Thursday, July 25, 2013

በሙስና የተጠረጠሩት የደብረ ጽጌ ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋሉ

  • በተጭበረበረ ውል ደብሩን ከ3 ሚልዮን ብር በላይ በማሳጣትና ሰነድ በማሸሽ ይጠየቃሉ
  • ከጥቂት የሙዳይ ምጽዋት ገቢ ምርመራ ብቻ ከ2 ሚልዮን ብር በላይ ጉድለት ተገኝቷል
  • የአብዛኛዎቹ የደብሩ ሕንጻ ሱቆች የኪራይ ውል በትክክለኛ ሰነድ የተፈጸመ አይደለም
  • ለማተሚያ ቤት አገልግሎት በተከራየው ክፍል በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የማይታወቅ ሞዴላሞዴል እንደሚታተምበት ተጠቁሟል
  • የፕሮቴስታንት ቤተ ጸሎት እንደሚያዘወትሩ የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋ

Dn Mirutse Tikue in Courtበአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ ዲያቆን ምሩፅ ትኵዕ በተጭበረበረ ሰነድ ከተፈጸመ የኪራይ ውል እና ለሒሳብ ምርመራ የሚፈለጉ የሙዳይ ምጽዋት የገንዘብ ቆጠራ ቃለ ጉባኤዎችን ከማሸሽ የሙስና ወንጀል ጋራ በተያያዘ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ፡፡
ዋና ጸሐፊው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት ባለፈው ሳምንት ዐርብ፣ ሐምሌ ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ረፋድ ላይ በደብሩ ጽ/ቤት ባሉበት ሲኾን ከዋና ጸሐፊው ጋራ በተጭበረበረው የኪራይ ሰነድና ውል ለደብሩ የሚገባውን ክፍያ ሳይፈጽሙ የግል ጥቅማቸውን አካብተዋል የተባሉ ሌሎች ሁለት የሕንጻው የንግድ ቤቶች ተከራዮችም በተመሳሳይ ቀን መያዛቸው ተመልክቷል፡፡
በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ከዋሉበት ቀን ጀምሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት ዋና ጸሐፊው ዲያቆን ምሩፅ እና ሁለቱ ተጠርጣሪዎች፣ ሐምሌ ፲፮ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት መቅረባቸው ተገልጧል፡፡
ዋና ጸሐፊውና የጥቅም ተባባሪዎቻቸው ፈጽመውታል የተባለውን ማጭበርበርና ምዝበራ  የሚያረጋግጡ የሰነድ ማስረጃዎችና የሰው ምስክሮች እንዳሉት ለችሎቱ የገለጸው ፖሊስ፣ በዋና ጸሐፊው ላይ ተጨማሪ ማስረጃዎችን ለማሰባሰብና የሰው ምስክሮችን ለማዘጋጀት የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡
ቤተ ክርስቲያን ያቀረበችባቸው ክሥ እንደሌለና ከሣሻቸው እንደማይታወቅ በመጥቀስ የፖሊስን የተጨማሪ ጊዜ ጥያቄ በጠበቃቸው በኩል የተቃወሙት ዲያቆን ምሩፅ÷ የሰባት ቤተሰብ አስተዳዳሪ መኾናቸውን፣ የሚጠየቁትን ማስረጃ ቤተሰቦቻቸው እያቀረቡ መኾኑን፣ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሲውሉ ቢሯቸውን ለመዝጋት እንዳልተፈቀደላቸው እና ሐምሌ ፳፪ ቀን በደብሩ የቅዱስ ዑራኤል ክብረ በዓል በመኾኑ ሥራዎች እንዳይስተጓጎሉ በመጥቀስ የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸውን በውጭ መከታተል እንዲችሉ እንዲፈቀድላቸው አመልክተዋል፡፡ ዮሐንስ አይዳኝ እና ዓለም ፍሥሓየተባሉት ሁለቱ ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው፣ እነርሱ ውል የያዙበት ሰነድ ከሌሎች ተከራዮች የተለየ እንዳልኾነ በመጥቀስ የዋስ መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል፡፡

