Tuesday, August 28, 2012

“መንግስት በአደባባይ የሚሰራቸውን ስህተቶች ቤተክርስትያን የእርምት እርምጃ እንዲወስድ የጠየቀችበት ጊዜ የለም” አቡነ ጢሞቲዎስ

ብፁዕ አቡነ ጢሞቲዎስ ዶክተር 

  •   “የቤተክርስቲያን መሪዎች መንግስት እንዳይነቀፍ ብለው ቤተክርስትያኒቱና ክርስትያኖች መብታቸው ሲነካ ዝም ብለው ካዩ የእግዚአብሔርን አደራ አልጠበቁም ፤ መንግስትንም ባለመምከራቸው ጎዱት እንጂ አልጠቀሙትም” አቡነ ጢሞቲዎ
  •    “ከእግዚአብሔር የመጣው መዓት እግዚአብሔር መዓቱን እስኪመልሰው ድረስ ከመጸለይ በስተቀር ምንም ለማድረግ አይቻልም” አቡነ ጢሞቲዎ
  •   “መንግስት ሃይማኖታችሁን ልንካ ካለ ግን ለሃይማኖታችሁ ፤ ለክብራችሁ ለመብታችሁ መሟገት እንዳለባችሁ እመክራችኋለሁ” አለቃ አያሌው ታምሩ
  •  “እውር ገደለ ታሰኝኛለህ እንጂ አንተን እዚህ እደፋ ነበር፡፡” ኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማሪያም ለአለቃ አያሌው ታምሩ የተናገረው
(አንድ አድርገን ነሐሴ 22 2004 ዓ.ም)፡- ከዛሬ 12 ዓመት በፊት ህዳር 8 1992 ዓ.ም አቡነ ጢሞቲዎስ ከ”ምኒልክ መጽሄት” ጋር ያደረጉትን ቃለ መጠይቅ ዘወር ብለን ለናንተው ለማቅረብ ወደድን ፤ ይህ መጽሄት በጊዜው ለአቡነ ጢሞቲዎስ ያቀረበላቸው ጥያቄና እሳቸው የሰጡት መልስ ጥቂቱን አሁን ካለንበት ሁኔታ ጋር ምን እንደሚመስል ለማየት እንሞክራለን ፤  በጊዜው አቡነ ጢሞቲዎስ የቅድሥት ሥላሴ  መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሃላፊ ሆነው ያስተዳድሩ ነበር፡፡

ድህረ አቡነ ጳውሎስ ሰዎች ምን ይላሉ?


  • “ስለ ሁሉም ግን መስማትና ማመዛዘን የሚችል አባት እንዲሰጠን ጸሎት ይዘናል”የተሀድሶ አቀንቃኝ ፊት አውራሪ 
  •  “ሞት ርስታችን ነው ፤ ጉዳዩ የቅደም ተከተል ነው ፤ የአቡነ ጳውሎስ ሞት ባያስደስተኝም  እግዚአብሔር ግን ይችን ቤተክርስትያን አሳረፋት” አንድ ሊቀ ጠበብት አባት
 
(አንድ አድርገን ነሐሴ 21 2004 ዓ.ም )፡- ባሳለፍነው ሳምንት በተከሰቱት ሁለት ትልልቅ ክስተቶች ላይ ሰዎች ትንሽ የመደናገጥ ስሜት ተፈጥሮባቸው ተስተውለዋል ፤ አንዱ ክስተት የአቡነ ጳውሎስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየት ነበር ፤ የፓትርያርኩ ሞት ከተሰማ ጀምሮ በርካታ ሰዎች ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ነበር ፤ የፓትርያርኩን ስንብት ላይ የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን 3 ሊቃነ ጳጳሳት ፤ 2 የግሪክ ኦርቶዶክስ  ሊቃነ ጳጳሳት ፤ በተጨማሪ በአሜሪካ ኒውስተን ዩኒቨርሲቲ 4 ተወካዮችን ጨምሮ የግብጽ ኮፕት ቤተክርስትያን 10 ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ከህንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን 5 አባላት ያሉት ቡድን ፤ የአለም አብያተ ክርስትያናት ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ ዶ/ር ኦላቭ እና 3 ሊቀ ጳጳሳት ፤ የአፍሪካ አብያተክርስትያናት ጸሀፊ  ዶ/ር አንድሪ ካራቫጋ እንዲሁም የዓለም ሀይማኖት ለሰላም 4 ሊቀጳጳሳት የአቡነ ጳውሎስ የቀብር ስነስርዓት ላይ ለመታደም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል  ተገኝተዋል፡፡

