Thursday, June 27, 2013

አቡነ ጢሞቴዎስ ለቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔ አልታዘዝ ብለዋል

  • ቋሚ ቅ/ሲኖዶስ ለኮሌጁ የመደባቸውን ሓላፊ አልቀበልም ብለዋል
  • ከኮሌጁ እንዲባረር የተወሰነበትን ዘላለም ረድኤትን ዋና ዲን ለማድረግ አስበዋል
  • ደቀ መዛሙርቱና መምህራኑ ለከፍተኛ ተቃውሞ እየተዘጋጁ ነው
  • ፓትርያሪኩ ለአቡነ ጢሞቴዎስ ተጽዕኖ የማደር ዝንባሌ እየታየባቸው ነው
በጠቅላይ ቤተ ክህነታችን መልክ መያዝና እልባት ማግኘት ከሚገባቸው ጉዳዮች አንዱ ውሳኔን በተግባር ተፈጻሚ ለማድረግ ያለመቻልልምሾነት ነው፡፡ ችግሩ ከሁሉ በፊት፣ ከፍተኛ አመራሩ በመግለጫው ያስቀመጠውን ያህል ለውሳኔው ተፈጻሚነት አለኝ የሚለውን ቆራጥ አቋም አጠያያቂ የሚያደርግ ነው፡፡ በሌላ በኩል ይኸው ‹‹ጥርስ አልባነት›› የሚያረጋግጥልን÷ ተጽዕኖ ፈጣሪዎችና ጥቅመኞችአስተዳደራዊ መዋቅራችንን በማይናቅ ደረጃ እንደተቆጣጠሩትና በአንዳንድ አብነቶች ተስፋ ሰጪ መነሣሣቶች እየታዩበት በሚገኘው የለውጥ ርምጃ ላይ በቀጣይነት የሚጋርጡትን ስጋትና ዕንቅፋት ነው፡፡ ጥቂት አስረጅዎችን እንጥቀስ፡-
የቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔዎች የተፈጻሚነት ጅምር ሚዛን

ዶ/ር አባ ኀይለ ማርያም መለሰ የጠቅ/ቤ/ክ ም/ሥራ አስኪያጅ ኾኑ፤ የመምሪያዎችና ድርጅት ሓላፊዎች ምደባም ተደርጓል

  • ለተመደቡበት ሥልጣን ፍጹም የማይመጥኑ ሓላፊዎች መካተታቸው ነጋገረ
  • ‹‹የተቋማዊ ለውጡን ሂደት ከአመስጋኝ አማሳኞች ድለላ መከላከል ይገባል፡፡››
Dr Aba Hailemariam Melese
ዶ/ር አባ ኀይለ ማርያም መለሰ
የጠቅ/ቤ/ክ ም/ሥራ አስኪያጅ
ቋሚ ቅ/ሲኖዶስ ዛሬ፣ ሰኔ ፲ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ለመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ም/ዋ/ሥራ አስኪያጅነት በቀረቡት ዕጩ ላይ በመስማማት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ እንዲሾሙ አድርጓል፤ የልዩ ልዩ መምሪያዎችና ድርጅቶች ዋና ሓላፊዎች ምደባም ተካሂዷል፡፡