ደቀ መዛሙርቱ በቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔዎች ተፈጻሚነት ላይ ስጋት ገብቷቸዋል

  • የተነሡ ሓላፊዎን የተመለከቱ የቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔዎች ወጪ አልተደረጉም
  • ንቡረ እዱ÷ አቡነ ጢሞቴዎስ ‹‹በሚሰጧቸው መመሪያ›› እንደሚሠሩ ተናግረዋል
  • ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው መምህራንና ሠራተኞች የሥራ ዋስትና አደጋ ላይ ነው
  • ጥያቄያችን አልተመለሰም ያሉ መምህራን በተቃውሟችን እንቀጥላለን  እያሉ ነው
  • ነገ ፈተና የሚጀምሩት የዘንድሮ ምሩቃን ፈተናቸውን በጨረሱ ማግሥት ይመረቃሉ!
  • ‹‹የተያዘው ጨዋታ ነው፤ መፍትሔ እንደሚሰጡን ከተናገሩ በኋላ እንደ ልጅ ሊያታልሉን እየሞከሩ ነው›› /ደቀ መዛሙርቱ/
  • ‹‹ከዚህ በኋላ አቡነ ጢሞቴዎስ ሊቀጥሉ አይችሉም፤ የእኛ ሥራ ነው፤ ለእኛ ተዉት›› /የቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት ለደቀ መዛሙርቱ/      
Sourse: Hara Zetewahedo
የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

አቡነ ጢሞቴዎስ ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሓላፊነት ተገለሉ፤ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ኮሌጁን በጊዜያዊ ሓላፊነት እንዲመሩ ተመድበዋል

  • አቡነ ጢሞቴዎስ ጉዳያቸው ከሚታይበት ስብሰባ ላለመውጣት ሲለመኑ ውለዋ
  • ፓትርያሪኩ ስለ አቡነ ጢሞቴዎስ ብዙ ከመናገር ተጠንቅቀዋል፤ ተቆጥበዋል
  • ደቀ መዛሙርቱና መምህራኑ ደስታቸውን በቅኔ፣ ወረብና መዝሙር እየገለጹ ነው
  • የቦርድ አባላቱ በሲኖዶሱ ፊት ያሰሙት ያልተጠበቀ ምስክርነት አስተዳደሩን አጋልጧል
  • የአጣሪ ኮሚቴው የመፍትሔ ሐሳቦች እንዲተገበሩ ቅ/ሲኖዶሱ መመሪያ ሰጥቷል
  • የንቡረ እድ ኤልያስ ምደባ ከሚያስነሣው ግዙፍ ጥያቄ ጋራ የምረቃው ቅድመ ዝግጅት ይቀጥላል..
His Grace Abune Timothy
ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ጢሞቴዎስ
ላለፉት 14 ዓመታት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅን በበላይ ሓላፊነት ሲመሩ የቆዩት ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ጢሞቴዎስ ከሥልጣናቸው እንዲገለሉ ቅዱስ ሲኖዶስ መስማማቱ ተገለጸ፡፡
ቅ/ሲኖዶሱ ዛሬ፣ ሐምሌ ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በደረሰበት ስምምነት መሠረት÷ በኮሌጁ ደቀ መዛሙርት እና መምህራን ከፍተኛ ተቃውሞ የተነሣባቸው ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ በበላይ ሓላፊነት ከያዙት ሥልጣን ይገለላሉ፤ ለኮሌጁ አዲስ ሊቀ ጳጳስ እስከሚመድብ ድረስም የመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ‹‹የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ›› ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ በጊዜያዊ ሓላፊነት እየሠሩ እንዲቆዩ ተመድበዋል፡፡

Thursday, July 18, 2013

ዜና ብሥራት ዘሥላሴ! ሐኬተኛው እና መናፍቁ ዘላለም ረድኤት ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እንዲወገድ ቋሚ ሲኖዶስ ወሰነ!