የዋልድባ አብረንታንት መነኰሳት መሰደድ ጀምረዋል



  • ባለፉት ጥቂት ቀናት ከስድስት ያላነሱ መነኰሳት ተሰደዋል
  • “ታጋይ ገድላችኹ እናንተ አትኖሩም” (የፀለምት - ማይ ፀብሪ ወረዳ ሓላፊዎች)።

 (ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 21/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 27/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ በዋልድባ አብረንታንት ገዳም መነኰሳት ላይ ባተኰረውና ካለፉት አራት ቀናት ጀምሮ እየተባባሰ በቀጠለው እስርና እንግልት ሳቢያ ከስድስት ያላነሱ መነኰሳት የፀለምት - ማይ ፀብሪ የፀጥታ ኀይሎች በሚያደርሱባቸው ግፍ ሳቢያ ወደ ሌሎች ገዳማት መሰደዳቸውን፣ በተቀሩትም አባቶች ላይ ድብደባ እየተፈጸመባቸው መኾኑን የሥፍራው ምንጮች እየገለጹ ናቸው፡፡
የዜናው ምንጮች እንደሚያስረዱት÷ የወረዳው ፖሊሶችና ታጣቂዎች በገዳሙ መነኰሳት ላይ የሚፈጽሙት እንግልትና ድብደባ የተባባሰው የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ኅልፈተ ሕይወት መሰማቱን ተከትሎ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽኑ ሕመም እና ኅልፈት ገዳማውያኑን ተጠያቂ በማድረግ ነው፡፡ ቀደም ሲል በየጊዜው እየታሰሩ በተለቀቁት አበው መነኰሳት ላይ ያነጣጠረው ይኸው ርምጃ በአሁኑ ወቅት ደግሞ መነኰሳቱ ጨርሶ ገዳሙን ለቀው እንዲወጡ ከማዘዝና ከማስገደድ ጋራ የተያያዘ መኾኑም ተመልክቷል፡፡

Thursday, August 23, 2012

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ ሥርዐተ ቀብር ዛሬ ይፈጸማል



  • የኮፕት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበር ይገኛሉ።
  • አቶ መለስ ዜናዊ (ገብረ እግዚአብሔርበጸሎተ ቅዳሴው ታስበዋል።
  • ጊዜያዊ ጠ/ሚ ኃ/ማርያም ደሳለኝ ይገኛሉ።
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 17/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 23/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አምስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ሥርዐተ ቀብር ዛሬ፣ ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም በ6፡00 በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል፡፡ ትናንት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ጸሎተ ቅዳሴ ተከናውኗል፡፡ በዚህ ወቅት የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል እንደተናገሩት÷ “የቤተ ክህነቱም የቤተ መንግሥቱም መሪዎቻችን በአንድ ቦታ እንገናኝ ብለው የተቃጠሩ ይመስል በአንድ ወቅት ተጠርተው ሄደዋል፡፡ ሁለቱንም መሪዎች ተራ በተራ እንሸኛቸዋለን፤ ተራ በተራ ነው የምንሸኛቸው፤” ብለዋል፡፡