ከሓላፊነቱ የታገደው ‹አባ› ጳውሎስ ከበደ ከአስተዳዳሪነቱ ተነሣ

ላለፉት ስምንት ዓመታት ለመዝባሪ እና የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ አቀንቃኝ ቡድኖች/ግለሰቦች ሽፋን በመስጠት፣ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀ/ስብከትን በአጠቃላይ የሐረር ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት በተለይ ሲያውክ የቆየው መልአከ ጽዮን ‹አባ› ጳውሎስ ከበደ ከአስተዳዳሪነቱ መነሣቱ ተገለጸ፡፡
ርምጃው የተወሰደው በዛሬው ዕለት ሲኾን የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በጉዳዩ ላይ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ ጋራ ከመከሩ በኋላ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ በተሰጠ ውሳኔ መኾኑ ተገልጧል፡፡
‹አባ› ጳውሎስ በደብሩ አስተዳዳሪነት ከተሾመበት ፲፱፻፺፰ ዓ.ም ጀምሮ ለለየላቸው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ አራማጅ ግለሰቦች፣ ለእነርሱ በተላላኪነት ለሚያገለግሉ ሕገ ወጥ ሰባክያንና ዘማርያን የመድረክ አገልግሎት ዕድል በመስጠት ለብዙዎች መሰናከል ኾኖ ቆይቷል፡፡
ከግንቦት ወር መጨረሻ አንሥቶ ደግሞ የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ለቁጥጥር ያሸገውን የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤትና ሙዳይ ምጽዋት በመከፋፈት፣ በአምሳያው ያደራጀውን የዘረፋና ኑፋቄ ቡድን በማሰማራት የደብሩን ሀብት በግላጭ ሲመዘብር ሰንብቷል፤ ከዚህም በላይ የደብሩ አስተዳደር ከሀ/ስብከቱና ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ማእከላዊ መዋቅር እንደተለየና ለማንም እንደማይታዘዝ በማወጅ በሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ላይ መጠነ ሰፊ የዐመፅ ቅስቀሳ ለማካሄድ ሲዘጋጅ እንደነበር ታውቋል፡፡
የቤተ ክህነታችን ብስልና ጥሬ! በፈጸሙት ጥፋትና ክሕደት የሕግ ተጠያቂነት ሳይሆን ከቦታ ወደ ቦታ ማዘዋወርን እንደ መፍትሔ የሚወስደው ቤተ ክህነታችን ከሐረር ደብረ ሣህል ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እልቅና ያነሣውን ‹አባ› ጳውሎስ ከበደን፣ የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አበምኔት አድርጎ ነው የሾመው!!!
ምንጭ: ሐራ ዘተዋሕዶ
የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

የተሐድሶ መናፍቃንና ጥቅመኞቻቸው የሐረር ደ/ሣ/ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ከሀ/ስብከቱ አስተዳደር ለመለየት እየቀሰቀሱ ነው

  • መናፍቃኑና ጥቅመኞቻቸው ሽፋን ሲሰጥ የቆየው የደብሩ አለቃ ከሓላፊነቱ ታግዷል!
  • በሀ/ስብከቱ የታሸገው የሰበካ ጉ/ጽ/ቤትና ሙዳይ ምጽዋት ተከፍቶ ገንዘቡ ተመዝብሯል
  • የሀ/ስብከቱን ሥራ አስኪያጅ እያስጨነቁ የሚገኙት አለቃውና ግብረ በላዎቹ በሊቀ ጳጳሱ ላይ ሁከት ለመቀስቀስ እየተዘጋጁ ነው፤ የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት የክልሉ ፍትሕና ጸጥታ ቢሮ ሰላምን የማስከበር ርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል
  • ‹‹ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጀምሮ ሊቃነ ጳጳሳቱ ሁሉ ሌቦች ናቸው፡፡›› /አለቃው ‹አባ› ጳውሎስ ከበደ ለተከታዮቹ ካሰማው የመድረክ ንግግር/
  • የቤተ ክህነቱ የመዋቅርና አሠራር ለውጥ ርምጃ÷ እንደ ‹አባ› ጳውሎስ ያለብቃታቸው የተሰገሰጉ፣ የቤተ ክርስቲያን አሐቲነትና ተቋማዊ ነጻነት ፀር የኾኑ የሙስናና ኑፋቄ መሸሸጊያዎችን በስፋትና በጥልቀት በማጥራት መጀመር ይኖርበታል

Wednesday, June 5, 2013

ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአ/አ ሀ/ስብከት የፓትርያሪኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ኾነው ተመደቡ

ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ
የርክበ ካህናት ቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬ፣ ግንቦት ፳፷ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም የቀትር በፊት ውሎው፣ የጅማ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የኾኑትንብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያሪኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ኾነው እንዲሠሩ በብዙኀኑ አባላቱ ድምፅ ደግፎ መድቧቸዋል፡፡
ብፁዕነታቸው በሀ/ስብከቱ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ ረዳት ሊቀ ጳጳስ እንዲኾኑ የተደረገው ምደባ የቅ/ሲኖዶሱን ይኹንታ ያገኘው በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ አቅራቢነት ነው፡፡ ይኸውም በ1991 ዓ.ም በቅ/ሲኖዶስ ጸድቆ በወጣው የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ልዩ መተዳደርያ ደንብ፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የመላው አህጉረ ስብከት ማእከል በመኾኑ ፓትርያሪኩ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን በቋሚ ሲኖዶስ እያስወሰነ በበላይነት እንደሚመራና እንደሚቆጣጠር በተገለጸበት አንቀጽ 7 ንኡስ ቁጥር 1 የተደገፈ እንደኾነ ተገልጧል፡፡
የልዩ መተዳደርያ ደንቡ መውጣት በቃለ ዐዋዲው አንቀጽ 43 ንኡስ አንቀጽ 4 ድንጋጌ የተመለከተ ቢኾንም ሊቀ ጳጳሱን የፓትርያሪኩ ረዳትየሚያደርገው አንቀጽ በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 35(2)÷ ‹‹እያንዳንዱ ሀ/ስብከት ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጀምሮ በቅ/ሲኖዶስ በተሾመ ሊቀ ጳጳስ ወይም ጳጳስ ይመራል›› በሚል ከተደነገገው ጋራ የሚቃረን ነው፤ ‹‹ረዳት›› የሚል ቅጽል የለውምና፡፡

Tuesday, June 4, 2013

ሰበር ዜና – ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኾነው ተመርጠዋል፤ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ኾነው ተሠይመዋል


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ግንቦት ፳፯ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም አምስተኛ ቀን ጥዋት የስብሰባ ውሎው የሰቲት ሁመራ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሉቃስን የቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ኾነው እንዲሠሩ ሠይሟል፤ የወላይታ ዳውሮ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስን ደግሞ የመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አድርጎ መርጧል፡፡
His Grace Abune Lukas
ብፁዕ አቡነ ሉቃስ
የቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ ፳፭ ንኡስ አንቀጽ ፩ እና ፬ መሠረት÷ ቅ/ሲኖዶስ በምልአተ ጉባኤውና በቋሚ ሲኖዶስ በየጊዜው በሚያደርገው ስብሰባ ላይ ሁሉ የሚነጋገርባቸውን ርእሰ ጉዳዮች የማዘጋጀት፣ ውሳኔዎቹን ሁሉ በተግባር ላይ መዋላቸውን የመከታተል ሥልጣንና ተግባር የብፁዕ ዋና ጸሐፊው ነው፡፡
በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ ፴ ንኡስ አንቀጽ ፱ መሠረት ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ÷ ቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎን የማስፈጸም ሥልጣነ ክህነት፣ በቂ የትምህርት ደረጃና ችሎታ ያላቸውን ሦስት ሰዎች ለም/ሥራ አስኪያጅነት በዕጩነት ለቋሚ ሲኖዶስ አስቀርበው ቅ/ሲኖዶስ ሲስማማበት የማስመረጥና በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ የማሾም ሥልጣን አላቸው፡፡ በዚሁ አንቀጽ ንኡስ ቁጥር ፲ መሠረት የመምሪያና የድርጅት ሓላፊዎችን እያጠኑና እያስመረጡ ፓትርያሪኩን በማስፈቀድ ይሾማሉ፡፡
His Grace Abune Mathewos
ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ
የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ/ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ
በሙሰኛና ጎጠኛ ቡድኖች ሤራ የምክነት ስጋት ያንዣበበት የተቋማዊ ለውጥ ዕቅዱ በሁለቱ ብፁዓን አባቶች አመራር የመስጠት ክሂልና የማስፈጸም ትጋት ከፍጻሜ ደርሶ የቤተ ክህነታችንን ትንሣኤ እንደሚያሳየን እናምናለን፡፡