  • መ/ር ፍሥሐ ጽን ደመወዝ በማስተማር ሥራ ብቻ ይወሰናሉ
  • የአቡነ ጢሞቴዎስ ቀጣይነት እየተጤነ ነው
  • የቅ/ሲኖዶሱ አስቸኳይ ስብሰባ ነገ እንደሚካሄድ ይጠበቃል
ጥቅመኛው፣ ሐኬተኛው (ክፋተኛው) እና መናፍቁ ዘላለም ረድኤት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከያዘው የቀን መደበኛ መርሐ ግብር አስተባባሪነት እንዲወገድ ቋሚ ሲኖዶስ ከስምምነት ላይ ደረሰ፡፡
ቋሚ ሲኖዶሱ ከዚህ ዐቢይ የስምምነት ውሳኔ ላይ የደረሰው በኮሌጁ አስተዳደርና በደቀ መዛሙርቱ መካከል ላለፉት ስድስት ወራት እየተባባሰ የመጣውን ውዝግብ ለማጣራት የተቋቋመው ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርት መሠረት በማድረግ ከኮሌጁ መምህራንና የደቀ መዛሙርቱ መማክርት አመራሮች ጋራ ከመከረ በኋላ ነው፡፡

Friday, July 5, 2013

ጨለማ የለውጥ ተግዳሮት

*እስክንድር ገብረ ክርስቶስ
ዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ ፶፱ኛ ዓመት ቁጥር ፻፶፰ ግንቦት እና ሰኔ ፳፻፭ ዓ.ም
                 /መጠነኛ አርትዖት ተደርጎበት የቀረበ/
Ato Eskinder Gebre Kirstos, Head of EOTC General Patriarchate Planning and Development Department
አቶ እስክንድር ገብረ ክርስቶስ
በቤተ ክህነታችን አሠራርና አደረጃጀት ውስጥ የሚታየውን የሙስናና የጎጠኝነት ችግሮች በተመለከተ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ በቤተ ክርስቲያኒቱ ልሳናት በመጠቀም ያልጠቆመው ያላመላከተውና በመረጃ በማስደገፍ ይፋ ያላደረገው ብልሹ አሠራር ይኖራል ተብሎ አይገመትም፡፡ ከቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮዎች እጅጉን በተቃራኒው መንገድ የሚገለጹት የብልሹ አሠራር ምንጮች እንዲወገዱም ምንጮችን እየጠቀሰና መረጃዎችን እያስደገፈ፣ ‹‹ኧረ በሕግ አምላክ! ቤተ ክርስቲያኒቱን እናድናት››በማለት መልእክቱን አስተላልፎአል፤ ሰሚ አላገኘም እንጂ፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በልዩ ልዩ ወቅቱ ያስተላለፏቸው መልእክቶች ቤተ ክርስቲያናችን ከሙስና፣ ጎጠኝነት፣ መድልዎና ጥላቻ የጸዳች እንድትኾን ያላቸውን ቁርጠኛ አቋም የሚያመላክቱ መኾናቸውን፤ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትም ይህን አቋም በእጅጉ እንደሚጋሩት የጽሑፉ አዘጋጅ ስለሚያምን የቅዱስነታቸውን መልእክቶች መነሻ በማድረግ ስለችግሮቹ አስከፊነት ጥቂት ማለቱ አስፈላጊ ኾኖ አግኝቶታል፡፡
ወደ ዋናው የጽሑፌ መልእክት ከመግባቴ በፊት÷ ቤተ ክህነቱ ተቋማዊ ለውጥ ያስፈልገዋል፤ ብልሹ አሠራር፣ ሙስናና አድልዎ ይወገድ የሚል ጠንካራ አቋም ይዘው ለውጥ ለማምጣት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ያደረጉ መሪዎችን ለአብነት ማንሣት የጽሑፌን ሐሳብ ስለሚያጠናክር ጥቂት ለማለት ወደድኹ፡፡
ለአብነት ጥናታዊ ጽሑፍ አዘጋጅተው ሲያበቁ የጥናቱ ጠቃሚነት በቅጡ ሳይጤን በግፍ ከቤተ ክርስቲያኒቱ እንዲለቁ የተገደዱትን አቶ በድሉ አሰፋን እናንሣ፡፡ አቶ በድሉ አሁን በዋና ሥራ አስኪያጅነት ከሚመሩት ተቋም አንጻር ያስመዘገቡት ውጤት በትክክልም የለውጥ ሰው መኾናቸውን፣ ኋላቀር አሠራር ጠላልፎ ሊጥለው የደረሰውን የአንበሳ የከተማ አውቶቡስ ድርጅት በተግባር በመለወጥ ሊጠቀስ የሚችል ሥራ ሠርተው አሳይተውናል፡፡ እኒያን የተግባር ሰው ያጣው ቤተ ክህነታችን ቁጭት ውስጥ ገብቶ ለለውጥ እንዲዘጋጅ የሚያነሣሣው ጠፍቶ አባቶችን ካባቶች የሚያለያይ ነግሦበት ከረመ፡፡ በመሠረቱ አቶ በድሉ የጨለማው ቡድን ሰለባ መኾናቸውን ስንቶቻችን እናውቅ ይኾን?

በሙስና የተጠረጠሩት የመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል የሓላፊነት ምደባ ታገደ

ቋሚ ሲኖዶስ የውጭ ግንኙነት መምሪያ ዋና ሓላፊ ኾነው እንዲሠሩ የመደባቸው መ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ከሙስና ተግባር ጋራ በተያያዘ በቀረበባቸው አቤቱታ ምክንያት የፈቀደላቸው ምደባ እንዲታገድ ማድረጉ ተገለጸ፡፡
ቋሚ ሲኖዶሱ ሰኔ ፲ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤትና በሥሩ ለሚገኙ ልዩ ልዩ መምሪያዎችና ድርጅቶች ባካሄዳቸው ምደባዎች መ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ከቅርሳ ቅርስ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ ዋና ሓላፊነት ወደ ውጭ ግንኙነት መምሪያ ዋና ሓላፊነት ተዛውረው እንዲሠሩ ፈቅዶላቸው ነበር፡፡
ይኹንና መ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል የቅርሳ ቅርስ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ ዋና ሓላፊ ኾነው በቆዩባቸው ሦስት ዓመታት ከፍተኛ የገንዘብ ብክነትና የቅርስ ማሸሽ ተግባራት ስለ መፈጸማቸው ልዩ ልዩ አካላት ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩና ለቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት የክሥ አቤቱታዎችን በማቅረባቸው በውጭ ግንኙነት መምሪያ የተፈቀደላቸው የዋና ሓላፊነት ምደባ ታግዶ እንዲቆይ መወሰኑ ተገልጧል፡፡
Dn. DANIEL SACKED FROM HIS POSITIONበቁጥር 1/1188/2005 በቀን 14/10/2005 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ተፈርሞ የወጣውና በአድራሻ ለመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል የተጻፈው ደብዳቤ፣ መ/ር ዳንኤል ላለፉት ሦስት ዓመታት ከቆዩበት የቅርሳ ቅርስ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ መነሣታቸውን ያስታወቃቸው ሲኾን በአስተዳደር መምሪያ የሠራተኞች አስተዳደር ዋና ክፍል ክፍል ተገኝተው ሪፖርት እንዲያደርጉ በመግለጽ ሲሠሩበት የነበረውን ቢሮ፣ ወንበር፣ ጠረጴዛና ዶኩመንቶች በቦታው ለተመደቡት መ/ር ሰሎሞን ቶልቻ የጠቅላላ አገልግሎት ዋና ክፍል በሚመድበው አረካካቢ እንዲያስረክቡ አዝዟቸዋል፡፡