Monday, August 20, 2012

(ሰበር ዜና )የጠቅላይ ሚኒስቴር መለሰ ዜናዊ ሞት በETV ተረጋገጠ

ጠቅላይ ሚኒስቴር መለሰ ዜናዊ እኝህ ነበሩ RIP
ላለፉት ፳ ዓመታ የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ፕሬዘደንት ከዛም ጠቅላይ ሚኒስቴር በመሆን ያገለገሉት ጠቅላይ ሚኒስቴር መለሰ ዜናዊ ላለፉት ሁለት ወራት በሕዝብ መገናኛዎች አለመታየታቸው በተለያዩ ተንታኞች ሕይወታቸው ማለፋቸውን ሲነገር እንደነበር ይታወሳል፣ ነገር ግን የተለያዩ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት በመገናኛ ብዙሐን ባሰራጩት ዜና መሰረት መታመማቸውን እንጂ የመሞታቸውን ዜና ከሕዝብ ተደብቆ እስከ ዛሬ ምሽት ድረስ ተደብቆ  የቆየ ቢሆንም ነገር ግን ዛሬ እረፋዱ ላይ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጣቢያ መሞታቸውን ለሕዝብ ይፋ ያደረገ አድርጓል።

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

ቅ/ሲኖዶስ የቀብር ቀን እንዲቀየር የቀረበውን ጥያቄ አልተቀበለውም

  • የፓትርያርኩ ቤተሰቦች “በሕግ እንጠይቃለን” እያሉ ነው፤ ፓትርያርኩ የቤተሰቦቻቸው ወይስ የቤተ ክርስቲያን?
  • የሰላም እና አንድነት ጉባኤ ልኡካን አዲስ አበባ ይገባሉ፤ ጉባኤው ልዩነት በአንድነት ሳይፈታ ሌላ ፓትርያርክ የመሾሙን ጉዳይ ቅ/ሲኖዶስ እንዲያስብበት ተማፅኗል፤ የመንግሥትንም እገዛ ጠይቋል።
  • የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለፓትርያርኩ ሥርዐተ ቀብር አፈጻጸም ዝግጅት እያደረገ ነው።
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 15/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 21/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዜና ዕረፍት ከተሰማበት ቀን አንሥቶ አጠያያቂ ከኾኑት ጉዳዮች መካከል ሐዘናቸውን በሚገልጹ አንዳንድ ወገኖችና ብዙኀን መገናኛ ዘንድ የሚሰማው “ቤተሰቦቻቸው” የሚለው ቃል ነው፡፡

Thursday, August 16, 2012

(UPDATED) የአቡነ ጳውሎስ ዜና ዕረፍት ጉዳይ ከተጨማሪ መረጃዎች ጋር

  •  READ THIS UPDATED NEWS IN PDF
  • በአንድ የመንግሥታዊው ባንክ ቅርንጫፍ ሦስት አካውንቶች ውስጥ በፓትርያሪኩ የተለያዩ ዘመዶች ስም ከ22 ሚልዮን ብር በላይ መከማቸቱ ተጠቁሟል፤
  • የተወሰኑ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አስከሬናቸው ባለበት በዳጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል ተገኝተው ሥርዐተ ግንዘቱን አከናውነዋል፤ ጥቅመኛዋ እጅጋየሁ በየነ “አልሞቱም፤ አስከሬናቸው ይመርመርልኝ” እያለች በማወክ ላይ ትገኛለች፤
  • ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአህጉረ ስብከት ሓላፊዎች፣ የአድባራትና ገዳማት አለቆች በአስቸኳይ ወደ አዲስ አበባ እንዲገቡ ጥሪ ተደርጓል፤
  • የአቡነ ጳውሎስን ቀብር የሚያስፈጽም ኮሚቴ በመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ጽ/ቤት ተቋቁሟል፤ መኖሪያ ቤታቸውና ቤተ መጻሕፍት ወመዘክሩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ታሽጓል፤ በእንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንና በሌሎችም ቦታዎች የሚገኙ ሙዝየሞች ለጎብኚዎች ዝግ ተደርገው ጥበቃው እንዲጠናከር ታዝዟል፤
  • ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ጉባኤ በማካሄድ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያሪክ ይሾማል፤ ከቋሚ ሲኖዶሱም ጋራ እየመከረ ይሠራል፤ (ሕገ ቤተ ክርስቲያን)
  • “ውሉደ ጳውሎስ” /እነ እጅጋየሁ በየነ/ በፓትርያሪኩ ስም “ጳውሎስ ፋውንዴሽን” ለማቋቋም እየተሯሯጡ ነው፤ የሀብት ቅርምቱን ለማመቻቸት ይኾን?