ቤተ ክርስቲያን በአደጋ ላይ! የቅ/ሲኖዶሱ ስብሰባ ሂደት በፅልመታዊው ጎጠኛና ሙሰኛ ቡድን ተጽዕኖ እንዳይጠለፍ ተሰግቷል


  • የጠ/ቤ/ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅነት ምርጫ ሊቃነ ጳጳሳቱን እርስ በርስ አደፋፍጧል
  • ርእሰ መንበሩ ስብሰባውን በአግባቡ ለመምራትና ለመጠቅለል ተስኗቸዋል ተብሏል
  • በሙሰኝነትና ጎጠኝነት በተዘፈቁበት ተግባራቸው ከሚመጣባቸው ተጠያቂነት ራሳቸውን ለማዳን የተባበሩ ጳጳሳትለተቋማዊ ለውጡ ስጋት ደቅነዋል፤ የፓትርያሪኩን የተቋማዊ ለውጥ ይኹንታዎች ተፈታትነዋል፤ አቡነ ሳዊሮስ፣ አቡነ ማርቆስ፣ አቡነ ፋኑኤል፣ አቡነ ዲዮስቆሮስ፣ አቡነ ቄርሎስ እና አቡነ ሕዝቅኤል ይገኙበታል
  • ምክትል ዋ/ሥራ አስኪያጁን ጨምሮ ልመታዊውን ቡድን በብርቱ የተቋቋሙ የተቋማዊ ለውጡ አውራዎችከሓላፊነታቸው እንዲነሡ መወሰኑ ተሰምቷል፤ራሳቸውን በሙሰኛና ጎጠኛ አሠራር ከመጠየቅ ለማዳን የሚረባረቡ ጳጳሳት ቡድናዊነትና ለዋ/ሥራ አስኪያጅነት ምርጫው የተያዘው መደፋፈጥ በሰፈነበት አጋጣሚ በአጀንዳው ዝርዝር ሳይካተት ም/ዋ/ሥራ አስኪያጁን ከሓላፊነት የማንሣት ውሳኔ የተላለፈበት ኹኔ ተኰንኗል
  • ምክትል ዋ/ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ውብሸት ከሓላፊነት የተነሡበት ምክንያት ‹‹ክህነት የላቸውም››  በሚል ቢኾንም ቄስ አይሏቸው መነኵሴ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ቦታውን ለመረከብ አሰፍስፈዋል፤ የአራት መኖርያ ቤቶችና አንድ የንግድ ቤት ባለቤት መኾናቸው የተረጋገጠው ንቡረ እዱ የፀረ – ሙስናውን እንቅስቃሴ በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ለማክሸፍ ተነሣስተዋል
  • ‹‹የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ስብከተ ወንጌል ነው›› በሚል የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ እንዲፈርስ ተወስኗል፤ የጠ/ቤ/ክህነቱ አስተዳደር መምሪያ ዋና ሓላፊ ታግደዋል፤ ውሳኔው ‹‹በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ ድንጋጌ መሠረት ደረጃውን ጠብቆ ያልተወሰደ፣ በፅልመታዊው ቡድን ጎጠኝነት የተገፋና የፀረ – ሙስና ትግሉን የሚያደናቅፍ የቂም በቀል ርምጃ ነ፤›› በሚል ተተችቷል
  • የፀረ – ሙስና እርምት ርምጃዎችን፣ የአስተዳደራዊ መዋቅር እና ፋይናንስ ሥርዐት ለውጦችን አጥንቶ የሚያቀርብበሁለት ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ የባለሞያዎች ኮሚቴ እንዲቋቋም ተወስኗል፤ ሕጉንና ቃለ ዐዋዲውን የማሻሻል ጅምርሥራዎች የማስፈጸምና የስልታዊ ዕቅዱ ዝግጅት በኮሚቴው ይከናወና
  • የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት በአንድ ረዳት ሊቀ ጳጳስና በአራት ሥራ አስኪያጆች እንዲመራ የቀረበው ሐሳብእያከራከረ ነው
የርክበ ካህናት ቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሁለተኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ከተጀመረ አራተኛ ቀኑን አስቆጥሯል፡፡ ግንቦት ፳ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የመክፈቻ ጸሎት ያካሄደው ምልአተ ጉባኤው 18 ያህል አጀንዳዎችን በማጽደቅ ዛሬን ጨምሮ በሥራ ላይ በቆየባቸው አራት ቀናት 13 ያህል አጀንዳዎችን ተመልክቶ ውሳኔ ማስተላለፉ ተዘግቧል፡፡

ምንጭ: ሐራ ዘተዋህዶ
የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም