችን በመደበቅ በአግባቡ ያለማቅረብ፣ የጥናቱን ዓላማ በማጣመም ተቃውሞ ለማነሣሣት መሞከር፣ የልኡካንን ስም ማጥፋትና ሥራውን ማጥላላት ከቀንደኛ አማሳኞችና የምዝበራ ሰንሰለታቸው የሚጠበቁ ተግዳሮቶች ቢኾኑም የጥናቱ ውጤት ቤተ ክርስቲያንን የሚጠቅምና ሀብቷን የሚያስጠብቅ ነውና እንቅስቃሴውን ለሕዝበ ክርስቲያኑ ግልጽ ከማድረግ ጀምሮ ችግሮችን በሓላፊነት ስሜት እየተቋቋሙ ለመሥራት አቋም ተይዟል፡፡
  • ለጥናቱ መነሻ እንደ ሞዴል ያገለግላሉ በሚል የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና የደብረ ምሕረት ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምአብያተ ክርስቲያን ተመርጠዋል፤ የጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤል፣ የደ/ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ፣ የገርጂ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ የብሔረ ጽጌ ቅድስት ማርያም፣ የደ/ገነት ቅዱስ ሚካኤል፣ ቦሌ ቡልቡላ መድኃኔዓለም፣ የጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት፣ የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅ/ገብርኤል…ለጥናቱ ከተለዩት 61 ያኽል አድባራት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