የአቡነ ጳውሎስ ጳውሎስ ዜና ዕረፍት አጭር ሪፖርታዥ



  • የአቡነ ጳውሎስን ቀብር የሚያስፈጽም ኮሚቴ በመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ጽ/ቤት ተቋቁሟል፤ መኖሪያ ቤታቸውና ቤተ መጻሕፍት ወመዘክሩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ታሽጓል፤
  • ጥቂት ብፁዓን አበው ወደ ባልቻ ሆስፒታል ሄደዋል፤ አስከሬናቸው በባልቻ ሆስፒታል ይገኛል፤ ጥቅመኛዋ እጅጋየሁ በየነ “አልሞቱም፤ አስከሬናቸው ይመርመርልኝ” እያለች በማወክ ላይ ትገኛለች::
     ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአድባራትና ገዳማት አለቆች በአስቸኳይ ወደ አዲስ አበባ እንዲገቡ ጥሪ ተደርጓል::
  • የአቡነ ጳውሎስን ቀብር የሚያስፈጽም ኮሚቴ በመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ጽ/ቤት ተቋቁሟል::
  • ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ይሾማል፤ ከቋሚ ሲኖዶሱም ጋራ እየመከረ ይሠራል::(ሕገ ቤተ ክርስቲያን)
  • “ውሉደ ጳውሎስ” /እነ እጅጋየሁ በየነ/ በፓትርያርኩ ስም “ጳውሎስ ፋውንዴሽን”ለማቋቋም እየተሯሯጡ ነው፤ የሀብት ቅርምቱን ለማመቻቸት ይኾን?
  • በፓትርያርኩ በተለያዩ ዘመዶቻቸው ስም በአንድ የመንግሥታዊው ባንክ ቅርንጫፍ ሦስት አካውንቶች ውስጥ ከ22 ሚልዮን ብር በላይ እንደሚገኝ ተጠቁሟል::
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 10/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 16/ 2012/READ THIS NEWS IN PDF) ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዛሬ፣ ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም፣ ንጋት ላይ በዳጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

(ሰበር ዜና) ቅዱስ ፓትርያርኩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ


(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 10/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 16/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ ኻያኛ ዓመት በዓለ ሢመታቸውን ከሐምሌ 5 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ወሩ መገባዳጃ ሲያከበሩ የቆዩት አምስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በጠና ታመው ነሐሴ 8 ማምሻውን ወደደጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል ከገቡ በኋላ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ማረፋቸውን ምንጮቻችን እየገለጹ ነው። አቡነ ጳውሎስ በምንገኝበት የፍልሰታ ለማርያም ጾም የሰሞኑ ውሏቸው በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ጸሎተ ቅዳሴ ላይ እንደነበሩ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን ፓትርያርኩን ለሕልፈት ያበቃውን ሕመም ለይተው አልገለጹም፡፡

እግራቸው ከጉልበታቸው በታች በከፍተኛ ደረጃ መጎዳቱንና የጤናቸው ኹኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ የሚነገርላቸው ፓትርያርኩ÷ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንደሚስተዋለው የአባ ጳውሎስ መውጣትና መግባት ግራና ቀኝ በሚይዟቸው ሰዎች ድጋፍ እንደሚከናወን የተዘገበ ሲሆን ራሳቸውን ችለው መራመድ ይኹን ከመኪናቸው መውጣትና መውረድም እንደተሳናቸው ተመልክቷል፡፡ አቡነ ጳውሎስ ለረጅም ጊዜ ሕመማቸውን ሲከታተሉ በቆዩበት የደጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል ዶክተሮች ከፍተኛ ክትትል ላይ መኾናቸውንና አስጊ በሚባል ኹኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ምንጮችን ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ደጀ ሰላም ዜናውን እየተከታተለች ማቅረቧን ትቀጥላለች።

ቸር ወሬ ያሰማን፤
አሜን፡፡

የተዋሕዶ ቤተሰቦች በመላው ዓለም

Wednesday, August 8, 2012

ውዳሴ ማርያም አንድምታ ዘይትነብብ በዕለተ ስሉስ



ውዳሴሃ ለእግዝትነ ማርያም ድንል ወላዲተ አምላክ ዘይትነብብ በዕለተ ሠሉስ 
ለምስጋና ሁለተኛ ለፍጥረት ሦስተኛ ቀን ነው በዚህም ቀን እመቤታችን ትመጣች የብርሃ ምንጻፍ ይነጸፋል የብርሃን ድባብ ይዘረጋል ከዚያ ላይ ሁና ሰላም ለከ ፍቁርየ ኤፍሬም ትለዋች እርሱም ታጥቆ እጅ ነስቶ ይቆማል ወድሰኒ ትለዋች በዕለተ 
ሰኑይ ድርክር አልቋልና ባርክኒ ይላታ በረከተ ወልድየ ወአቡሁ ወመንፈስ ቅዱስ ይኅድር በሳዕሌከ ትለዋች ተባርኮ ምስጋናዋን ይጀምራል፡፡ ውዳሴ ዘሠሉስ ውዳሴ በሠሉስ ውዳሴሃ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ዘይትነበብ በዕለተ ሠሉስ ይላል ቃለ ጸሐፊ ነው፡፡ እርሱ ግን አክሊለ ምክሕነ ይጀምራል አክሊለ ምክሕኒ፡፡ አክሊል የወዲህኛው ምክሕ የሰዲያኛው፡፡ ወቀዳሚተ መድኃኒትነ፡፡ ቀዳሚት የወዲህኛው መድኃኒት የወዲያኛው፡፡ መወሠረተ ንጽሕነ፡፡ መሠረት የወዲህኛው ንጽሕ የወዲያኛው፡፡ ኮነ በማርያም፡፡ በማርያም ድንግል ሆነልን አለ በዚህ ቀን ከነገሥታት ዳዊትን ከመሳፍንት ኢያሱን ከደናግል ኤልያስን አስከትላ መጥታለች ዳዊት ምንም ንጉሠ ነገሥት በህትባ የመመኪያችንን ዘውድ ማምጣት አልተቻለህም፡፡ ኢያሱም መድኃኒት ብትባል የደኅንነታችን መጀመሪያ መሆን አልተቻለህም፡፡ ኤልያስም ንጹሕ ድንግል ብትባል የንጽሕናችን መሠረት ዘውድ የደኅንነታችን መጀመሪያ የንጽሕናችን መሠረት ድንግል ምርያም ናት ሲል ነው፡፡ አንድም አክሊሎሙ ለሰማዕት እንዲለው አክሊለ ሰማዕት የሚባል ጌታ ጥንተ ሕይወቶሙ እንዲለው ጥንተ ሕይወት የሚባል ጌታ አኃዜ ዓለም በእራኁ ኲሉ ኁዝ ውስተ እዴሁ መሠረተ ዓለም ይጾውር ድደ ወይነብር ጠፈረ እንዲል፡፡ መሠረተ ዓም የሚባል ጌታ በድንግል ማርያም ማለት ፍጽምት ማለት ነው፤ ለጊዜው መልክ ከደም ግጋት ስተባብራ ተገኝታለች ፍጻሜው ግን ንጽሐ ሥጋ ከንጽሐ ነፍስ ድንጋሌ ሥጋ ከድንጋ ነፍስ አስተባብራ ተገኝታለችና አንድም ጸጋ ወሀብት ማለት ነው፤ ለጊዜው ለናት ላታቷ ጸጋ ሁና ተሰጥታለች ፍጻሜው ግን ለሰው ሁሉ ጸጋ ሁና ተሰጥታለችና አንድም መርሕ ለመንግሥተ ሰማያት ማት ነው፡፡ ምዕመናንን መርታ ገነት መንግሥተ ሰማያት አግብታለችና አንድም ልዕልት ማለት ነው ሮም አአርያ ማለት ልዑል ማት እንደሆነ፡፡ እርስዋንም መትሕተ ፈጣሪ መልዕልተ ፍጡራን ይላታልና፡፡ አንድም ማኅበረ መሃይምናን ወሕዝብ ተለአኪተ እግዚአብሔር ወሰብእ ተፈሥሒ ቤተ እስራኤል ወተሐሠዪቤተ ይሁ ማለት ነው፡፡ አንድም ማርያም ማት እግዝእተ ብዙኃን እንዲ አይለውም ብሎ ማርያም ማለት ቅሉ እግዝእተ ብዙኃን ማለት ነው፡፡ አብሃም ማለት አበ ብዙኃን ማለት እንደሆነ፡፡ እንተ ወለደት ለነ ዘአእግዚአብሔር ቃለ፡፡ መመኪያነቷን በቅጽል አመጣው አካላዊ ቀልን በወለደችልን በድንግል ማርያም ተገኝልን፡፡ ዘኮነ ሰብአ በእንተ መድኃኒትነ፡፡ እኛን ስለማዳን ሰው የሆነ፡፡ እምድኅረ ኮነ ሰብአ ጥዩቀ አምላክ ፍጹም ውእቱ፡፡ ሰውም ከሆነ በኋላ ፍጹም አምላክ ነው ፡፡ ሐራ ጥቃ ቃል ሥታ ኮነ ያውን ይዘው ወደታች ተለወጠ ይላሉና፡፡ ሰውም ከሆነ በኋላ ፍጹም አምላክ ነው አለባቸው፡፡ ወበእንተዝ ወለደቶ እንዘ ድንግል ይእቲ፡፡ ስለዚህ ነገር ማኅተመ ድንግልናዋ ሳይለወጥ ወለደችው፡፡ መንክር ኀይለ ወሊዶታ ዘኢይ ትነገር፡፡ ድንቅ የሚሆን የመውለዷ ሥራ የማይመረመር ነው ፡፡ የማይመረመር የመውለዷ ሥራ ድንቅ ነው፡፡ በማይመረመር ግብር ከወለድሽው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለሚኚልን፡፡ ሐተታ እንደ ሰኞ፡፡ እስመ በፈቃዱ፡፡ በርሱ ፈቃድ፡፡ ወበሥምረተ አቡሁ፡፡ ባበቱ ፈቃድ ወመንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ፡፡ መጽአ ወአድኃነነ፡፡ ሰው ሆኖ አዳን፡፡ አንድም ሰው ሁኖ አድኖናልና፡፡ መንድር ብህ እስር፡፡ መጽአ በኲርሕ፡፡ በግድ ሰው ሆነ የሚሉ መናፍቃን አሉና እሰመ በፈቃዱ አበባቸው፡፡ በዕለተ ፍጥረት አብ መንፈስ ቅዱስ፡፡ አዳም ስሑት ፍጥረት ነው፡፡ አይፈጠር ቢሉ ወልድ እኔ ያዛለሁ ይፈጠር ብሎ ነበርና በግድ ሰው ሆነ የሚሉ መናፍቃን አሉና እስመ በፈቃዱ አለባቸው፡፡ እሊህንም እመቦ ዘይቤ ተሐብዩ ለብእሲ እምቅድመ ይፍጥሮ ውጉዘ ለይኩን ብሎ ሊቁ በዐሥራ አንደኛው ግዝት አንሥቷቸዋል፡፡ ኒህስ ምን ያለውን ይዘው ተነሥተዋል ቢሉ በዕርገተ ኢሳይያስ ሰማዕኩ እዘ ይአኤዝዞ እግዚእ ለእግዚእየ ወይቤሎ ኅልፍ እንተ ሰብዐቱ አናቅጸ ሰማያት ወረደ ላዕሌሁ ለመልአከ ሞት ካው ተሐብዩ የሚል ጥሬ አገኘን ብለው ይኸንን ይዘው ተነሥተዋል፡፡ ዐቢይ ውእቴ ስብሐተ ድንግልናኪ አማርያ ድንግል ፍጽምት፡፡ በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ፍጽምት የምትሆኚ እመቤታችን በድንግልና ጸንተሸ ብትገኚ ላንቺ የተሰጠሸ ጸጋ ፍጹም ነው፡፡ ርከብኪ ሞገስ እግዚአብሔር ምስሌኪ፡፡ እግዚ አብሔር ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ካንቺ ጋራ አንድ ባሕርይ ቢሆን ባለሟልነትን አግኝተሸልና፡፡ አንድም በጸጋ ቢያድርብሽ ባለሟልነትን አግኝተሸልና ላንች የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ አንቲ ውእቱ ሰዋሰው ዘርእየ ያዕቆብ እምድር ዘይበጽሕ እስከ ሰማይ ወመላእክተ እግዚአብሔር የዐርጉ ወይወርዱ ወስቴታ፡፡ መጽሐፍ ምሥጢር እንጂ ዘይቤ አይጠነቅቅምና ዘይበጸሕ ብሎ ውሰቴታ አለ ከምድር እስከ ሰማይ ተተክላ መላእክት ስወጡባት ሲወር ዱባት ያዕቆብ በፍኖት ሎዛ ያያት የወርቅ መሰላል አንቺ ነሽ ታሪክ ያዕቆብ ወደ ሶርያ ሲሄድ ሎዛ ሲደርስ ጊዜ መሸበት ከመንገዱ እልፍ ብሎ ድንጊያ ተንተርሶ ተኛ ሌሊት በራእይ የወርቅ መሰላል ከምድር እስከ ሰማይ ተተክላ መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት ዙፋን ባላዋ ላይ ተዘርግቶ ንጉሥ በላዋ ላይ ተቀምጦባት ሲወርዱባት ዙፋን ባላዋ ላይ ተዘርግቶ ንጉሥ በላዋ ላይ ተቀምጦባት ያያል ሲነጋ ተነሥቶ ደንጊያ ተክሎ ዘይት አፍስሶባት ዛቲ ይአቲ ኆኅታ ለሰማይ ዝየ ይትሐነጽ ቤተ እግዚአብሔር ብሎ ይሔዳል፡፡ ይኸም ምላሴ ነው የወርቅ መሰላ የመቤታችና ደንጊያው የትንቢተ ነቢያት እመቤታችን በትንቢተ ነቢያት ጸንታ ለመገኘቷ ምሳሌ፡፡ ድንግል አምሳ ወትንቢት ዘነቢያት እንዲል፤ መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት አለ ቤታችን ከመቤታችን ሰው ከነሆኑ አስቀድሞ ለተልእኮ አይወጡም አይወርዱም ነበር ጌታችን ከመቤታችን ሰው ከሆነ በኋላ ግን ለተልእኮ የሚወጡ የሚወርዱ ሆነዋልና አንድም የዐርጉ ሰው አምላክ ሆነ ይወርዱ አምላክ ሰው ሆነ እያ፤ ዙፋ የማኅፀኑዋ ንጉሥ የጌታ ምሳሌ፡፡ ንድም ደንጊያው የታቦት ዘይት የሜሮን ምሳሌ፡፡ አንድም ያዕቆብ የቀሳውስት ደንጊያው የአሕዛብ ዘይት የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ፡፡ ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ በአምሳለ ንጉሥ ካየው ልጅሽ ጽንዕት በድንግ፤ማ እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡: ይቆየን...........